Get Mystery Box with random crypto!

አንሙት አብርሃም

የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የሰርጥ አድራሻ: @animutabraham
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.51K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-02-14 08:08:07

588 views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 08:05:51

569 views05:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 23:06:56 "የአውዳሚ ፕሮጀክቱ" ሒደቶች...

[አንሙት አ.]
--
⁽⁽የኦሮሞ ብሔር ግንባታ ፕሮጀክት⁾⁾: አያሌ አውዳሚ ግቦችንና ስትራቴጂዎችን የሚከተል እንደሆነ ባለፉት ዓመታት የነካካቸው ነገሮች ሁሉ ምስክር ናቸው።

⁽⁽ በአንዱ ዓመት እንደ አምስት ዓመት መሥራት⁾⁾ በሚል እየተሮጠበት ያለው የብሔር-ግንባታ ፕሮጀክት ፡ የ"ማፍረስ" እና የ"መልሶ መበየን" ስትራቴጂ የሚከተል መሆኑ አንድ ጉዳይ ነው።
አውዳሚ ቀውሶች መፈልፈልን ጨምሮ ከፕሮጀክቱ ⁽⁽ማሳኪያ⁾⁾ እና ⁽⁽ማስጠበቂያ⁾⁾ መንገዶች ውስጥ ጦርነት፣ ጭፍጨፋ፣ የጅምላ ማፈናቀልን የመሠሉ ስልቶችን የሚከተል መሆኑ አውዳሚነቱንና አፍራሽነቱን የከፋ አድርጎታል።

ፕሮጀክቱ እንዲሳካ "የኃይል አማራጭን" ጭምር ተዘጋጅቶበት፡ በጠረጴዛው ላይ አስቀምጦ የሚንቀሳቀስ በመሆኑ ከእስካሁኑም የባሰ ውድመት ወደፊት ይጠበቃል።
መደበኛ እና ኢ-መደበኛ ሠራዊትን ያቀናጀው የኃይል አማራጭ፡ ኦሮሚያ ክልልን በታሪክ ከፍተኛ የታጠቀ ሠራዊት ባለቤት አድርጎታል። ዛሬም በሐረርጌ ሚሊሻዎችን ሲያስመርቅ ውሏል።

በዚህ ወቅት ከሁሉም ክልሎች ጋር የወሰንና ድንበር ቅራኔ ውስጥ የገባው በአውዳሚ ስልቶች በሚመራው ፕሮጀክት አላማ የተነሳ ነው።
እነ'ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የማኦኮሞንና ካማሺ ዙሪያ ወረዳዎችን አስረክበው ዝም ያሉት፡ "አሶሳ የእኛ ነው" በሚለው የጨፌው ፕሮጀክት፡ ወደፊት ክልሉ እንደማይኖር ተረድተውት ሊሆን ይችላል።
እነሐረሪ የተበሉ እቁቦች የሆኑት፣ ድሬዳዋን፡ "ዙሪያዋን የማስተካከል" ሥራዎች የሚሠሩት ፣ በሌሎችም ክልሎች በኢ-መደበኛው ሠራዊት የሚሠራው "አጥቅቶ በር የማስከፈት" ተልዕኮ ክልሎችን በር ዘግቶ ለቅሶ ውስጥ ከቷቸዋል።
አንዳንዶች ወረዳ ተወሮባቸው አዲስአበባ ላይ በሚታደላቸው የባሕል ማዕከል መሥሪያ ካርታ እየተፅናኑ ቀጥለዋል።

ሌላም ሌላም..

መፈናቀልን እንጂ መንቀሳቀስን በሚከለክለው የፕሮጀክቱ አካል ፡ "በኦሮሚያ የሚኖረውን ሌላ ሕዝብ ማስወጣት" እና "ወደ አዲስአበባ እና ኦሮሚያ የሚመጣን ሕዝብ መግታት" በዋና አላማነት እየተሠራበት ነው።
እንደ ማውደሙ፡ ሕዝብን "ማስወጣቱም" ሆነ "አለማስገባቱ" የሚመለከተው ሰሜኑን መሆኑ ግልፅ ከሆነ ቆየ።
ከጭፍጨፋ ተርፈው ተፈናቅለው አዲስአበባ መድረስና መጠለልም ክልክል ነው።
በደብረብርሐን እና በጎጃም መስመሮች እንጂ፡ በናዝሬት ወይ በሐዋሳ አሊያም በአንቦ መስመሮች መታወቂያ እየቀሙ ከመንገድ መመለስ የለም።
ምክንያቱም "ፕሮጀክቱ" :መውጣት እንጂ መግባትን የሚከለክለው "ባሕላዊ-ሰሜንን" ነው።

እነ'ተመስገን ጥሩነህ እና መሠል ብዐዴናውያን ፡ የመጡበት ክልል ማሕበረሰብ "የፀጥታ ስጋት ስለሆነ መግባት የለበትም" ተብሎ ሲመሰቃቀል፣ ልክ ነው ብለው ያስፈፅማሉ።
"ፕሮጀክቱን የማደናቅፍ" አቅም ያለው የኃይል ሚዛን የተፈጠረ ሲመስል፡ ሰበብ ይቀመጥላቸውና ፡ እሥርና ማሳደዱን ከታዘዙት አስበልጠው ይሠሩታል።
ያደጉባትን ቤተክርስቲያን "አፍርሰን እኛን እናስመስላት" ሲባሉ፡ እሺ ብለው ጎዳና ላይ የሠራዊት ልምምድ ያደርጋሉ።

አሉልህ ደግሞ፡ የሆኑ "አማራዎች" !
ይሔ ስርዓት እና መንግስት አንድ ነገር ከሆነ ፡ ⁽⁽አማራዊ ጥቅማችን አይሳካም⁾⁾ ብለው ገትረው የቆሙ! እንዲህ ያለ "የፕሮጀክቱ ስትራቴጂካዊ አጋርነት" በዘርህ አይድረስ!!

ሚሊዮኖች ተፈናቅለው በየድንኳኑ በተቀመጡባት አገር፡ የተፈናቀለ ሕዝብ ያነሳት ይመስል፤ "ፕሮጀክቱ" ስትራቴጂካዊ ተግባር አድርጎ በፈጠረው "የሸገር ከተማ አስተዳደር" በተባለው የአዲስአበባ ዙሪያ፡ "ሕገወጥና የጨረቃ ቤት" በሚል "የብሔር ማፅዳት" እየተፈፀመ መሆኑን የሚኮንን የመንግስት ሹመኛ ጠፍቷል።

የሚሆንባቸውን እያዩ ያሉት ክልሎች "ስለምትበለፅገዋ ኢትዮጵያ" እና "የኢትዮጵያዊነት ሱስ"፡ በሚነገራቸው "የማቆያ ወግ" ታጥነዋል። Because Some are CONVINCED, others are CONFUSED!

Such a Destructive ⁽⁽Nation building project⁾⁾ !!

ሁሉም ቀውሶች እና ውድመቶች "ፕሮጀክቱን" የሚያገለግሉ ናቸው።
እነ'ዲማ ነገዎ፣ ሌንጮ ለታ፣ ወዘተዎች የ50 ዓመታት ናፍቆትና ስሌት በስተርጅና እያስኬዱት መሆኑ እድለኛ ያስብላቸው ይሆን!?
673 views20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-12 16:44:55
⁽⁽ የመንግስት ተግባር ብዝበዛ እና ጭቆና እስከሆነ ድረስ!

ግድያ እስከሆነ ድረስ!

ደም ማፍሰስ እስከሆነ ድረስ!

የሕዝቡም ሥራ ይበልጥ እየደረጀ የሚሔድ አቢዮት መሆኑን ልትጠራጠሩት አይገባም!!

ጭቆና አለ !! ጭቆና እስካለ ትግል አይቀርም!! ⁾⁾

--
1966 ዓ.ም የኢትዮጵያ ተማሪዎች ንቅናቄ መሪ የአቋም መግለጫ ንግግር፤
631 views13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 23:15:43 ሕያው የዘመን ምስክር!
-
⁽⁽ተቋም⁾⁾ እና ⁽⁽ተቋማዊነት⁾⁾ ብርቅ በሆነበት የአፍሪቃ ምድር፣ ከሁለት ሺህ ዓመታት በላይ ፡ ክፉና ደጉን እያስተናገደች የዘለቀች ሕያው አሕጉራዊ ተቋም ነች።

በአፍሪካ የአገር ምስረታ ሒደቶች፡ የኢትዮጵያን አገር ምስረታ ሒደቶችን የተለየ ገፅታ የሠጠች ልዩ እና ታሪካዊ ተቋም ነች።
ሲሶ መንግስት በመሆን፡ አውሮፓ የተመራበት የFighting, Praying, Tilling፡ ማለትም የአራሽነት ፣ ተኳሽነት እና ቀዳሽነት፡ አገራዊ ወጋግራ ⁽⁽የሶስቶዮሽ ሥሪትን⁾⁾፡ የጠበቀችና ያቆመች፡ አምድ ነች።

እንደ አፄ ዘረያዕቆብ ያከበራት ፣ እንደአፄ ፋሲል የሞገታት ፣ እንደአፄ ቴወድሮስ የደፈራት፣ እንደአፄ ዮሐንስ ጠበቃ ሆኖ ያገለገላት አልነበረም፤ ሁሌም ግን በቦታዋ ነበረች፣!!

በዘመኗ፡ አፄ ሱስንዮስንም፣ አፄ ዮሐንስንም ፡ አፄ ቴዎድሮስንም ፣ ሊቀመንበር መንግስቱንም አይታለች።

በኢትዮጵያ ላይ መጥቶ ይህችን ተቋም ያልነካ፡ ተድላ እና ፈተና የለም። በዚህች አገር ላይ የወረደ ፀጋና መርገምት የእሷም ነበር/ነው።

የአዳል ሱልታኔትን ጥቃት፣ የእየሱሳውያን መልዕክተኞችን ሴራ ፣ የመሐዲስቶችን እና የኦሮሞ ተስፋፊዎችን መከራዎች ፣ የቱርክን እና ግብፅን ተቃርኖ ደባዎች እንዲሁም የፖርቹጋልን ደጋፊነት አልፋዋለች።

በውስጧም፡ የቅብዓት፡ ተዋህዶ፡ የአምልኮ አተያይ ልዩነት ፈተና ንጧታል፤

ግን ቀጥላለች!

ጉድለት አለባት!
ፈተናዎችም አብረዋት ነበሩ።
መወደድ እና መተቸትን የሚጋብዝ ቁመና ይሁን እምነት አይጠፋትም።

ግን፤

ከዜሮ ድምር የሚነሳ የፖለቲካ ሽግግር በሚንጣት አገር ፡ ተቋማዊ ቀጣይነትን፣ ተቋማዊ መርህና እሴትን ፣ ተቋማዊ ትዝታ ፣ የእምነትና ታሪክ ውርስ ቀጣይነትን ከዚህች ተቋም የተሻለ የሚያስረዳ የታሪክ ማሕደር፡ በኢትዮጵያ ምድር የለም።

ክብር ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን !!
710 views20:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-10 18:00:03 ⁽⁽የቋሚ ቀውስ ፖለቲካዊ ስትራቴጂ⁾⁾

ቀውስን የቁጥጥር እና ትኩረት መበተኛ አድርጎ የመውሰድ ፖለቲካ ለአንዳንዶች ከፖለቲካነት ይልቅ በሰዎች ደምና ውድመት የሚቆመር ኢ-ሰብዓዊነት ነው።

ለአንዳንዶች ግን አገርን ሙሉ ለሙሉ ለመቆጣጠር ፣ ተገዳዳሪን ለማስወገድና ለማዳከም፣ ተገዳዳሪ የተደረገን አካል አቅሞችና እሴቶችን በማውደም (Destruction) ለሚሠራ የDeconstruction እና Reconstruction ሥራ ቁልፍ ስትራቴጂካዊ መሣሪያ ተደርጎ ይወሰዳል።

"Permanent crisis justifies permanent control of everybody and everything by the agencies of the central government "

የሚፈጠር ቀውስ የሕዝብን ትኩረት ሰቅዞ በመያዝ ፣ ከቀውሱ ጀርባ የሚሠራውን የማፍረስና የመቆጣጠር ተግባር እንዳይመለከተው ፣ እንዳያጤነው ያደርጋል። ቢያጤነውና ቢመለከተውም በሙሉ አቅሙ ወደመከላከልና ማስቆም እንዳይመጣ ቀውሱ እረፍት አይሰጠውም።

ስለሆነም የተፈለገው ዓላማ እስኪሳካ ፡ ተገዳዳሪ ያሉትን አካል: ከአንድ ቀውስ ወደ ሌላ ቀውስ በማዘዋወር እረፍት ይነሱታል።
"ቋሚ ወይንም የተራዘመ ቀውስ" የቁጥጥርና ውድመት ሒደቱ የአመራር ዘይቤ ተደርጎ ይሠራበታል።

በኢትዮጵያ እየሆነ ያለውም ይሔው ነው !

የግለሰቦች ግድያ ማከናወን ➙የንፁሐን ጅምላ ግድያዎችና ሠፊ መፈናቀል➙ የማይረጋ የካቢኔ ሹምሽር ማከናወን ➙ ለሁለት አመት የዘለቀ ጦርነት ➙ በመሐል ብቅ በሚሉ ፋታዎች ወቅት የታጣቂ ጭፍጨፋ ማስፈፀም➙ ጦርነቱ ፋታ ሲሰጥ የተራዘመ ቀውስ ፍለጋ የእምነት ተቋማት ውስጥ መገኘት ➙ ሌላም ሌላም ቀውስና የታጣቂ ጭፍጨፋዎችን በቋሚነት ማስፈፀም፡ "በቋሚ ቀውስ ፖለቲካ" ስትራቴጂነት እየተሠራበት ነው።
694 views15:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-08 22:26:23
849 views19:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 11:13:49 የሀዘን እና ለቅሶ አይነቶችን በመለዋወጥ የምታገኘው እረፍት የለም

ለበርካታ አሠርት አመታት የማያባራ ለቀሶ ውስጥ መገኘት ነውርና አስቀያሚ የትውልድ ውድቀት ነው።

ስርዓታዊ ጥቃት መፍትሔው ስርዓቲዊ ለውጥ ነው።
መንግስት ለመሆን እና ስልጣን ለመቆጣጠር መታገል ነው የሚያድንህ !
አለበለዚያ ነገም ጉዳይ ቀይረህ ለቅሶ ትወጣለህ!

በደም የጨቀየውን አዲሱንና መጪውን የፖለቲካ ኃይል አሰላለፍ የተረዳ ትግል ያስፈልጋል።

በአንድነት ፣ በወንድማማችነትና እህትማማችነት ፣ በመናበብ፣ በመከባበር ፣ በመተሳሰብና በመደማመጥ መታገል ነው እረፍት የሚሠጥህ !!

የለቅሶ ዘርፍ ስትቀያይር ትኖራለህ እንጂ፡ ጠላት ላይምርህ ከተማማለ ሠንብቷል !!
383 views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-07 09:17:24 ⁽⁽ሁሉም የኢትዮጵያ መሪዎች የየራሳቸውን ፓትርያርክ ሲሾሙ ስለነበር፡ እኔም የራሴን እሾማለሁ ነው የቀውሱ መነሻ። ሕዝቡን በራሴ ፓትርያሪክ በኩል እቆጣጠረዋለሁ፡ ቤተክርስቲያኗን እበርዛለሁ የሚል አላማ ነው።

ደርግ ገድሎ ፣ ወያኔ ከአገር አሰድዶ የየራሳቸውን ፓትርያሪክ ሾመዋል። የአሁኖቹ ደግሞ ለማሰደድም ለማስነወርም የቻሉትን ሁሉ ካደረጉ በኋላ ሳይሳካ ሲቀር፡ 'የብሔረሰቦች ሲኖዶስ' ብለው ዱርዬዎችን አሠማርተው እየደገፉ ነው።

በሁሉም የአገሪቱ ቋንቋዎች የምታሥተምረውን ቤተክርስቲያን በኦሮምኛ ለማገልገል የሚለው ሽፋን ነው። ስለኦሮምኛ ቋንቋ እያወሩ ስለብሔርሰብ ሲኖዶስ መቋቋም የሚያወሩህ እምነት ሳይሆን ፖለቲካ ስለሆነ ነው። ፓትርያርክ ሆኛለሁ የሚለው አቶ አካለወልድም ቢሆን የኦሮምኛ አገልግሎት አይችልም። በቋንቋው እያገለገሉ ያሉት እነአቡነ ናትናኤል ናቸው። እነሱ ሕገወጥነቱን እና ቤተክርስቲያንን የማፍረስ አላማን እያወገዙ ነው።

ከዚህ ቀደም በመሪዎች ጫና የቤተክርስቲያን ፓትርያርክ እና መሪዎች ሲለወጡ ከነበር እንኳ: ከእንግዲህ ተቋሟ ነፃነቷን የማስጠበቅ ግዴታ አለባት። የክርስቶስ አገልጋይ እንጂ የፌደሬሽን ምክርቤትም አይደለቸም።⁾⁾
468 views06:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-02 17:39:56
የእስቴ ፈረሰኞች
889 views14:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ