Get Mystery Box with random crypto!

አንሙት አብርሃም

የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የሰርጥ አድራሻ: @animutabraham
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.51K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-02-21 09:08:22
409 views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-21 09:08:11 ወረዳዎቹን አስረክቦ ቁጭ ያለው የቤኒሻንጉል ክልል ፤

የማኦኮሞ ልዩ ወረዳ እና ያሶ ወረዳዎችን "የኦሮሚያ ኃይል" ጠቅልሏቸዋል። ይሔንን ያወቀው የቤኒሻንጉል አመራር ቀደም ብሎ እንዲፈርስ ለተደረገው የማንነትና ወሰን ኮሚሽን ቢያሳውቅም መፍትሔ አላገኘም።

ቤኒሻንጉል ጉሙዝን ከጋምቤላ የሚያዋስነው የማኦኮሞ ወረዳ አሁን ሙሉ ለሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ጥቅለላና ወረራ ተፈፅሞበታል።
ከዚህ ቀደም በነበረው የአገሪቱ ካርታ ኦሮሚያ ክልል ከሱዳን የሚዋሰንበት አካባቢ አልነበረም። የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መግለጫም " ክልሉን በደቡብ የጋምቤላ ክልል ያዋስነዋል" ይል ነበር። አሁን ግን በሁሉም የካርታ መረጃዎች ላይ ኦሮሚያ ከሱዳን በስፋት እንዲዋሰን ሆኗል። [ see Maps ]

ይህን ለማድረግ መጀመሪያ በአካባቢው ታጣቂ በማስረግ ጥቃት መፈፀም ቀጥሎም የተጠቁ ሰዎች ሲሸሹ በስራና መሰል ጉዳይ ሰዎች ማስገባት የአፈፃፀም ቅደም ተከተል ነው።
በማኦ ኮሞ ወረዳ በእርሻና በእጣን ለቀማ ላይ በነበሩ ሠራተኞች ላይ የተፈፀመው ጥቃትና አፍኖ መሠወር ተግባር የሚታወቅ ነው። አሁን ደግሞ ብልጫ ቁጥጥር በተያዘበት አካባቢ የኦሮሚኛ ቋንቋ ትምህርት እንዲሰጥ እየሆነ ነው።

መተከል ውስጥ አባይን ተሻግሮ ያለው ወምበርማ ወረዳ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ያሶ ወረዳ እንጅ ከኦሮሚያ ጋር ድንበር አልነበረውም::
በካርታው ላይ በቀስት የተመለከተው የያሶ ወረዳ ክፍል ከተጠቀለለ በኋላ ግን የኦሮሚያ ድንበር አባይ ድረስ ሆኗል።
በወቅቱ ሁኔታውን የፃፈው Getahun kassahun እንዲህ ብሎ ነበር።
" The Oromia Region has annexed parts of the Benshagnul-Gumuz (BG) areas adjacent to the Abay River by stealth and are now administered by so-called Oromia region. In the process, Oromia Police forcefully displaced Gumuz residents from their places. For example, I have confirmed about 730+ Gumuz people were forced to flee to the low-laying areas of Womberma Woreda of Gojjam (metekel) across Abay River. "

በነገራችን ላይ፤

ከአሶሳ ወደ ነቀምት አድርጎ አዲስአበባ መምጣት ከተዘጋ አራት አመቱ ነው!!

Beles Media

#የታሪክ_ምርኮኞች
#Oromo
#FascistRegime
#Ethiopia
414 views06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-20 19:46:31 የአማራ ክልል መንግስት መግለጫ!!!
**************

በትላንት የታሪክ ምርኮኞችና በነገው ተስፋችን ቁማርተኞች ሕልውናዋን የማታጣ ሃገር መገንባት ከሁላችንም የሚጠበቅ ሃላፊነት ነው!!
--
በምድራችን ካላፉት የሥርዓተ መንግሥታት ታሪክ ውስጥ በራሳቸው ሕዝብ መካከል ተቃርኖን እየሸመኑ አንዱን የማኅበረሰብ ክፍል ከሳሽ፤ ሌላኛውን ደግሞ ተከሳሽ የሚያደርግ ጥልፍ በመጎንጎን የሀገረ መንግሥትነት ሕልውናቸውን ያጸኑም ሆነ ዘላቂ ሰላምና እድገታቸውን ያረጋገጡ መንግሥታት ተብለው ለአብነት ያህል እንኳ ስማቸው የሚጠቀስ ነገሥታትም ሆኑ መንግሥታት የሉም።

እንዳለመታደል ሆኖ ከታሪክም ሆነ ከአሁናዊ ነባራዊ ሁኔታዎች ላይ ተመስርቶ የአንድ ሀገር ሕዝብን በአንድነት እና እኩልነት ላይ በተመሰረተ ዴሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ሕዝብና ሀገራቸውን ለመለወጥ ከመታተር ይልቅ፤ በየሚዲያው የጥላቻ ተረክን እየነዙ ፖለቲከኞች በፖለቲካ ገበያው ውስጥ ናኝተው ይታያሉ፡፡

መታወቅ ያለበት ሃቅ የትላንት መጥፎ ታሪክ ጠበቃዎች አይደለንም። ልንሆንም አንችልም። ሁኖም ግን ታሪክ ትምህርት ቤት መሆኑን እናምናለን። የትላንት ታሪካችንም ቢሆን መጥፎ ብቻ አይደለም። መጥፎ ታሪክ ካለም ለመጥፎ ታሪኩ ጠበቃ የመሆን ፍላጎት የለንም። ይልቁንም የትናንትናውን መጥፎ ታሪክ ላለመድገም እንጥራለን አብዛኛውን በጎውን የጋራ ታሪካችንን ደግሞ አሻሽለን ትውልድን ለመጥቀም እንተጋለን። ነገር ግን የትላንት የታሪክ ምርኮኞች ሆነን ህዝባችንን ለፓለቲካ በሽታ የማጋለጥ ፍላጎቱም ትልሙም የለንም። አላማችንም አይደለም።

ይሁን እንጅ አሁን አሁን የትላንት ታሪክ ምርኮኛ ፖለቲከኞች ታሪክን እያዛቡ በማመንዠክ ዛሬያችንን ስለነገው ተስፋችን ከመሥራት ይልቅ ስለትላንቱ ተረከ-ታሪክ እሰጥ-አገባ መቆም የትውልዳችን ወትሯዊ ውሎ ሲሆን ይስተዋላል፡፡

የትላንት ታሪክ ምርኮኛዎች ትናንትን ከዛሬ በዉል ለይቶ ወደ ነገ መሻገር ሲሳናቸዉ በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ ቁሞ ቀር የፖለቲካ አስተሳሰብን ማመንዠክ ልዩ ክህሎትና መገለጫቸው እየሆነ መጥቷል፡፡

ጀንበር መሽቶ በጠባ ቁጥር ልብስና ወንበር እየቀየሩ በተቀናጀ እና በተናበበ መንገድ የሚረጩት መርዛማነቱ ከልብስና ወንበራቸው ጋር አብሮ ያልተቀየረ የከፋፋይነት እርካሽ ፖለቲካዊ ብያኔና ፍረጃ የሀገርና የሕዝብን ሰላም፣ አብሮነት እና ልማት ምን ያህል እያቀነጨረው እንደሆነ ሊገነዘቡት አልቻሉም ወይም አልፈለጉም፡፡

ይህን መሰሉ ፖለቲካዊ ግልሙትና በሕዝብ ትከሻ ላይ ተንጠልጥሎ ስሁት ትርክት እየነዙ ደም አፋሳሽ በሆነ መንገድ በሥልጣን ለመኖር ወይም ወደ ስልጣን ለመምጣት ቅጽበታዊ እድል ለማግኘት ካልጠቀመ በስተቀር ለሀገር አንድነትና ሕልውና ፋይዳ ቢስ ስለመሆኑ ከሥርዓተ መንግሥታትና ከነገሥታቱ ታሪክም ሆነ ከዘመናዊው የፖለቲካ ሳይንስ አስተምህሮት መማር ይቻላል፡፡

በዚህ ወቅት በሰፊ ሀገርና በታላቅ ሕዝብ ውስጥ እየኖሩ የጠበበ ግላዊና ቡድናዊ የጥቅም ፍላጎትን የሕዝብ አስመስሎ በማቅረብ፣ በጥላቻ ላይ ተመስርቶ ፤ ስሁት ትርክትን ተደግፎ ግጭት እየዘሩ፤ መከራን ኮትኩተው ሞት እያሳጨዱ ቡድናዊ ጥቅሜን አስቀጥላለሁ ብሎ ማመን ከትናንቱ ታሪክና ከነገው ተስፋ ጋር ተጻራሪ መሆንን ከማስረገጡ ባሻገር ዛሬን በሕይወት የመኖር ጸጋን ለመንፈግ የፖለቲካ ቁማር ቋሚ ሰልፈኝነትን ያስረዳል፡፡

ይህን መሰሉ አሰላለፍ የአፍታ ተዝናኖት ይሰጥ ካልሆነ በቀር የጀንበር ማብቂያ ያህል እድሜ ያለው ግላዊም ሆነ ቡድናዊ ሕልውነትን አይሰጥም፡፡ የሰላም፣ የልማትና የዴሞክራሲ ያደረ ጥያቄ እና ያልበረደ ፍላጎት ያለውን ሕዝብ እየመሩና ለመምራት እየሻቱ በተቃራኒው የሴራ ፖለቲካ እየሸመኑ፤ ዘረኝነትን እያቦኩ መኖር የሚቻልበት እድልም ጊዜም የለንም፡፡

ለዘመናት ተዋዶና ተዋህዶ በፍቅርና በአንድነት፣ በብሔርና በጎሳ ሳይከፋፈል፣ በቋንቋና ባህል ልዩነት ሳይለያይ፣ ብዙኅነቱን ተቀብሎ ለዘመናት ክብሩንና ታሪኩን ጠብቆ የኖረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ የትላንት ታሪክ ምርኮኞች የሚከውኗቸውን ኢትዮጵያውያንን በቋንቋ እና በዘር የሚከፋፍሉና ሕዝባችን ውስጥ ቅራኔና ጥላቻ የሚፈጥሩ ንግግሮችንና ተግባራትን እንደ አንድ ሕዝብ አምርሮ ሊቃወም፣ ሊታገልና ከውስጡ ሊያገላቸው ይገባል፡፡

ይህ ወቅት መላው ኢትዮጵያዊ አንደ አንድ ልብ ተባብሮ የታሪክ ምርኮኞችን መታገል የሚያስፈልግበት ወሳኝ ምዕራፍ እየሆነ መጥቷል። ሞቅ ቀዝቀዝ በሚል የትግል ሂደት ጠማማ የታሪክ ምርኮኞችና ቅን ልቦና የተሳናቸው የፖለቲካ ቆማሪዎች በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ላይ የጋረጡትን አደጋ ማስቀረት የሚቻለው ለእውነትና መርህ በመገዛት መታገል ሲቻል ነው።

ስለሆነም የእስካሁኑ የትግል ስልትና አካሄድ ብቻውን በቂ ባለመሆኑ ሁሉን አቀፍና አሳታፊ፣ ተጠያቂነት ያለው ህዝባችንን ያማከለ፣ በመልካም ዓላማ አገር ግንባታን ማዕከል ያደረገ፣ ወጥነት ያለው፣ የሀሳብና ዴሞክራሲያዊ ፍትሃዊ ትግል ማድረግ የሁላችንም የሁል ግዜ መደበኛ ሥራ ሊሆን ግድ ይላል።

በትላንት የታሪክ ምርኮኞችና በነገው ተስፋችን ቁማርተኞች ሕልውናዋን የማታጣ፤ በጠንካራ የሕዝብ አንድነትና እኩልነት ላይ የፀና ሃገረ መንግሥት ለማቆም መረባረብ ከሁላችንም የሚጠበቅ ሃላፊነት ነው፡፡

የምናልመው ለውጥና ስኬትም ሆነ የሕዝባችን መሰረታዊ ጥያቄዎች በምኞትና በፍላጎት ብቻ ሊፈቱ የሚችሉ አለመሆናቸው ታውቆ ሁሉም ዜጋ ችግሮቻችንን ውጫዊ በማድረግ የሆነን አካል ብቻ እንዲፈታ ከመጠበቅ ወጥቶ፤ የበኩሉን ድርሻ በማድረግና በመተጋገዝ ተደማምጦ በአንድነት ለለውጥና ስኬት በመታገል ተስፋና ለጋ ውጤቶቻችንን በማዝለቅ እንደ ሕዝብ ለገጠመን ፈተና ደግሞ የጋራ መፍትሔ እያበጁ መሄድ ይገባል። አማራጩም ይሄው ነው!!


Amhara communications office
532 views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-19 07:12:22 አዲዮስ ብልፅግና !!

ብልፅግና የሚባለው ማሕበር ፖለቲካሊ ከታዬ እርቃኑን ቆሟል!!

ጠበንጃን የተደገፈ አምባገነን ግለሰብ እና ⁽⁽ሠፊ ሆድ-ዕቃ⁾⁾ ያላቸው ፅንፈኞች ስብስብ ብቻ ነው።

➙ ሁሉም ክልሎች በአገዛዙ አልጠግብ ባይነትና ተስፋፊነት ተማረዋል። ያሰቃያቸው እንጂ የመራቸው ክልሎች አሉ ለማለት አይቻልም። ሊወራቸውና ሊውጣቸው መዘጋጀቱን አውቀው ካደሩ ሠንብተዋል። የሁሉም ክልል አመራር የሆዱን በሆዱ ይዞ ለይምሰል አንገታቸውን ነቅንቀው ብቻ ይወጣሉ።

➙ በዚህ አገዛዝ ያልተመረረ ብሔረሰብ የለም። ወላይታው፣ ሲልጤው፣ ጉራጌው፣ ትግሬው፣ አማራው፣ አፋሩ፣ ወዘተ በዚህ አገዛዝ ጭካኔ፣ ቸልተኛነት ፣ ተንኮል እና ጨፍጫፊነት ተማረዋል።

➙ የታችኛው መዋቅር እንደድርጅት ክዶታል። እግር አልባ ነው። አንድ ድርጅት አይደለም ብቻ ሳይሆን ተፍቶታል። በጠላትነትና ባላንጣነት እያየው ነው። ይታገለዋል እንጂ አይታገልለትም።

➙ የእምነት ተቋማት በጠላትነት የፈረጁት ሥርዓትና አገዛዝ ነው። ማታለል፣ ማጭበርበር፣ አውቅላችኋለሁ ባይነቱ ሁሉንም ኃይማኖቶች ቅራኔ ውስጥ ከቷል። ሁሉም የትግል ረመጥ ሆነዋል።

➙ ሲቪል ሠርቪሱ እያነባ ነው። በገንዘብ ሙስና የተጨማለቀው ስርዓት ሲቪል ሠርቪሱን ለርሃብና ጠኔ አጋልጦ ጥሎታል። መምህራን ፣ ሐኪሞች፣ ሌሎችም ሌሎችም ያበጠ ቅራኔ ተሸክመው እያጉረመረሙ ነው።

➙ ኑሮ የጠበሰው ሠፊው ሕዝብ ምሬት በሙስና ሆድ-ዕቃቸው በደነቆሩ ገዢዎች ሊደመጥ አልቻለም።

በዚህ ደረጃ ቅራኔ የሚንጠው አገርና ሥርዓት ተፈጥሮ አያውቅም።
በዚህ ሥርዓት ደረጃ የአገርን መፍረስ እና የብሔሮችን መጨፋጨፍ የስልጣን መደራደሪያ ያደረገ ስርዓት ኖሮ አያውቅም።

ብልፅግና የቀረው ነገር፡ በስልጣን ጥበቃ መባተት ነው!

የኢሠፓ ሊቀመንበር በአቢዮት ጠባቂ ሲያደርገው እንደነበረው፡ የብልፅግና ሊቀመንበርም በሪፐብሊካን ጋርድ ሲገድልና ሲያስር ሠንብቶ ወደመቃብር መጓዝ ነው።

አዲዮስ!
623 views04:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-18 11:04:12 ሠይጣንን ድል መንሻ ፤
በረከት ማግኛችን የፆም ወር መጣልን።

#እኔ_እፆማለሁ!
#እፀልያለሁ

አንተስ?|አንቺስ?
631 views08:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 21:11:06
ለእኔ ፤

የራስን ፓትርያሪክ የመሾም እና ተቋሟን ተቆጣጥሮ "ዲ-ኮንስትራክት" የማድረግ ዓላማ፡ በሌላኛው ስትራቴጂክ ስልቱ ያደረገው ሙከራ እንደገና ሳይሳካ ቀርቷል።

ያ ማለት ግን ፡ የጊዜ እና ስልት ለውጥ ለማድረግ የተላለፈ እንጂ የቀረ አላማ አይደለም

ምን አይነት ስልቶች ታሳቢ ይሆናሉ? የሚል የቢሆኖች ምልከታ የእስከዛሬውን የገዢ ቡድኑን ሒደቶችና ስልቶች ለሚያሰላስሉ አሳቢዎች ልተወው።

በዚሁ መሐል ግን ፤

➙ በሰላማዊ ተቋማት እና አገልጋዮች ላይ እንዲያፈነግጡ ተደርገው አመፅና ተቃውሞ በመምራት ለተከስተው የንፁሐን ግድያና መቁሰል ፍትሕ ተጠያቂው ማን ነው!?

➙ ቤተክርስቲያኗን ሊያፈርስ ለተነሳ ቡድን የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ በተቋሟ ሕልውና ላይ የተነሱ ባለሀብቶችና ግለሰቦች ተጠያቂነት የት ድረስ ነው!?

➙ የእምነት ተቋማት አመራር የሚሆኑ ሰዎች በአራት ኪሎ የፖለቲካ መሪዎች ፈቃድና ፍላጎት የሚዘወርበት ልማድ የሚሠበረው መቼ ነው!?

➙ ቤተእምነቷን የሚከዱና የፖለቲካ መጠቀሚያ የሚሆኑ ግለሰቦች፡ እንደገና ተመልሰው በተቋሟ ውስጥ ቁልፍ ስፍራ ይዘው እንዲቀጥሉ የሚደረግበት ልማድ አዋጪነቱ እስከየት ነው!?

➙ የቤተክርስቲያኗ እና የአመራሮቿ ዘላቂ "ደህንነት" ማረጋገጫ መንገዶች ምንድን ናቸው!?

➙ ለእምነቱ ቀናኢ ሆኖ የተነሳው ምዕመን ፅናትና ተቆርቋሪነት የት ድረስ ይፀናል!?

በመጨረሻ ግን ከሁነቱ ፤

ብዙዎች ከነበሩበት የመሪ ንግግር ተስፋና ድብታ ነፃ የወጡበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። UNCOVERED !

የኢ|ኦ|ተ|ቤ ልጆች በድንጋጤ ተነስተው ወደ እናት ቤታቸው ያማተሩበት አጋጣሚ ተፈጥሯል። ReActivated!

ብዙው ሥራና ትምህርት ለቤተክርስቲያኗ መሪዎች ነው!!

ስለሁሉም እግዚአብሔር ይመስገን
910 viewsedited  18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-15 09:44:38 https://m.tiktok.com/v/7199613754756107526.html?u_code=dkkkh70df13fh7&preview_pb=0&language=en&_d=dkkkh7h48hml7k&share_item_id=7199613754756107526&source=h5_m×tamp=1676443451&user_id=7010681088990512134&sec_user_id=MS4wLjABAAAAHz8I2i5HxZla0ohHX3SFaJHzaJMTjFx2Ikh_xKQzvFvNqcGyH1mrY0E3aMBLivLd&utm_source=more&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7019568815193966342&share_link_id=0c6d4c34-bbbc-489b-bbfd-504e6b03496c&share_app_id=1233
784 views06:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 22:38:55 ⁽⁽ቤተክርስቲያንን አጠቃህ⁾⁾ እንዳትባል ምን ታደርጋለህ ..!?
... ደግሞ አጋጣሚውን ተጠቅመህስ!?

[አንሙት አ.]
--
የወቅቱ፡ "አገር አፍርሶ-አገር ገንቢዎች" ፡ እንደብሒሉ "የኃይማኖት ተቋማትን በታማኞችህ ሳትቆጣጠር ስልጣን ትርጉም የለውም" ከሚል አተያይ በላይ፤ "የእምነት ተቋማትን አፍርሰህ-ሳትሠራ፡ አገር አፍርሰህ ሠራህ ማለት አይቻልም" የሚል እምነት እንደያዙ ነው የገባኝ።

"በወንጌላውያን ሕብረት" እና "በመጅሊሱ" የተሳካ ቁጥጥር ተፈፅሞ አፍርሶ-ግንባታው በመጀመሩ ብዙዎች ከእነ'ቅራኔያቸው እየተቆጩ አሉ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን መንፈሳዊ አመራሮች በመቀየር ተቋሟን ተቆጣጥሮ በራስ-አምሳል የመሥራት ተልዕኮን ለማሳካት ብልፅግና ስልጣን ከያዘበት ማግስት ጀምሮ የተለያዩ ስልቶች እንደተሞከሩ መረዳት ይቻላል።

3ኛ ሲኖዶስና 3ኛ ፓትርያርክ እንዳይኖር ለማድረግ፡ ከተወሰዱ፡ አባቶችን አስታርቆ የማሰባሰብ አካሔዶች፡ እስከ ተጨማሪ ሲኖዶስ ማቋቋም ብዙ ስም ማጥፋቶችና ክሶች አልፎም ከአገር-የማሰደድ ፍላጎቶች ተሞክረዋል።
አዲስ ሲኖዶስ መሥርቶ በእርቅ ሥልጣን ተጋርቶ የመቆየት እና በሒደት የመቆጣጠር አካሔዱ፡ በመንግስታዊ ጣልቃ-ገብነት እና ተቋማዊ ጥቃት ስለተወሰደ ፡ ታላቅ የሕዝብ ቁጣ ቀስቅሷል።

እናም አሁን፡ አዲስ፡ ግን ሲሠራበት የነበረ ስልት፡ ወደሥራ እየገባ ይመስላል፤

ይሔውም ⁽⁽የኃይማኖት ጣልቃገብነት⁾⁾ ቅራኔውን፡ ወደ ⁽⁽መፈንቅለ መንግስት⁾⁾ ክስ በመቀየር፡ ⁽⁽የቤተ-እምነቷን ድምፅ እና አቅሞች⁾⁾ ለማዳከም የሚረዳ ስራ ተጀምሯል።

1) ከሽምግልናው በኋላም ስለእምነትና ተቋማቸው ሲቆረቆሩ የነበሩ ግለሰቦችና የተቋሟ አገልጋዮች እስራት እየተሠራ ነው።
በአዲስአበባም ለምናልባቱ ከቤተ-እምነቷ ጋር ሊቆሙ የሚችሉ እና "በአመፅ ሊሳተፉ ይችላሉ" ተብለው የሚጠረጠሩ ወጣቶች እየታሠሩ ነው።
ይሔ ምናልባት ፡ የቤተክርስቲያኒቱን የመብት ጥያቄዎች በኃይል በመጨፍለቅ ቁጥጥሩን ለማስፈፀም ሲሞከር እምቢ ባይ ወጣቶች እንዳይኖሩ ታስቦ ይሆናል።
እስከከዚያው፡ ደግሞ "ቤተክርስቲያኗን አጠቃህ" ሳይሆን "መፈንቅለ-መንግስት ያሰበን ተቆጣጠርክ" ያስብላል የሚል እምነት ተይዞ ይሆናል።

2) ከ5 አመት በፊት ጀምሮ የዲሞግራፊ አላማ ተይዞለት "ከአዲስአበባ ዙሪያ ሌሎች ተወላጆችን የማስወጣት/ማፅዳት" ሥራ ተጠናክሮ ቀጥሏል። አሁን ደግሞ ⁽⁽መፈንቅለ መንግስት ለመፈፀም፡ እና አመፅ ለማድረግ ታስቧል⁾⁾ የሚለው ክስ ምቹ ሰበብ ተደርጎ፡ (ምናልባትም የቤታቸውን መፍረስ የሚቃወሙ) በጅምላ እየታሠሩ ነው።
የአዲስአበባ ዙሪያ፡ "መንግስታቸው የሚነካባቸው ዜጎች" ብቻ መኖሪያ እንዲሆን የማድረግ ፕሮጀክቱ ቀጥሏል።

3) በኦሮሚያ ኢ-መደበኛ ታጣቂ ግድያ ሲዘጋ የቆየው የአባይ መውጫ የፌደራል መንገድ ፡ አሁን ደግሞ በመደበኛው የመንግስት መዋቅር ማለፍ ተከልክሏል። እየተቀባበሉ የሚያስተዳድሩት መንገድ ሆኗል።
ወደ አዲስአበባ ከሚያስገቡ 5/6 መስመሮች መንገደኛ የሚገደልባቸው እና "አመፀኛ የሚገባባቸው" ያሏቸው ከአማራ ክልል የሚነሱት ናቸው።
"ማስወጣት እንጂ ማስገባትን" የሚከለክለው ፕሮጀክት አላማ ሆኖ፡ "የአማራዎችን ወደመሐል አገር የመግባት ፍላጎት እና ስነልቦና መግታት" አይደለም ብሎ የሚያሳምነኝ አላገኘሁም።
"መፈንቅለ መንግስት እና አመፅ ሊፈፅምብኝ የተዘጋጀ አካል ስላለ ዘጋነው" የሚለውን ለዓመታት ሰማነው። በፊት "የወያኔ ተላላኪ ስለሚገባ" የሚለው ሽፋንም ለዛሬ ስለማይሠራ አረዳዴን አይለውጥም ።

የታጠቀው የኦሮሚያ ኢ-መደበኛ ቡድን የሚንቀሳቀስበት ምስራቅ ሸዋ ወይም ምዕራብ ሸዋ መስመሮች ግን አይዘጉም። የግል ጉዳይና ኑሮ የሚያመላልሳቸው ሲቪል አማራዎች ናቸው "የስልጣን ስጋት" የተደረጉት።

በእርግጥ የብልፅግና አመራር ፡ የአዲስአበባ ከተማን ፖሊስ 50ሺህ የማድረስ ሥራ እና በከተማዋ "100ሺህ ሕዝባዊ ሠራዊት" አደራጅቻለሁ ብሏል።

ይሔ ሁሉ ተደማምሮ፡ ⁽⁽ ብልፅግና ወለድ፡ መፈንቅለ-መንግስትን የመከላከያ ስልት⁾⁾ ሊባል ይቻል ይሆን!?

----
* ልዩ ነገራችን
➙ ከየትም መጥተን ስልጣን እንያዝ፣ የእኛ ነገር የመጀመሪያ እና የመጨረሻ አድርገን በማመን መድከማችን !

➙ አቢዮታዊት ኢትዮጵያ ፣ አዲስቷ ኢትዮጵያ ፣ የበለፀገች ኢትዮጵያ እያልን በዜሮ ድምር ፖለቲካ የምንታክት አጥፍቶ ጠፊዎች አልሆንም!?
823 views19:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 20:20:01 ተከታዮቹን ሚድያዎች Subscribe and share በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን ማግኘት ትችላላችሁ፤


A) YouTube media

1 - https://youtube.com/@user-jw5xw2pr3l

2- https://youtube.com/@AratKiloMedia

3- https://youtube.com/@ETHIO251MEDIA

4- https://youtube.com/@amaramediacentre

5- https://youtube.com/@thevoiceofamhara2536

6- https://www.youtube.com/@ethiodaily8912/videos

7- https://youtube.com/@ethionikat


ለ) የቴሌግራም ገፆች

1- https://t.me/Mulugetaanberberr

2- https://t.me/ethio251media

3- https://t.me/thevoiceofamharamain

4- https://t.me/AnimutAbraham

5- https://t.me/Horn_African_News

6- https://t.me/GetachewShiferaw
556 viewsedited  17:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-02-14 20:17:06 https://www.bbc.com/amharic/articles/c3g49we102qo
518 views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ