Get Mystery Box with random crypto!

አንሙት አብርሃም

የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የቴሌግራም ቻናል አርማ animutabraham — አንሙት አብርሃም
የሰርጥ አድራሻ: @animutabraham
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.51K

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-10 20:46:39 https://www.counterpunch.org/2023/03/10/ethiopia-the-agony-of-tribal-nationalism/
562 views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 23:39:16
734 views20:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 23:39:12 በነገራችን ላይ ኦነጋውያኑን ማመስገን ይገባል!!

በየቀኑ አምርሮ የሚታገላቸውን ኃይል እየፈጠሩ፣ ሁሉንም በሕልውናው ላይ ቀጥተኛ እና ምህረት የለሽ አደጋ በመጣል ቆርጦ የሚታገል ኃይል እያደራጁልን በመሆኑ ከዚህ ወዲያ በሁለት ልብ የሚያላዝን የለም።

እንኳን በቡድኖች እና ሕብረተሰብ ሕልውና ላይ የአገር ሕልውናን አስይዞ ለመሞት የተማማለ ስብስብ በመሆኑ የኃይል ሚዛኑን አስተካክሎልናል።
ያልደረሰህ ካለህ፡ ስለማይቀርልህ እስኪመጡ በመጠበቅ አትድንም

ይብላኝነት ለጀነራል አበባው እና የጥሩነህ ልጆች እንጂ ሕዝቤስ ጨርሷል።

አሹሹ በልልኝ !!
700 views20:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 09:38:12 በሙሉ ጊዜው፡ በሩቅ አላማው ፡ ያለውን ሁሉ አሰልፎ ሊያጠፋህ እየሠራ፣
ሲያዋርድህ እየዋለ፤ ......
በትርፍ ጊዜህ እና ሲያደርስህ መቆጣት፤
እንዲያውም ጥቃቱን መመከት የሌሎች ሰዎች ሥራ በማድረግ፣
እነ'እገሌን የሚመለከት ጉዳይ አድርገህ ማየት የራስ መቃብር ቁፋሮ ይባላል

በትርፍ ጊዜ እና ሲያደርሰው የሚያጠቃህ ቢኖር እንኳ ፣ ሲያደርስህ ታግለህ አታስቆመውም

በምትችለው ሁሉ ደግፍ እና አደጋውን የሚመጥን አስተዋጽኦ አድርግ !!

አይዞህ ማለት ከእንቅፋት ያድናል !!

መልካም ቀን
991 views06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 20:05:08
823 views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 20:05:02 ዩኒቨርሲቲ የተመረቀችን የአማራ ወጣት ሴት ለቤት ሰራተኝነት ለመመልመል ማስታወቂያ ማውጣት ከጀርባው ምን ታስቦ ነው ?

ቀጣዩ ሀሳብ
" የ Ahmedin M Suleyman ነው

ሳዑዲ አረቢያ ባቀረበችው የገረድ (የቤት ሠራተኛ) አቅርቦት ጥያቄ መሠረት፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ የዐማራ ሴቶችን በገፍ ለማቅረብ የተጀመረው እንቅስቃሴ…

እንደ ባሪያ ንግድ ነው የማየው። ኢትዮጲያ ባሮችን ለአረቦች በማጋዝ ለማቅረብ ተስማማች።

በቅጡ ለአቅመ ሔዋን ያልደረሱ ልጃገረድ ሴቶችን

ግማሽ ሚሊዮን የኦሮሞ ሴቶች እንደማይሄዱ ይታወቃል። ግማሽ ሚሊዮን የትግሬ ሴትም አይሄድም። አገዛዙ በሽያጭ ለአረቦቹ የሚያቀርበው ግማሽ ሚሊዮን የዐማራ ሴቶችን ነው።

ጥናትና ቁጥር የተሠራበት ባይሆንም ሳዑዲ አረቢያ ከሄዱ በኋላ በርካቶቹ የአእምሮ በሽታ ታማሚ ይሆናሉ።

አብዛኞቹ ትዳር እንዳይዙ ተደርጎ ሕይወታቸው ይጨናገፋል። ግርድናው ትዳርንም እድሜያቸውንም ይሰርቃል። ያ ማለት አይወልዱም። ቢወልዱ እንኳ በሕጋዊ ትዳር የሚወልዱት ጥቂት ናቸው። በሌላ አባባል ዘር ማንዘር ተጨናገፈ፣ ሕይወት ተበላሸ ማለት ነው። ይሄ ለሴት ለቤተሰቦቿ ቅስም ሰባሪ ነው።

በዛ ሲሄዱ ክርስቲያኖች ከስማቸው ጀምሮ ማንነታቸውን በግድ እንዲቀይሩ ሆነው ነው የሚሄዱት። ሌላ የማንነት ማስክ እንዲያደርጉ ያደርጓቸዋል። እምነታቸውን ቀይረው እንዲሄዱ ነው የሚደረጉት። ማተብ ክራቸውን አስበጥሰው ነው የሚወስዷቸው።

ሙስሊሞችም እንደዛው። በዛ ከሄዱ በኋላ ሳይገባቸው ማንነታቸውን ነው የሚያጡት እናት አባቶቻቸውን ያሳደጋቸውን ማህበረሰብ አንጓጣጭ ነው የሚያደርጋቸው። የማንም ኡስታዝ መጫወቻ፣ ካዳሚና ጠብ ላይልላቸው የገንዘብ ምንጭ ሆነው ነው የሚቀሩት።

ብዙ አለ። ይሄ ሁሉ ሕዝብና አገር የሚያወድም ፕሮጀክት ነው። ሆን ተብሎ ተቀርጾ የተነደፈ ነው። ትናንት 500 ሺ ሕገ ወጥ ኢትዮጲያዊያንን አባረርኩኝ ያለች ሃገር በመነጋታው 500 ሺ ላኩልኝ ልትል አትችልም። ከበስተኋላው አደገኛ አጀንዳ አለው።

ትናንት ከሃገሯ የለበሱትን ልብስ ብቻ አስቀርታ ሃብት ንብረታቸውን፣ የሠሩበትን የላባቸውን እንጥፍጣፊ ጥሪት ወርሳ፣ በየ እሥር ቤቱ አንገላታና ገድላ የተረፉትን የዲቃላ ሕፃናት አስታቅፋ ሕይወታቸውን ከመነቃቀረች በኋላ በመቶ ሺዎች እህቶቻችንን ከዚህ ውስጥ 80% ዐማራ ያባረረች ሳዑዱ አረቢያ፣ ዛሬ ዞራ ተጨማሪ 500 ሺ ሴቶችን ለግርድና አቅርቡልኝ ልትል አትችልም።

ይሄ ከዘር ፍጅት ተለይቶ አይታይም። ይሄ ወላድ ዐማራ ሴቶችን ሆን ብሎ ለአረብ ግርድና በመሸጥ ዘር ማምከን የሕዝቡን ቁጥር መቀንጨር ነው። በሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር (በአብዛኛው ከ 12-15 እድሜ ውስጥ ያሉ ሴት ሕፃናቶች እና ከ 14-17 እድሜ ውስጥ ያሉ ወንድ ልጆች) የሚታመስ ክልል፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ሕፃናቶች በአገዛዙ ግፍ ወላጅ አልባ የሆኑበት ክልል፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች በአገዛዙ ግፍ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው በሚንገላቱበት ክልል፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ልጆቹ በአንድም በሌላም ምክኒያት ትምህርታቸውን እንዳይማሩ የሆኑበት ክልል አሁን ደግሞ ግማሽ ሚሊዮን ሕፃናት ሴቶችን ለባርነት አቅርብ እየተባለ ነው።

አሁን ወሎ፣ ሰሜን ሸዋና ጎጃም በዋናነት አገዛዙ ባዋቀራቸው የባሪያ መልማዮች እየታመሱ ነው።"
805 views17:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 23:08:50 የመዓዛ መሐመድ ሽልማት፡ እሷ በግሏ ላደረገቻቸው ጥረቶች እውቅና የሠጠ ብቻ አይደለም።

በሰሜኑ ጦርነት የአማራ ሴቶች ላይ የተፈፀሙ ፆታዊ ጥቃቶችን እንዲሁም በኦሮሚያ ደንቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ታግተው ደብዛቸው የጠፋ የአማራ ሴት ተማሪዎች ላይ የደረሱትን ጥቃቶች እውቅና የሰጠ ተደርጎ መታየት አለበት።
የአሳሪዎቿን ገመናም የገለጠ ነው።

የተፈፀሙ ግፎች አለምአቀፍ እውቅና ከተሰጣቸው በኋላ የተጠያቂነት እዳ የሚያስቀምጡ ናቸው።

መዓዛ የዚህ ምክንያት በመሆኗ እና ጥረቷ እውቅና በማግኘቱ እንኳን ደስ አለሽ እንላለን !!

ማስታወሻ፤
[ሌሎች ሙያተኞች እንዲሁም የአማራ የሙያ እና ሲቪክ ማሕበራት በየዘርፉ እየተፈፀሙ ያሉ ጥቃቶችን የተመለከቱ መረጃዎች ተደራሽ ለማድረግ ጥሩ ምሳሌ ሊያደርጉት ይገባል። ]
314 views20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 19:35:18 የኦሮሙማ ፕሮጀክትን በጨረፍታ!!

የቀደሙ የአገር ምሥረታ ሒደቶችን በተመለከተ የተፃፉ ፅሑፎችን ባሕሪዎች ለሚመረምር ሰው ፡ አሁን ስልጣን ላይ ያሉ ኦነጋውያን እያደረጉት ካለው ጋር ተገጣጥሞ ያገኘዋል።

ጥቂት ምሳሌዎች እናንሳ፤
1) ከሒደቶች መካከል የኔ ነው የምትለውን ግዛት መለየት እና መያዝ (Expansion of Territorial claim and possession) ዋነኛዎቹ ሒደቶች ናቸው። That is bringing territorial claims under centralized rule.
The Oromo elites claim territories across Ethiopia bordering Oromia ! በመላው ኢትዮጵያ ሁሉንም ክልል የሚያካልል የመሬትና ግዛት በመለየት የኔ ነው መያዝ አለብኝ ካለ ቆይቷል። የይገባኛል ካርታ ሠርቶ እየዞረ የኖረ ነው።

2) ⁽⁽የኔ ነው ያሉትን መሬት መያዝ⁾⁾ ግን በነፃ እና በሠላም ስለማይሆን ማስፈፀሚያ መንገድ አለው። ጠበንጃ ነው የአገር ግዛቶችን የመቆጣጠሪያ መሣሪያ !! በኃይል ነው የአገሮች ግዛቶች የተመሠረቱት።
"The means of destruction were guns !" ይለዋል። "War created states, states created wars !"
ኦነጋውያን ሕጋዊና መደበኛ (ልዩ ኃይል እና የመከላከያ ሠራዊት ቁጥጥር እድልን) እንዲሁም ኢ-መደበኛና ሕገ-ወጥ (የኦነግ ሸኔ ወዘተ) እንዲሁም ሕግና አሠራርን ቀላቅለው እያስፈፀሙት ነው።
[The oromos are using the legitimate and illegitimate forces to control territorial claims and to make destructions! ]

ስልጣን አንለቅም የምትባለው የስልጣን ጉዳይ ይሔንን ፕሮጀክት የማደናቀፍ ስጋት ስለሆነ ነው። ስለሆነም ምርጫ "አፍሪካ ውስጥ ነን አጭበርብረን እናሸንፋለን" ተብሏል፤ በግድያና አመፅ አታስቡት ተብለሃል ፣ "በመቶሺህዎች እንተላለቃለን" ትባላለህ ፤ "ከደርግ-ኢሕአፓ በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ምላሽ እንሠጣለን" የሚልህ ይሔንን ነው።
አሁን እየተፈፀመ ያለው ይሔ ነው።
ግዙፉ እና ድብቁ የኦሮሞ ልዩ ኃይል ስልጠና የሚጠብቀው ይሔንን ሒደት እና ክስተት ነው።
የእነ'ጃዋር እና መሰሎቻቸው ዝምታ ተገለፀልህ!? በዚህ ላይ ምንም ልዩነት የለምና ነው!!

3) አገራት በአቢዮት [Revolution] እና በዝግመት [Evolution] ተፈጥረዋል። ተሻለ ጥበቡ (የኢትዮጵያ ምሥረታ ሒደት ሁለቱንም ሒደቶች እንደሚዳስስ ያስረዳል።)
የOROMO State formation ግን ከመጀመሪያው ጀምሮ በአቢዮት የሚያምን ነው። በviolence and destruction በሚመራ አቢዮት ሊመሠረት የሚታሠብ የአገር ምስረታ ሒደት ነው።
ይሔንን ፕሮጀክት የሚገዳደሩ እና ሊያደናቅፉ የሚችሉት አማራ እና ትግራይ ሠፊ Destruction ተፈፅሞባቸዋል። ጦርነቱ የዚህ የኦነጋውያን ፕሮጀክት ልዩ እድል ነው። እዚያ ሔዶ የሞተ የኦሮሞ ወታደር ለትልቁ ብሔራዊ አላማ የከፈለው ዋጋ ነው።

4) National identity ከሚፈጠርባቸው ሒደቶች መካከል በstate formation ሒደተች ወቅት የሚፈፀም የዘር ማስወጣት/ ዘር ማፅዳት - ethnic cleansing ነው።
ከጌዲዮ እስከ ወለጋ ፣ ከካማሺ እስከ አጣዬ እየተሠራ ያለው ይሔ ነው።
ሒደቱን በኃይልና በፊት ለፊት እየተከላከለ ያለ የክልል መንግስት እና አካል ባለመኖሩ የኦነጋውያን ኢ-መደበኛ ኃይል በዋናነት የዘር ማፅዳቱን እያስፈፀመ ይገኛል።

Destruction ጉልበት እንጂ ሕግ አይፈልግም። ሕግ አይገዛውም
የማውደም አላማ ባለው የግዛት ምሥረታ ሒደቶች የሰዎች መፈናቀልና መጨፍጨፍ የሒደቶቹ አካል እንጂ የሰብዓዊነት መሥፈርት አይጠይቅም። ሒደቱ ሕገወጥነት ነው። ኃይል ነው ገዢው
ሕግ ሲደረመስ የሚውለው ለዚህ ነው። ጭፍጨፋና ማፈናቀል የሒደቱ አካል ነው

ለምሳሌ የተነሱትን እነዚህን ሒደቶች እና መሠል ጉዳዮች እያስፈፀሙ ካሉት ኦነጋውያን ጋር የትኛውም የማንነት ቡድን የpolitical contract ሊገባ አይችልም ነበር።
ግን በርካታ ክልሎች በCONVINCE and CONFUSE Strategy የተመቱ ናቸው።
ቢያፈነግጡም የተፈጠረውን ኮንትራት መሠረት አድርጎ ከስልጣን ይነቀላሉ!! ወይም እንደአብዲ ኢሌ ታንክ ይነዳባቸዋል

ጥቂት አማራዎችም በፖለቲካ እና ፀጥታው ዘርፍ ይህ አላማ "ሳይገባቸው" ወይም "ተወዛግበው" እያስፈፀሙ መሆናቸው ሊረሳ አይገባም።
በነገራችን ላይ ትግራይ ይሔንን ፕሮጀክት የጨረሰችው 1983 ነው።
ነገሩ የ19ኛው ክፍዘ አጀንዳ ቢመስልም እውነታው ይሔ ነው !!
--
[ምናልባት ዶር ተሻለ ጥበቡን እንኮርጅ ካልን ፤
የኦሮሚያን state formation በተመለከተ OLF has initiated and elaborated it. OPDO Consolidated and OPP is working to complete it. የዐቢይ አሕመድ ሕልም ይህ እንደነበር ማን ጠብቆ ይሆን? ]
282 viewsedited  16:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 08:44:59
445 views05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-06 08:44:54 ከልማት ድርጅቶች ላይ ይነሱ
እነዚህ የሕዝብ ጠላቶች ከተደበቁበት የሕዝብ ተቋማት ላይ ይነሱ
በፖለቲካ የሥልጣን ዘመናቸው የፈረደበትን ሕዝብ ተጫወቱበት፤ ጠላትን አጅበው አስበሉት።
ዛሬ ሲያጨማልቁት በኖሩት ግርግር ተሸፍነው በአማራ ሕዝብ ላብ የቆሙ ተቋማትን እያከሰሙ ይገኛሉ።
በፖለቲካው ጥለውን ሲያበቁ በቢዝነስ ያሳልፉላችኋል በሚለው ብዐዴናዊ እርግማን የተነሳ የሕዝባችን ጫንቃ ላይ ተኮፍሰዋል።
አንሷቸው

የእነዚህ ሰዎች ሥራ ለማመን ሁሉ ይቸግራል።
እነዚህ ሶስቱም ሰዎች ባለፈው ፍርድ ቤት ሲመላለሱ ነበር። የተከሳሽ ተከላካይ ምሥክር ሆነው።
ከሳሽ አንድ በግፍ የተባረረ አማራ ሠራተኛ ፣ ተከሳሽ ጥረት !!
እነዚህ ትልቅ የሚመስሉህ ቀትረ-ቀላል ቀጣፊዎች ግን ለአማራዎች የሥራ እድል ይፈጥራል ተብሎ በተቋቋመ ድርጅት አንድ ልጅ ከሥራ አባረው ልክ ነን ለማለት ፍርድ ቤት ሲመላለሱ ነበር።
እነዚህ ወለጋ ካሉ አራጆቻችን አይለዩም

Yilkal Kefale-ይልቃል ከፋለ እነዚህን በልማት ድርጅት መሪነት ስም የአማራን ደም እየመጠጡ የሚገኙ ጠላቶች ከኃላፊነታቸው የማንሳት ኃላፊነት አለብህ

እእያንደንዱ የልማት ድርጅት ውስጥ የመሸጉ መዥገሮች የሚሠሩትን እናውቃለን!!
የንጋት ቦርድ ሰብሳቢ ስዩም መኮንን እና ሌሎች አባላት ፤ የሕልውና ትግል ማለት የአንድን ሕዝብ ተቋማዊ ህልውና የማስቀጠል ትግልም ነው።
ተቋም እየፈረሰ ስለሕዝብ ሕልውና ማንሳት አይቻልም።
ዲግሪ እና ሽልማት በገንዘብ ሲገዛ የሚውለው የበአምላኩ አስተዳደር የአማራ የሕልውና ስጋት ነው !!
434 views05:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ