የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች:
15.48K
የሰርጥ መግለጫ
╭━─━─━─≪✠≫─━─━─━╮╭━─━─━─
ገና እንዘምራለን
የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ አስተምህሮና ስርዓትን የጠበቁ የመዝሙር ግጥሞችን ወረባቶችን ከነዜማቸው ለማግኘት @Zemaryan
╰━─━─━─≪✠≫─━─━─━╯╰━─━─━─
ለማንኛውም ሀሣብ, ጥቆማ, አስተያየት ጥያቄ> creator ለማግኝት @kidanemiherat_bot
@yita21
@Binyam
https://youtu.be/Fz4JARE6-DI
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5
2023-03-03 14:57:47
#የዜና_ጥቆማ
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቴሌቪዥን
ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን
ለኦሲኤን ቴሌቪዥን
ለአሐዱ ሬዲዮና ቴሌቪዥን
ለባላገሩ ቴሌቪዥን
ለናሁ ቴሌቪዥን
ለአሻም ቴሌቪዥን
ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን
ለሀገሬ ቴሌቪዥን
ለተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል
ለET ART ሚዲያ
ለንቁ ሚዲያ
ባላችሁበት
ጉዳዩ፡- የዜና ሽፋንን ይመለከታል
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር ተያይዞ በዛሬው ዕለት የካቲት 24 ቀን 2015 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መግለጫ የሚሰጥ በመሆኑ ከላይ የተጠቀሳችሁ ሚዲያዎች ብቻ በሰዓቱ ተገኝታችሁ መግለጫውን በመቅረጽና በመዘገብ የሚዲያ ሽፋን እንድትሰጡ የተጋበዛችሁ መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት
@zemaryan
485 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, edited 11:57
2023-03-03 11:26:42
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት እንኳን ለ፲ኛ ዓመት በዓለ ሢመትዎ በሰላም አደረስዎ!@zemaryan
1.6K views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, edited 08:26
2023-03-02 20:54:39
የኢትዮጵያ ገበዝ
የኢትዮጵያ ጠባቂ
የቅዱስ ጊዮርጊስ ታቦት ላይ መንግስት ተኩስ ከፍቷል! ምዕመኑ በዓሉን ማክበር ታቦቱን ማንገስ አልቻሉም።
ተዋግቶ ኢትዮጵያን ላስከበራት ለቅዱስ ጊዮርጊስ መሳርያ ይገባዋል???
@zemaryan
1.0K views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, edited 17:54
2023-03-01 11:35:09
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት መቐለ አሉላ ኣባነጋ ዓለም አቀፍ አየር ማረፍያ በሰላም ገብተዋል።
በአየር ማረፊያው ሲደርሱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት እና የቤተ ክህነት ሠራተኞች እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እና ምእመናን አቀባበል አድርገውላቸዋል።
539 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, 08:35
2023-02-26 21:37:26
በወለጋ ነቀምቴ ከተማ መንበረ ጵጵስናው በሚገኝበት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ውጥረት ተከስቷል።
የብፁዕ አቡነ ናትናኤል ሀገረ ስብከት በሆነው በነቀምቴ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስን ትእዛዝ በሚቀበሉ ኦርቶዶክሳውያን እና ሕገወጡን ተሿሚ እንቀበላለን በሚሉ ከሌላ አካባቢ በመኪና ለሁከት እንዲመጡ በተደረጉ ሰዎች መካከል ውጥረት መከሰቱ ተገልጿል።
ጉዳዩ የተከሰተው ነገ የሚታሰበውን ወርኃዊ የቅዱስ ገብርኤል በዓል ምክንያት በማድረግ ሕገወጥ ተሿሚ የሆነውና ደጋፊዎች ነን የሚሉ ወደ ገዳሙ እንገባለን በማለታቸው እና በሰንበት ተማሪዎች፣ ኦርቶዶዶክሳውያን ወጣቶችና የአካባቢው ምእመናን ቅዱስ ሲኖዶስ የተወገዘ አካል በገዳሙ አይገባም በማለታቸው ነው።
ውጥረቱን ለማርገብ የመከላከያ ሠራዊት የተገኘ ሲሆን የከተማው ከንቲባና የከተማው ፖሊስ አዛዥ ጉዳዩን ለመረዳት ከመሞከር ይልቅ ከብሔርና ፖለቲካ ጋር በማገናኘት መፍትሔ ሳይሰጡ በማባባስ ላይ እንደሚገኙ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በአሁኑ ሰዓት የአካባቢው ምእመናን፣ ወጣቶችና የሰንበት ት/ቤት ተማሪዎች በቅዱስ ገብርኤል ገዳም ቅጥር ግቢ ውስጥ በመሆን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እየጠበቁ ይገኛሉ።
ጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም በሕገ ወጥ መንገድ በወሊሶ የተሾሙ 25 "ኤጲስ ቆጶሳት" በቅዱስ ሲኖዶስ መወገዛቸው እንዲሁም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ ማገዱ ይታወሳል።
@zemaryan
@zemaryan
544 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, 18:37
2023-02-22 10:01:19
ከኃጢያታችን የበለጠ እግዚአብሔርን እጅግ የሚያሳዝነው
ይቅር አይለንም ብለን ማሰባችን ነው።
@zemaryan
647 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, edited 07:01
2023-02-19 23:16:46
1. ዘወረደ
የዐቢይ ጾም የመጀመሪያው ሰንበት ሲሆን ይህም ቅድመ ዓለም የነበረ ዓለምን ፈጥሮ የሚኖር አልፋና ኦሜጋ ከሰማየ ሰማያት መውረዱንና ከእመቤታችን ከቅድስተ ቅዱሳን ከንጽሕተ ንጹሐን ከድንግል ማርያም መወለዱን የሚያመለክት ሥያሜ ነው፡፡
@zemaryan
@zemaryan
183 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, 20:16
2023-02-18 21:58:04
24,300 ዶላር ደርሷል።
በመላው ዓለም የምትገኙ ቅድሚያ ለጋሾች እናተው ናችሁ!!
አገር ቤት ያለነው መልዕክቱን በማጋራት የተግባር ሰው እንኹን!
ብዙዎች በበጎ ይነሱ ዘንድ ስክሪን ሻት ላኩልን እናጋራለን!!
https://www.gofundme.com/f/eotc-charity-fundraiser-united-we-stand?utm_campaign=p_cf+share-flow-1&utm_content=undefined&utm_medium=copy_link&utm_source=customer&utm_term=undefined
380 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, 18:58
2023-02-17 22:35:08
† [ ሰበር መረጃ ! ]
ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት የተሰጠ መግለጫ በከፊል !
@zemaryan
@zemaryan
† † †▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
1.1K views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, edited 19:35
2023-02-16 09:11:45
ለ ሕጋዊ የሚድያ ተቋማት በሙሉ፤የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለዘመናት ያካበተቻቸውን መንፈሳዊ፣ ቁሳዊ፣ ታሪካዊ እና ኪናዊ ሀብቶቿን በተለያዩ የብዙኅን መገናኛ ተቋማት የሚዲያ ሽፋን በመስጠት ጉልህ አስተዋጽኦ ስታበረክቱ መቆየታችሁ ይታወቃል።
ስለሆነም ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ከብዙኅን መገናኛ ድርጅቶች ጋር ተቀራርባ የምትሠራባቸው የተሻለ አሠራር መዘርጋት ትችል ዘንድ የብዙኋን መገናኛ ድርጅቶች በቤተ ክርስቲያኒቱ እውቅና ተሰጥቷቸውና ሕግና ሥርዓትን በጠበቀ መልኩ ከቤተ ክርስቲያናችን የሚወጡ መረጃዎችን በኃላፊነት እና መርሕን ባከበረ መንገድ፤ ለተዛባ ትርጉም ሳይጋለጡ እንዲዘገቡ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት በማስፈለጉ ኃላፊነት የሚሰማቸው ሚዲያዎች መረጃዎችን በትክክል እንዲያደርሱ የግንኙነት መዋቅር መዘርጋት ይቻል ዘንድ የምክክር መድረክ ለማዘጋጀት በዝግጅት ላይ ትገኛለች።
ስለሆነም ይህ ማሳሰቢያ ከወጣበት ጊዜ አንስቶ ተቀማጭነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የግል እና የመንግሥት ብዙኅን መገናኛ ተቋማት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ጥሪ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ አግኝተነዋል።
በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የዐውደ ምሕረት እና የአደባባይ በዓላትን ለመዘገብ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በየጊዜው የምትሰጣቸውን መግለጫዋች የሚዲያ ሽፋን ለመስጠት፤ በየአብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ቅርሶችን፣ ወቅታዊ ሁኔታዎችን እና በርካታ ሀብቶችን መሠረት ያደረገ የሚዲያ ሽፋን በመስጠትና ልዩ ልዩ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ለመሥራት ወዘተ... የሚፈልግ ማንኛውም የመንግሥትም ይኹን የግል ሚዲያዎች ከዛሬ የካቲት 9ቀን 2015 ዓ.ም እስከ የካቲት 15 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ብቻ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ በመገኘትና የተዘጋጀውን ቅጽ በመሙላት ምዝገባ እንድታካሂዱ እያሳሰብን አዲስ የሚመሠረት የሚዲያ ተቋምና ተቀማጭነታቸው አዲስ አበባ ካልሆኑት በስተቀር ማንኛውም የሚዲያ ተቋም በእነዚህ ቀናት ተገኝቶ ምዝገባ በማከናወን ቤተ ክርስቲያናችን በምታዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ካልተካፈለ በምንም አይነት መንገድ ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚዲያ አገልግሎት ጥያቄ ቢያቀርብ የማይስተናገድ መኾኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክጠቅላይ ቤተ ክህነት የህዝብ
ግንኙነት መምሪያ
የካቲት 9 ቀን 2015
@zemaryan
441 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, edited 06:11