2023-02-08 07:38:38
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አሁንም በብፁአን አባቶች እና ምእመናን ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይና እንግልት መቀጠሉን ገለፀች።
ቤተክርስቲያኗ ከቀናት በፊት በሻሸመኔ ከተማ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተፈፀመው ጥቃት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ከፍ ማለቱን ገልጻለች።
ቤተክርስቲያኗ የሻሸመኔ ደብረ ስብሐት ቅዱስ ሚካኤል አገልጋይ የነበሩት ቀሲስ ሐረገወይን ከመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በተተኮሰ ጥይት ተመትተው በሕክምና ሲረዱ ቢቆዩም ህይወታቸው ሊተርፍ እንዳልቻለ አሳውቃለች።
በተጨማሪ ቤተክርስቲያኗ ፤ በፓሊሶች ፊት በአጣና ጭንቅላቱን ተቀጥቅጦ በሀዋሳ በፅኑ ህሙማን ክፍል ሕክምና ሲደረግለት የነበረ አያሌው ተረፈ የተባለ ምዕመን በደረሰበት ጉዳት ህይወቱን ማትረፍ ሳይቻል ቀርቶ ማረፉን ገልጻለች።
በጽኑ ሕሙማን ክፍል ሌሎችም ተጎጂዎች እንደሚገኙ የገለፀችው ቤተክርስቲያን የጤናቸው ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑን አስረድታለች።
ከሰሞኑ ሁኔታ ጋር በተያያዘ በሻሸመኔ ከተማ እስካሁን አጠቃላይ ህይወታቸው ያለፈ ሰዎችን ቁጥር ቤተክርስቲያኗ ይፋ አላደረገችም።
ከዚህ ባለፈ ቤተክርስቲያኗ ፤ በሻሸመኔና አርሲ ነገሌ በሌሎችም ስፍራዎች የቤተክርስቲያን አባቶች፣ ምዕመናን ሰብአዊ ክብራቸው ተጥሶ ዛሬም በየእስር ቤቱ እንደሚገኙ አሁንም እየታሰሩ የሚገኙ መኖራቸውን አሳውቃለች።
መንግስታዊዎቹ የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋምና የሰብአዊ መብት ኮሚሽን ዝምታን መምረጣቸው እጅግ እንዳሳዘናት ቤተክርስቲያኗ ገልጻለች።
በሌላ በኩል ቤተክርስቲያኗ ፤ ወደ ከፋ ሸካና ቤንች ማጂ ሀገረ ስብከታቸው የተጓዙት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል የኦሮሚያ ክልል የጸጥታ ኃይሎች ክልሉን አቋርጠው ወደ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እንዳይሄዱ በማገዳቸው ወደ አዲስ አበባ እንደተመለሱ ገልጻለች።
@zemaryan
918 views ყเƭαყαℓ የ҈ ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ ል⃝ጅ Cinematographer }, 04:38