Get Mystery Box with random crypto!

Tiriyachen | ጥሪያችን

የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tiriyachen — Tiriyachen | ጥሪያችን
የሰርጥ አድራሻ: @tiriyachen
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.91K

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2023-01-05 17:49:47
297 views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 20:44:48 ንጉሡ ዳዊት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

4፥172 አልመሢሕ ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ

መሢሑ ከዳዊት ዘር የሚመጣ ነቢይ ስለሆነ "ዳዊት" ተብሏል፥ "ደውድ" דָּוִד ማለት "የተደደ" ማለት ነው፦
ሕዝቅኤል 37፥24 ባሪያዬም ዳዊት ንጉሥ ይሆናቸዋል፥ ለሁሉም አንድ እረኛ ይሆንላቸዋል። በፍርዴም ይሄዳሉ፥ ትእዛዜንም ይጠብቃሉ ያደርጓትማል። וְעַבְדִּ֤י דָוִד֙ מֶ֣לֶךְ עֲלֵיהֶ֔ם וְרֹועֶ֥ה אֶחָ֖ד יִהְיֶ֣ה לְכֻלָּ֑ם וּבְמִשְׁפָּטַ֣י יֵלֵ֔כוּ וְחֻקֹּתַ֥י יִשְׁמְר֖וּ וְעָשׂ֥וּ אֹותָֽם׃

መሢሑ ኢየሱስ ሲሆን ኢየሱስ ዳግም ሲመጣ ሰዎች በአምላክ ፍርድ ይሄዳሉ፣ ትእዛዙንም ይጠብቃሉ ያደርጉታል፥ ፈጣሪ የሚመጣውን መሢሕ፦ "ዐብዲ" עַבְדִּ֔י ማለትም "ባሪያዬ" ይለዋል። ይህ የፈጣሪ ባሪያ ንጉሥ፣ እረኛ፣ አለቃ ነው፦
ሕዝቅኤል 37፥25 ባሪያዬም ዳዊት ለዘላለም አለቃ ይሆናቸዋል። וְדָוִ֣ד עַבְדִּ֔י נָשִׂ֥יא לָהֶ֖ם לְעֹולָֽם׃

እዚህ አንቀጽ ላይ "ዘላለም" ለሚለው የገባው ቃል "ዖላም" עוֹלָ֗ם ሲሆን አላፊ ወይም መጻኢ ውስን ጊዜን ለማመልከት ይውላል፥ ለምሳሌ፦ እዚህ ጥቅስ ላይ መጻኢ ውስን ጊዜን ለማመልከት መጥቷል፦
ዘጸአት 21፥6 ወደ ደጁም ወደ መቃኑ አቅርቦ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ “ለዘላለምም” ባሪያው ይሁን። וְהִגִּישֹׁ֤ו אֲדֹנָיו֙ אֶל־הָ֣אֱלֹהִ֔ים וְהִגִּישֹׁו֙ אֶל־הַדֶּ֔לֶת אֹ֖ו אֶל־הַמְּזוּזָ֑ה וְרָצַ֨ע אֲדֹנָ֤יו אֶת־אָזְנֹו֙ בַּמַּרְצֵ֔עַ וַעֲבָדֹ֖ו לְעֹלָֽם׃ ס

ስለዚህ "ለዘላለም አለቃ ይሆናቸዋል" ሲባል መጻኢ ውስን ጊዜን ለማመልከት ነው። የሚያጅበው ነገር አንዱ አምላክ ያህዌህ እና ንጉሥ፣ እረኛ፣ አለቃ የተባለው መሢሑ "ወ" וְ ማለትም "እና" በሚል መስተጻምር ተለይተዋል፦
ሆሴዕ 3፥5 ከዚያም በኋላ የእስራኤል ልጆች ተመልሰው አምላካቸውን ያህዌህን እና ንጉሣቸውን ዳዊትን ይፈልጋሉ። אַחַ֗ר יָשֻׁ֙בוּ֙ בְּנֵ֣י יִשְׂרָאֵ֔ל וּבִקְשׁוּ֙ אֶת־יְהוָ֣ה אֱלֹהֵיהֶ֔ם וְאֵ֖ת דָּוִ֣ד מַלְכָּ֑ם
ኤርሚያስ 30፥9 ለአምላካቸው ለያህዌህ እና ለማስነሣላቸው ለንጉሣቸው ለዳዊትም ይገዛሉ። וְעָ֣בְד֔וּ אֵ֖ת יְהוָ֣ה אֱלֹֽהֵיהֶ֑ם וְאֵת֙ דָּוִ֣ד מַלְכָּ֔ם אֲשֶׁ֥ר אָקִ֖ים לָהֶֽם׃ ס

እዚህ አንቀጽ ላይ "ይገዛሉ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ዓቤዱ" עָ֣בְד֔וּ ሲሆን ቅሉ ግን ሚሽነሪዎች በአንድ ቃለ ማሠሪያ አንቀጽ ላይ ያለውን ይህንን ግሥ "ያመልካሉ" በማለት ይረዱታል፥ ይህ ያረጀ እና ያፈጀ፤ የተመታ እና የተምታታ መደዴ ሙግት ነው። ምክንያቱም ከአምላክ ጋር "እና" በሚል መስተጻምር በአንድ ግሥ ተጫፍሮ እና ተዛርፎ የተቀመጠ ፍጡር በፍጹም ፈጣሪ ስላልሆነ አይመለክም፦
2ኛ ዜና 35፥3 አሁንም አምላካችሁን ያህዌህን እና ሕዝቡን እስራኤልን አገልግሉ። עִבְדוּ֙ אֶת־יְהוָ֣ה אֱלֹֽהֵיכֶ֔ם וְאֵ֖ת עַמֹּ֥ו יִשְׂרָאֵֽל׃

“ዒብዱ” עִבְדוּ֙ ማለት “አገልግሉ” “ተገዙ” “አምልኩ” ማለት ነው፥ እና የእስራኤል ሕዝብ ከያህዌህ ጋር ይመለካል ማለት ነውን? “አይ የእስራኤል ሕዝብ ይገለገላል የተባለው ያህዌህ በሚገለገልበት ሒሣብ አይደለም” ካላችሁ እንግዲያውስ "ለአምላካቸው ለያህዌህ እና ለማስነሣላቸው ለንጉሣቸው ለዳዊትም ይገዛሉ" ማለትን በዚህ ስሌት ተረዱት! ንጉሡ ዳዊት ከአምላክ ጋር "እና" በሚል መስተጻምር በአንድ ግሥ ተጫፍሮ እና ተዛርፎ ተሰግዶለታል፦
1ኛ ዜና 29፥20 ራሳቸውንም አዘንብለው ለያህዌህ እና ለንጉሡ ሰገዱ። וַיִּקְּד֧וּ וַיִּֽשְׁתַּחֲו֛וּ לַיהוָ֖ה וְלַמֶּֽלֶךְ׃

እዚህ ዐውድ ላይ "ንጉሡ" የተባለውን ንጉሡ ዳዊት እንደሆነ እሙን እና ቅቡል ነው፥ ለያህዌህ እና ለዳዊት "ሰገዱ" ተብሎ የገባው የግሥ መደብ "ዪስታሃዉ" יִּֽשְׁתַּחֲו֛וּ ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "ሻኻህ" שָׁחָה ነው። እና ዳዊት ከያህዌህ ጋር ይመለካል ማለት ነውን? እንቀጥል፦
መሣፍንት 7፥18 እኔ ከእኔም ጋር ያሉት ሁሉ ቀንደ መለከት ስንነፋ፥ እናንተ ደግሞ በሰፈሩ ዙሪያ ሁሉ ቀንደ መለከታችሁን ንፉ፦ "ለያህዌህ እና ለጌዴዎን" በሉ፡ አላቸው። וְתָקַעְתִּי֙ בַּשֹּׁופָ֔ר אָנֹכִ֖י וְכָל־אֲשֶׁ֣ר אִתִּ֑י וּתְקַעְתֶּ֨ם בַּשֹּׁופָרֹ֜ות גַּם־אַתֶּ֗ם סְבִיבֹות֙ כָּל־הַֽמַּחֲנֶ֔ה וַאֲמַרְתֶּ֖ם לַיהוָ֥ה וּלְגִדְעֹֽון׃ פ

እዚህ አንቀጽ ላይ ጌዴዎን "እና" በሚል መስተጻምር ከያህዌህ ጋር ስለተጫፈ እና ስለተዛረፈ እኩል ክብር እና ሥልጣን አላቸውን? እንቀጥል፦
ምሳሌ 24፥21 ልጄ ሆይ! ያህዌህን እና ንጉሥን ፍራ። יְרָֽא אֶת־ יְהוָ֣ה בְּנִ֣י וָמֶ֑לֶךְ

እዚህ ዐውድ ላይ "ንጉሥ" የተባለው በፍርድ ወንበር የሚቀመጥ ማንኛውም ንጉሥ ያመለክታል፥ ምሳሌ 20፥8 ተመልከት! ያህዌህ እና ንጉሥን "ፍሩ" ተብሎ የገባው የግሥ መደብ "ዩራ" יְרָֽא־ ሲሆን ሥርወ-ቃሉ "ያረ" יָרֵא ነው። እና በፍርድ ወንበር የሚቀመጥ ማንኛውም ንጉሥ ከያህዌህ ጋር ይመለካል ማለት ነውን?
ስለዚህ ከላይ ፈጣሪ "ባሪያዬ" የሚለው መሢሑ አይመለክም። ከዚያ በተቃራኒው ይህ መሢሕ ለአሏህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፦
4፥172 አልመሢሕ ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ لَّن يَسْتَنكِفَ الْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًا لِّلَّهِ

አምላካችን አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
ወሠላሙ ዐለይኩም
ጥሪያችን ሪሌግራም
https://t.me/tiriyachen
181 views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 20:44:02
165 views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 17:18:07 የመሢሑ አወጣጥ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ

አምላካችን አሏህ በአደም፣ በኑሕ፣ በኢብራሂም፣ በዒምራን ቤተሰብ ውስጥ መሢሑ እንዲመጣ አድርጓል፥ መርየም የዒምራን ልጅ ስትሆን መሢሑ ደግሞ ዘሯ ነው፦
3፥33 አላህ አደምን፣ ኑሕንም፣ የኢብራሂምንም ቤተሰብ፣ የዒምራንንም ቤተሰብ በዓለማት ላይ መረጠ፡፡ إِنَّ اللَّهَ اصْطَفَىٰ آدَمَ وَنُوحًا وَآلَ إِبْرَاهِيمَ وَآلَ عِمْرَانَ عَلَى الْعَالَمِينَ
3፥36 «እኔም እርስዋን እና ዝርያዋን ከተረገመው ሰይጣን በአንተ እጠብቃቸዋለሁ» وَإِنِّي أُعِيذُهَا بِكَ وَذُرِّيَّتَهَا مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ

"ዙሪያህ" ذُرِّيَّة ማለት "ዘር"offspring" ማለት ሲሆን "ዙሪያህ" ذُرِّيَّة በሚለው መድረሻ ቅጥያ ላይ "ሃ" هَا የሚለው አንስታይ አገናዛቢ ተውላጠ ስም መርየምን አመላካች ስለሆነ ዒሣ የመርየም ዘር መሆኑን ቁልጭ እና ፍንትው አርጎ ያሳያል። በተመሳሳይ ባይብል ላይ መሢሑ ከአብርሃም፣ ከይስሐቅ፣ ከያዕቆብ፣ ከይሁዳ፣ ከእሴይ ወዘተ ... እንደሚወጣ ተተንብይዋል፦
ሚክያስ 5፥2 አንቺም ቤተ ልሔም ኤፍራታ ሆይ፥ አንቺ በይሁዳ አእላፋት መካከል ትሆኚ ዘንድ ታናሽ ነሽ፤ ከአንቺ ግን አወጣጡ ከቀድሞ ጀምሮ ከዘላለም የሆነ፥ በእስራኤልም ላይ ገዥ የሚሆን ይወጣልኛል። וְאַתָּ֞ה בֵּֽית־לֶ֣חֶם אֶפְרָ֗תָה צָעִיר֙ לִֽהְיֹות֙ בְּאַלְפֵ֣י יְהוּדָ֔ה מִמְּךָ֙ לִ֣י יֵצֵ֔א לִֽהְיֹ֥ות מֹושֵׁ֖ל בְּיִשְׂרָאֵ֑ל וּמֹוצָאֹתָ֥יו מִקֶּ֖דֶם מִימֵ֥י עֹולָֽם

እዚህ አንቀጽ ላይ "ቀድሞ" ተብሎ የተቀመጠው ቃል "ቄዴም" קֶדֶם ሲሆን ይህ "ቀድሞ" የተባለው ጊዜ አብርሃም፣ ይስሐቅ፣ ያዕቆብ የነበሩበትን ጊዜ ነው፦
ሚክያስ 7፥20 ከ-"ቀድሞ" ዘመን ጀምረህ ለአባቶቻችን የማልህላቸውን እውነት ለያዕቆብ፥ ምሕረትንም ለአብርሃም ታደርጋለህ። תִּתֵּ֤ן אֱמֶת֙ לְיַֽעֲקֹ֔ב חֶ֖סֶד לְאַבְרָהָ֑ם אֲשֶׁר־נִשְׁבַּ֥עְתָּ לַאֲבֹתֵ֖ינוּ מִ֥ימֵי קֶֽדֶם

"ለአባቶቻችን የማልህላቸውን" የሚለው ይሰመርበት! ይህም መሃላ ከእነርሱ ዘር በሚወጣው መሢሕ እንደሚባረኩ ነው፥ ዘፍጥረት 22፥18 ዘፍጥረት 26፥4 ዘፍጥረት 28፥14 ተመልከት! "ቄዴም" קֶדֶם ሌላ ትርጉሙ "ምሥራቅ" ማለት ነው፦
ዘፍጥረት 10፥30 ስፍራቸውም ከማሴ አንሥቶ ወደ ስፋር ሲል እስከ "ምሥራቅ" ተራራ ድረስ ነው። וַֽיְהִ֥י מֹושָׁבָ֖ם מִמֵּשָׁ֑א בֹּאֲכָ֥ה סְפָ֖רָה הַ֥ר הַקֶּֽדֶם

እዚህ አንቀጽ ላይ "ምሥራቅ" ለሚለው የገባው ቃል "ቄዴም" קֶדֶם እንደሆነ ልብ አድርግ! ከ 306 እስከ 373 ድኅረ ልደት ይኖር የነበረ ሶሪያዊ ኤፍሬም ድንግል ማርያምን "ምሥራቅ" ኢየሱስን "ኮከብ" በማለት "አወጣጡ ከምሥራቅ ነው" የሚለውን ፈሥሯታል፦
ውዳሴ ማርያም ዘዐርብ ቁጥር 6 "አንቲ ውእቱ ምሥራቅ ዘወጽአ እምኔኪ ኮከብ"

ትርጉም፦ "ኮከብ ከአንቺ የወጣብሽ ምሥራቅ አንቺ ነሽ"

"ከዘላለም የሆነ" የሚለውን ደግሞ በቀጣይ የመጣ ነው፥ “ዘላለም” የሚለው የዕብራይስጡ ቃል “ዖላም” עוֹלָ֗ם ሲሆን አላፊ ወይም መጻኢ ውስን ጊዜን ለማመልከት ይውላል፥ ለምሳሌ አላፊ ውስን ጊዜን ለማመልከት ይህንን ጥቅስ እንመልከት፦
ዘዳግም 33፥15 በቀደሙትም ተራሮች ከፍተኛነት፥ በዘላለሙም ኮረብቶች ገናንነት። וּמֵרֹ֖אשׁ הַרְרֵי־קֶ֑דֶם וּמִמֶּ֖גֶד גִּבְעֹ֥ות עֹולָֽם׃

እዚህ አንቀጽ ላይ ለተራራ ቀዳማይነት የገባው ቃል "ቄዴም" קֶדֶם ሲሆን ለኮረብታ የገባው ቃል ደግሞ “ዖላም” עוֹלָ֗ם ነው፥ ለጌታው ባሪያ ለዘላለምም ባሪያው ይሁን ሲባል የተጠቀመበት ቃል “ዖላም” עוֹלָ֗ם ሲሆን መጻኢ ውስን ጊዜን ለማመልከት መጥቷል፦
ዘጸአት 21፥6 ወደ ደጁም ወደ መቃኑ አቅርቦ ጆሮውን በወስፌ ይብሳው፤ “ለዘላለምም” ባሪያው ይሁን። וְהִגִּישֹׁ֤ו אֲדֹנָיו֙ אֶל־הָ֣אֱלֹהִ֔ים וְהִגִּישֹׁו֙ אֶל־הַדֶּ֔לֶת אֹ֖ו אֶל־הַמְּזוּזָ֑ה וְרָצַ֨ע אֲדֹנָ֤יו אֶת־אָזְנֹו֙ בַּמַּרְצֵ֔עַ וַעֲבָדֹ֖ו לְעֹלָֽם׃ ס

መሢሑ ከ-"ቀድሞ" ዘመን ጀምሮ አወጣጡ ከአብርሃም፣ ከይስሐቅ፣ ከያዕቆብ፣ ከይሁዳ፣ ከእሴይ ወዘተ ... ነው፦
ዘኍልቍ 24፥17 ከያዕቆብ ኮከብ “ይወጣል”።
ዘኍልቍ 24፥19 ከያዕቆብም “የሚወጣ” ገዥ ይሆናል።
ዕብራውያን 7፥14 ጌታችን ከይሁዳ ነገድ “እንደወጣ” የተገለጠ ነውና።
ኢሳይያስ 11፥1 ከእሴይ ግንድ በትር “ይወጣል”።

ስለዚህ ሚክያስ 5፥2 ኢየሱስ ዓለም ሳይፈጠር እና ዘመን ሳይቆጠ አብን አህሎ እና መስሎ እንዲሁ ከባሕርይው ባሕርይው እና ከአካሉ አካሉ ወስዶ ወጣ፣ ተገኘ፣ ተወለደ ለሚለው የዘላለማዊ ውልደት”eternal generation” ደርዛዊ ሥነ-መለኮት ማስረጃ መሆን አይችልም። አሏህ ሂዳያህ ይስጣችሁ! ለእኛም ጽናቱን ይስጠን! አሚን።

ከዐቃቤ እሥልምና ወሒድ
ወሠላሙ ዐለይኩም
መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
237 views14:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 17:16:52
229 views14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-04 07:58:51
የኡስታዝ ወሒድ ዐቃቤ እሥልምና ፣ USTAZ Abu Heydar ፣ የሕያ ኢብኑ ኑህ - Yahya Ibnu Nuhe . እና ሌሎችም በአንድ ፔጅ በቪድዮና በጽሑፍ የሚለቀቅበትን ፔጅ ሁላችንም እየገባን like follow በማድረግ እናበረታታ ::

Facebook
https://www.facebook.com/tiriyachen/

Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
415 views04:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 20:12:41 --------------------------------------------------------
ወጀዛኩሙሏህ ኸይራ!
የበለጠ ለማወቅና ለመከታተል ፔጁን like . follow ያድርጉ






አዲስ ቪድዮ በዩትዩብ ቻነላችን ላይ

መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
‐‐‐
https://fb.me/tiriyachen
https://t.me/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
364 views17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 20:12:40 ጠቃሚ ዕውቀት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

96፥5 *ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን*፡፡ عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ

በሥነ-ዕውቀት ጥናት "መውሡዓህ" مَوْسُوعَة ማለት "መድብለ-ዕውቀት"encyclopedia" ማለት ሲሆን ፍልስፍናን መሠረት ያደረገ የዕውቀት መድብል ነው፥ "ፈልሠፋህ" فَلْسَفَة የሚለው ቃል "ፈልሠፈ" فَلْسَفَ ማለትም "ተፈላሰፈ" ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ፍልስፍና" ማለት ነው፥ ፍልስፍና የሚፈላሰፍ "ፈላስፋ" ደግሞ "ፈይለሡፍ" فَيْلَسُوف‎ ይባላል። ፍልስፍና "ኢስሙል ኢሥቲፍሃም" اِسْم الاِسْتِفْهَام ማለት "መጠይቅ ተውላጠ-ስም"interrogative pronoun" ያለበት ሲሆን እነዚህም፦
"ማ" مَاْ ማለት "ምንድን"what" ማለት ሲሆን "ምንነትን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው፣
"መን" مَنْ ማለት "ማን"who" ማለት ሲሆን "ማንነትን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው፣
"መታ" مَتَى ማለት "መቼ"when" ማለት ሲሆን "ጊዜን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው፣
"አይነ" أَيْنَ ማለት "የት"where" ማለት ሲሆን "ቦታን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው፣
"ከይፈ" كَيْفَ ማለት "እንዴት"how" ማለት ሲሆን "ሁኔታን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው፣
"ሊመ" لِمَ ማለት "ለምን"why" ማለት ሲሆን "ምክንያትን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው፣
"ከም" كَمْ ማለት "ምን ያህል"how much" ማለት ሲሆን "መጠንን" የምጠይቅበት መጠይቅ ተውላጠ-ስም ነው።

ፍልስፍና በራሱ ችግር ያለው ነገር ባይሆንም መሬት ላይ የማይተገበር እና በቃላት ተጀምሮ በቃላት የሚያልቅ አየር ላይ የተንሳፈፈ ዕውቀት ሁሉ መዋዕለ ጊዜን እና መዋዕለ ጉልበትን ከማፍሰስ እና ከማባከን ውጪ ለዲንያህ ሆነ ለአኺራ ሕይወት የሚፈይደው አንዳች ነገር እና ቁብ የለም፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 34, ሐዲስ 17
ጃቢር እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"አሏህን ጠቃሚ ዕውቀት ጠይቁት! ከማይጠቅም ዕውቀት በአሏህ ተጠበቁ!"*። عَنْ جَابِرٍ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ سَلُوا اللَّهَ عِلْمًا نَافِعًا وَتَعَوَّذُوا بِاللَّهِ مِنْ عِلْمٍ لاَ يَنْفَعُ ‏"‏

የማይጠቅም ዕውቀት የተቆላ ገብስ ነው፥ ሲበሉት ይጣፍጣል ሲዘሩት ግን አይበቅልም። ጠቃሚ ዕውቀት ለእለት ለእለት ሕይወታችን የሚሆን የነቅል ሆነ የዐቅል ዕውቀት ያካትታል። "ነቅል" نَقْل የሚለው ቃል "ነቀለ"نَقَلَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን ከአሏህ በነቢይ የሚተላለፍ ዕውቀት ነው፥ "ዐቅል" عَقْل የሚለው ቃል ደግሞ "ዐቀለ"عَقَلَ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን በቀለም የሚተላለፍ ዕውቀት ነው። አምላካችን አሏህ ሰውን ያላወቀውን ሁሉ በቀለም ያሳወቀው ነው፦
96፥4 *"ያ በብርዕ ያስተማረ"*፡፡ ٱلَّذِى عَلَّمَ بِٱلْقَلَمِ
96፥5 *ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን*፡፡ عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ

"ቀለም" قَلَم የሚለው ቃል "ቀለመ" قَلَمَ‎ ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን "ብዕር" ማለት ነው። ከሞት ጋር ሥራዎች ሲያከትሙ ጠቃሚ ዕውቀት ግን ለአኺራም አጅር የሚያስገኝ ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 25, ሐዲስ 20
አቡ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ሰው በሞተ ጊዜ ከሦስት ነገር ከሶደቀቱል ጃሪያህ ወይም በእርሱ የሚጠቀሙበት ዕውቀት አሊያም ዱዓእ የሚያደርግለት ሷሊሕ ልጅ በቀር ሥራው ያከትማል"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ‏ "‏ إِذَا مَاتَ الإِنْسَانُ انْقَطَعَ عَنْهُ عَمَلُهُ إِلاَّ مِنْ ثَلاَثَةٍ إِلاَّ مِنْ صَدَقَةٍ جَارِيَةٍ أَوْ عِلْمٍ يُنْتَفَعُ بِهِ أَوْ وَلَدٍ صَالِحٍ يَدْعُو لَهُ ‏"‏

መልካም ሥራዎች መሠረታቸው ጠቃሚ ዕውቀት ነው። ያለ ዕውቀት ማመን እና መልካም ነገር መሥራት እምነቱም ጭፍን እምነት ነው፥ ሥራውም እዚሁ ዲንያህ ላይ የሚቀር ነው፦
17፥36 *"ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል! መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ ተጠያቂ ነውና"*፡፡ وَلَا تَقْفُ مَا لَيْسَ لَكَ بِهِ عِلْمٌ ۚ إِنَّ السَّمْعَ وَالْبَصَرَ وَالْفُؤَادَ كُلُّ أُولَـٰئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْئُولًا

"ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል" የሚለው ኃይለ-ቃል ይሰመርበት! ይህንን የዐቅል ሆነ የነቅል ዕውቀት መፈለግ በሁሉም ሙሥሊም ላይ ግዴታ ነው፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 229
አነሥ ኢብኑ ማሊክ እንደተረከው፦ "የአላህ መልእክተኛም"*" አሉ፦ *"ዕውቀት መፈለግ በሁሉም ሙሥሊም ላይ ግዴታ ነው"*። عَنْ أَنَسِ بْنِ مَالِكٍ قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ طَلَبُ الْعِلْمِ فَرِيضَةٌ عَلَى كُلِّ مُسْلِمٍ

ይህንን ጠቃሚ ዕውቀት ግዴታ የሆነው ማወቅ ብቻ ሳይሆን ማሳወቅም ጭምር ነው፥ ማንም ስለ ዕውቀት የሚያውቀውን ተጠይቆ የደበቀ በትንሳኤ ቀን ከእሳት ልጓም ይለጎማል፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 266
አቡ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛም"ﷺ" እንዲህ አሉ፦ *"ማንም ስለ ዕውቀት የሚያውቀውን ተጠይቆ የደበቀ በትንሳኤ ቀን ከእሳት ልጓም ይለጎማል"*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ ‏ "‏ مَنْ سُئِلَ عَنْ عِلْمٍ يَعْلَمُهُ فَكَتَمَهُ أُلْجِمَ يَوْمَ الْقِيَامَةِ بِلِجَامٍ مِنْ نَارٍ ‏"‏

አምላካችን አሏህ ጠቃሚ ዕውቀት ዐውቀው ከሚያሳውቁ ያድርገን! አሚን።

ሼር

ከኡስታዝ ወሒድ ዑመር
ወሠላሙ ዐለይኩም
---------------------------------------------------------
ተጠራሩ፣ ሼር አርጉ፣ አንብቡ፣ አስነብቡ፣ ሁሉም ቦታ አሰራጩት! ሂዳያህ ያገኘውን ሰው የሚያገኘውን አጅር ከእርሱ ላይ ሳይቀነስ ሳይጨመር ታገኛላችሁ፦
ሡነን ኢብኑ ማጃህ መጽሐፍ 1, ሐዲስ 206
አቢ ሁረይራህ እንደተረከው፦ "የአሏህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ አሉ፦ "ማንም ወደ ምሪት የሚጣራ ጠሪ ጥሪውን የተከተሉት ከሚያገኙትን ምንዳ ከእነርሱ ላይ ሳይጓደል ያገኛል"። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ ـ صلى الله عليه وسلم ـ قَالَ ‏ "‏ مَنْ دَعَا إِلَى هُدًى كَانَ لَهُ مِنَ الأَجْرِ مِثْلُ أُجُورِ مَنِ اتَّبَعَهُ لاَ يَنْقُصُ ذَلِكَ مِنْ أُجُورِهِمْ شَيْئًا ‏"‏ ‏.‏
319 views17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 20:09:31
234 views17:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-01-03 20:08:21 ኢየሱስ አይመለክም

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል *”ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ”* ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَآ أَمَرْتَنِى بِهِۦٓ أَنِ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبَّكُمْ

ዒሳ የትምህርቱ ጭብጥ፦ “አላህ ጌታዬና ጌታችሁ ነው፤ ስለዚህ አምልኩት” የሚል ነው፤ አምላካችን አላህም ኢየሱስ ተናገር ብሎ ያዘዘው ቃል “ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ” ማለትን ነው፦
5፥117 በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል *”ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ”* ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡ مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَآ أَمَرْتَنِى بِهِۦٓ أَنِ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبَّكُمْ
3፥51 *”አላህ ጌታዬና ጌታችሁ ነው፤ ስለዚህ አምልኩት”* ፤ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው» አላቸው፡፡ إِنَّ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبُّكُمْ فَٱعْبُدُوهُ ۗ هَٰذَا صِرَٰطٌۭ مُّسْتَقِيمٌۭ
5፥72 እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! *”ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ”* ፤ እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ لَقَدْ كَفَرَ ٱلَّذِينَ قَالُوٓا۟ إِنَّ ٱللَّهَ هُوَ ٱلْمَسِيحُ ٱبْنُ مَرْيَمَ ۖ وَقَالَ ٱلْمَسِيحُ يَٰبَنِىٓ إِسْرَٰٓءِيلَ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبَّكُمْ ۖ إِنَّهُۥ مَن يُشْرِكْ بِٱللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ ٱللَّهُ عَلَيْهِ ٱلْجَنَّةَ وَمَأْوَىٰهُ ٱلنَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّٰلِمِينَ مِنْ أَنصَارٍۢ
19፥36 ዒሳ አለ፦ *”አላህም ጌታዬ ጌታችሁም ነውና ተገዙት”* ፡፡ ይህ ቀጥተኛ መንገድ ነው፡፡» وَإِنَّ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبُّكُمْ فَٱعْبُدُوهُ ۚ هَٰذَا صِرَٰطٌۭ مُّسْتَقِيمٌۭ

አምልኮ” የሚለው ቃል በእብራይስጥ “አባድ” עָבַד ፣ በግሪክ “ላትሬኦ” λατρεύω ፤ በዐረቢኛ “ዒባዳ” عبادة ሲሆን “ስግደት” ደግሞ በዕብራይስጥ “ሻቻህ” שָׁחָה ፣ በግሪክ ደግሞ “ፕሮስካኒኦ” προσκυνέω ፣ በዐረቢኛ “ሡጁድ” سُّجُود ነው፤ እነዚህ ቃላት በዐረቢኛ ባይብል ላይ በአንድ አንቀጽ ላይ ለየቅል ተቀምጠዋል፦
ማቴዎስ 4፥10 ያን ጊዜ ኢየሱስ፡— ሂድ፥ አንተ ሰይጣን ለጌታህ ለአምላክህ *ስገድ* እርሱንም ብቻ *አምልክ*፡ ተብሎ ተጽፎአልና፡ አለው። حِينَئِذٍ قَالَ لَهُ يَسُوعُ: «اذْهَبْ يَا شَيْطَانُ! لأَنَّهُ مَكْتُوبٌ: لِلرَّبِّ إِلَهِكَ تَسْجُدُ وَإِيَّاهُ وَحْدَهُ تَعْبُدُ».

ልብ አድርግ “ስገድ” ለሚለው ቃል የመጣው “ተሥጁዱ” تَسْجُدُ ሲሆን “አምልክ” ለሚለው ቃል ደግሞ “ተዕቡዱ” تَعْبُدُ ነው። “እርሱንም ብቻ አምልክ” የሚለው ሃይለ-ቃል አምልኮ የአንድ አምላክ ብቻ ገንዘብ መሆኑን እንረዳለን። ይህንን እሳቤ ይዘን ለኢየሱስ “ሰገዱለት” ተብሎ የተቀመጠው ቃል “ሠጀዱሁ ለሁ” سَجَدُوا لَهُ ብቻና ብቻ ነው፦
ማቴዎስ 2፥11 ወደ ቤትም ገብተው ሕፃኑን ከእናቱ ከማርያም ጋር አዩት፥ ወድቀውም *ሰገዱለት*፥ فَلَمَّا رَأَوُا النَّجْمَ فَرِحُوا فَرَحاً عَظِيماً جِدّاً وَأَتَوْا إِلَى الْبَيْتِ وَرَأَوُا الصَّبِيَّ مَعَ مَرْيَمَ أُمِّهِ فَخَرُّوا وَسَجَدُوا لَهُ
ማቴዎስ 14፥33 በታንኳይቱም የነበሩት፡— በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ነህ፡ ብለው *ሰገዱለት*። وَالَّذِينَ فِي السَّفِينَةِ جَاءُوا وَسَجَدُوا لَهُ قَائِلِينَ: «بِالْحَقِيقَةِ أَنْتَ ابْنُ اللَّهِ!».
ዕብራውያን 1፥6 ያለው ከቶ ለማን ነው? ደግሞም በኵርን ወደ ዓለም ሲያገባ፡— የእግዚአብሔር መላእክት ሁሉም ለእርሱ *ይስገዱ*፥ ይላል። وَأَيْضاً مَتَى أَدْخَلَ الْبِكْرَ إِلَى الْعَالَمِ يَقُولُ: «وَلْتَسْجُدْ لَهُ كُلُّ مَلاَئِكَةِ اللهِ».

“ሡጁድ” سُّجُود ፍጡራን ለፍጡራን እጅ መንሳትን ያመለክታል፤ “ይሰግዱ” ለሚለው ቃል ያገለገለው “የሥጁዱነ” َيَسْجُدُونَ ነው፦
ራእይ 3፥9 እነሆ፥ አይሁድ ሳይሆኑ፡— አይሁድ ነን ከሚሉ ነገር ግን ከሚዋሹ ከሰይጣን ማኅበር አንዳንዶችን እሰጥሃለሁ እነሆ፥ መጥተው በእግሮችህ ፊት *ይሰግዱ* ዘንድ እኔም እንደ ወደድሁህ ያውቁ ዘንድ አደርጋቸዋለሁ። هَئَنَذَا أَجْعَلُ الَّذِينَ مِنْ مَجْمَعِ الشَّيْطَانِ، مِنَ الْقَائِلِينَ إِنَّهُمْ يَهُودٌ وَلَيْسُوا يَهُوداً، بَلْ يَكْذِبُونَ: هَئَنَذَا أُصَيِّرُهُمْ يَأْتُونَ وَيَسْجُدُونَ أَمَامَ رِجْلَيْكَ، وَيَعْرِفُونَ أَنِّي أَنَا أَحْبَبْتُكَ. لأَنَّكَ حَفِظْتَ كَلِمَةَ صَبْرِي،እግዚአብሔር

ፈጣሪ ግን በግልጽ “የዕቡዱነኒ” َيَعْبُدُونَنِي ማለትም “ያመልኩኛል” ብሏል፦
ሐዋ. ሥራ 7፥7 ደግሞም ፡— እንደ ባሪያዎች በሚገዙአቸው ሕዝብ ላይ እኔ እፈርድባቸዋለሁ፥ ከዚህም በኋላ ይወጣሉ በዚህም ስፍራ *ያመልኩኛል*፤ አለ። وَتَكَلَّمَ اللهُ هَكَذَا: أَنْ يَكُونَ نَسْلُهُ مُتَغَرِّباً فِي أَرْضٍ غَرِيبَةٍ فَيَسْتَعْبِدُوهُ وَيُسِيئُوا إِلَيْهِ أَرْبَعَ مِئَةِ سَنَةٍ وَالْأُمَّةُ الَّتِي يُسْتَعْبَدُونَ لَهَا سَأَدِينُهَا أَنَا يَقُولُ اللهُ. وَبَعْدَ ذَلِكَ يَخْرُجُونَ وَيَعْبُدُونَنِي فِي هَذَا الْمَكَانِ.

ዋቢ መጽሐፍ ዐረቢክ ባይብል ይመልከቱ፦
Arabic/English Online Bible
http://www.copticchurch.net/cgibin/bible/
ከወንድም ወሒድ ዑመር

ወሰላሙ አለይኩም
256 viewsedited  17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ