Get Mystery Box with random crypto!

TIKVAH-ETHIOPIA

የቴሌግራም ቻናል አርማ tikvahethiopia — TIKVAH-ETHIOPIA
ርዕሶች ከሰርጥ:
Furtheraheadtogether
Mpesasafaricom
Addisababa
Genocide
Rwanda
Remembering
Kwibuka
Safaricomethiopia
Nevacomputer
Tikvahethiopiafamilyhawassa
All tags
የሰርጥ አድራሻ: @tikvahethiopia
ምድቦች: ዜና , ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.35M
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 433

2021-10-01 12:15:25
200.7K views09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-01 11:12:10
203.3K views08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 22:42:05
69.7K viewsedited  19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 22:34:17
የአፋር ክልል እና ሲዳማ ክልል መንግስት የካቢኔ አባላት እነ ማን ናቸው ?

በዛሬው ዕለት የአዲስ መንግስት ምስረታ ያካሄዱት የአፋር ክልል እና ሲዳማ ክልል ምክር ቤቶች በክልሎቹ ፕሬዜዳንቶች (አቶ አወል አርባ እና አቶ ደስታ ሌዳሞ) የቀረቡላቸውን የካቢኔ አባላት ሹመት አፅድቀዋል።

የሁለቱም ክልል ካቢኔ አባላት ሙሉ ስም ዝርዝር ከላይ ተያይዟል።

@tikvahethiopia
69.7K views19:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 21:55:31
96.5K viewsedited  18:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 21:54:53
#ETHIOPIA

ሀገራችን ኢትዮጵያ ተጨማሪ 48 ዜጎችን በኮቪድ-19 ሳቢያ አጥታለች።

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የጤና ሚኒስቴር ይፋ ባደረገው ሪፖርት ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 48 ሰዎች ሲሞቱ ከተደረገው 10,226 የላብራቶሪ ምርመራ ደግሞ 1,352 ሰዎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው ተገኝተዋል።

የዛሬው ሪፖርት እንደሚያሳየን 790 ሰዎች በፅኑ ታመዋል።

#ጥንቃቄ #TikvahFamily

@tikvahethiopia
88.3K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 21:07:43
* UPDATE

የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ ኢትዮጵያ የድርጅቱን ከፍተኛ ሰብዓዊ አስተባባሪዎች ጨምሮ ሰባት የድርጅቱን ሰራተኞች ለማባረር መወሰኗን በመስማቴ ደንግጫለሁ ሲሉ አስታወቁ፡፡

ዋና ጸሃፊው ሁኔታውን በማስመልከት በቃል አቀባይ ጽህፈት ቤታቸው በኩል መግለጫ አውጥተዋል፡፡

በመግለጫው “ኢትዮጵያ የድርጅቱን ከፍተኛ ሰብዓዊ አስተባባሪዎች ጨምሮ ሰባት የድርጅቱን ሰራተኞች ለማባረር መወሰኗን በመስማቴ ደንግጫለሁ” ነው ያሉት፡፡

ሁሉም ሰብዓዊ ተግባራት በሰብዓዊነት፣ ያለ አድልዖ፣ በነጻ እና ገለልተኛነት መርሆዎች የሚመሩ ናቸው ያሉ ሲሆን ድርጅታቸው በኢትዮጵያ ምግብና መድሃኒቶችን ጨምሮ ህይወት አድን ድጋፎችን እያደረገ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

“ይህን በሚሰሩ የኢትዮጵያ ስታፍ አባላት ሙሉ መተማመን አለኝ” ም ነው ጉቴሬዝ በመግለጫው ያሉት፡፡

ድርጅታቸው ሰብዓዊ ድጋፍ የሚሹ ኢትዮጵያውያንን ለመርዳት ቁርጠኛ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

ሰራተኞቹ ስራቸውን በሚቀጥሉበት ሁኔታ ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመነጋገር ላይ መሆናቸውንም ዋና ጸሃፊው አስታውቀዋል፡፡

ኢትዮጵያ በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ ገብተዋል ያለቻቸውን ሰባት የድርጅቱን ሰራተኞች በ72 ሰዓታት ሃገሪቱን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቧ ይታወቃል።

Credit : አል ዓይን

@tikvahethiopia
122.5K viewsedited  18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 19:32:01
ነገ የሚዘጉ መንገዶች !

ነገ ዓርብ መስከረም 21 ቀን 2014  ከጧቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ ከፀጥታ ስራ ጋር በተያያዘ በመስቀል አደባባይ እና ዙሪያው በሚገኙ መንገዶች ለተወሰነ ሰዓት ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ የተለመደ ትብብሩን እንዲያደርግም ፖሊስ ጥሪ አስተላልፏል።

በዚህም መሰረት፦

• ከቦሌ አየር መንገድ በሚሊኒዬም አዳራሽ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ወሎ ሰፈር አደባባይ

• ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚውስደው መንገድ 22 ማዞሪያ

• ከ4ኪሎ በውጭ ጉዳይ ሚ/ር ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ፓርላማ መብራት

• በቸርችር ጎዳና ፒያሳ ወደ መስቀል የሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ

• ከጦር ሃይሎች በለገሃር ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት

• ከጀሞ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ የሚወስደው መንገድ ሳር ቤት አደባባይ

• ከሳሪስ ፣ በጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ አጎና ሲኒማ

• ከቦሌ፣ አትላስ ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ከርስቲያን የሚወስደው መንገድ ኤድናሞል አደባባይ

• ከአዋሬ ወደ ካሳንቺስ የሚወስደው መንገድ ሴቶች አደባባይ

• ከልደታ በጌጃ ሰፈር፣ ጤና ጥበቃ የሚወስደው መንገድ አብነት ፈረሰኛ አካባቢ ከጠዋቱ 3:00 ጀምሮ ለጊዜው መንገዶቹ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆናቸውን ህብረተሰቡ ተገንዝቦ የተለመደውን ትብብር እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ መልዕክቱን አስተላልፏል።

@tikvahethiopia
162.6K viewsedited  16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 19:31:54
ምርጫው እስከ ሁለት ሰዓት ተራዝሟል።

በዛሬው እለት በሐረሪ፣ በሶማሌ እና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ክልል ድምጽ አሰጣጥ እና ህዝበውሳኔ ሲከናወን ውሏል።

ነገር ግን ተጨማሪ የድምጽ መስጫ ሰአት የሚያስፈልጋቸው ምርጫ ክልሎች በመገኘታቸው እና ድምጻቸውን መስጠት የሚፈልጉ ዜጎች እድሉን እንዳያጡ በማሰብ የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ እስከ ምሽቱ 2 ሰአት ድረስ መራዘሙን ምርጫ ቦርድ አሳውቋል።
 
1. በሐረሪ ክልል በሚገኙ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች
2. ከሐረሪ ክልል ውጪ ለሐረሪ ክልል የሚመርጡ ምርጫ ጣቢያዎች
3. ሕዝበውሳኔ በሚካሄድባቸው ሁሉም የምርጫ ክልሎች (ህዝበውሳኔን ለብቻ ለሚያካሂዱ እንዲሁም ህዝበውሳኔን እና ምርጫን ለሚያካሂዱ በሙሉ)  
አስፈጻሚዎች ከላይ ከተጠቀሱት ቦታዎች ውጪ ባሉ ቦታዎች 12 ሰአት ሲሞላ ሰልፍ ላይ ያሉ መራጮችን በማስተናገድ ምርጫውን እንዲያጠናቅቁ እንዲሁም 12 ሰአት ላይ መራጮችን አስተናግደው ያጠናቀቁ ጣቢያዎች በህጉ መሰረት ታዛቢዎች በተገኙበት ቆጠራን እንዲጀምሩ ቦርዱ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
148.9K viewsedited  16:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-30 19:21:43
ኢትዮጵያ 7 የUN ሰራተኞችን ሀገሪቱ ለቀው እንዲወጡ አዘዘች።

የኢትዮጵያ መንግሥት በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) ስር በተለያዩ ኤጀንሲዎች ውስጥ የሚሰሩ 7 የውጭ አገር ዜጎች በ72 ሰዓት ውስጥ ኢትዮጵያን ለቀው እንዲወጡ ትእዛዝ ማስተላለፉን የኢፌዴሪ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንዳስታወቀው የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት የመንግሥታቱ ድርጅት ባልደረቦች በአገር ውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ህገ ወጥ ሥራ ሲሠሩ የተገኙ መሆናቸውም ነው የተገለፀው።

የኢትዮጵያን ድንበር ለቀው እንዲወጡ የታዘዙት ሰባት የውጭ አገር ዜጎች ፦

1. የዩኒሴፍ የኢትዮጵያ ተወካይ UNICEF ሚስ አዴል ኮደር

2. የዩኤን የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ግራንት ሊያቲ

3. የዩኤን የተራድኦ ምክትል አስተባባሪ ተወካይ ሚስ ጋዳ ኤልታሂር ሙዳዊ፣

4. የዩኤን የሰላምና ልማት አማካሪ ከውሲ ሳንቼሎቲ

5. የሰብአዊ መብት ከፍተኛ ኮሚሽነር ቢሮ ባልደረባ ሶኒ ኦኒግ ቡላ

6. የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት UNOCHA ምክትል አስተባባሪ ሰኢድ መሀመድ ሀርሲ

7. የተመድ የሰብአዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ፅ/ቤት UNOCHA ኃላፊ ሚስ ማርሲ ቪጎዳ ናቸው።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
152.7K viewsedited  16:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ