Get Mystery Box with random crypto!

የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የሰርጥ አድራሻ: @tewahdo_haymanotie
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.40K
የሰርጥ መግለጫ

✍️"አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች ❹፥➎)✅
✍️ጥንታዊቷንና እውነተኛዋን ሃይማኖት ለመማር ከ1️⃣ኛ ዓመት ጀምሮ ኮርሶች እየተሰጡበት ያለ የእግዚአብሔር ቤት ነው።
✍️የማንኛውም ሃይማኖት ተከታይ ገብቶ መማር ይችላል። 🌹ቅድሚያ ለነፍስዎ ይኑሩ!🌹
ኮርሶች👇
t.me/Tewahdo_Haymanotie/703
አገልጋዮችን ለማግኘት
@Dingl_Ruhruhitu_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-31 22:55:20 @Tewahdo_Haymanotie
747 views19:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:52:03 @Tewahdo_Haymanotie
379 views17:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 22:48:26 @Tewahdo_Haymanotie
795 views19:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 22:42:44 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
፫.፭, #ምሥጢረ_ንስሐ
፫.፭.፫,
#የንስሐ_አጀማመር
የሰው ልጅ ሁሉ አባት የሆነው አዳም ምክረ እግዚአብሔርን ዘንግቶ በምክረ ከይሲ ዲያቢሎስ ተታልሎ ሕግ ባፈረሰ ጊዜ ጸጋው ተገፎና ባሕርይው ተጎሳቅሎ ነበር።
ነገር ግን እንደወደቀ ሳይቀር እንባውን እያፈሰሰ በሐዲስ ተፈጥሮ እንዲያድሰው ወደ ወጣበት ርስት መልሶ እንዲያገባው ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።
እግዚአብሔርም ልመናውን ሰምቶ ከመከራው አድኖ ተስፋ ድኅነት ሰጥቶታል።
የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜም አንድያ ልጁን ልኮ አድኖታል። (ገላ 4፥4)


በብሉይ ኪዳን የመጀመሪያው ተነሳሒ አባታችን አዳም ነው። እርሱን አብነት አድርገው ልጆቹ ቢበድሉም በሕገ ልቦና ኋላም በሕገ ኦሪት የኖሩ አበው ንስሐን ገንዘብ አድርገው ይኖሩ ነበር።

ይሁን እንጂ በምድር በሥጋ መከራው ቢቀልላቸውም ዞሮ ዞሮ ከሞት ማምለጥ/ከሲኦል መሰወር ግን አይቻላቸውም ነበር።

ነቢዩ ኢሳይያስ "ሁላችን እንደ ርኩስ ሰው ሁነናል ጽድቃችንም እንደ መርገም ጨርቅ ነው።" (ኢሳ 64፥6) ብሎ መናገሩ በብሉይ ኪዳን የነበረው ንስሐ ሰውን ፍጹም ከእግዚአብሔር ጋር ማስታረቅ ስላልቻለ ነው።

ምንም እንኳን ነቢያት በየዘመናቱ ከደረሰውና ከሚደርሰው መከራ በምክራቸውና በትምህርታቸው ሕዝቡን ወደ ንስሐ ቢመልሱም፤ በጸሎትና በምልጃቸው ሕዝቡን ከመዓት፣ ከቁጣና ከሞት ቢያድኑም (መዝ 105፥23) ይህ ሁሉ ተጋድሎአቸው ግን የሰውን ልጅ በንስሐ ከሲኦል ወደ ገነት ሊመልስ አልቻለም። ሁሉም በጥንተ አብሶ ባለእዳ ነበሩና። (መዝ 63፥5)


ሐዲስ ኪዳን በሐዲስ ኪዳን መሥዋዕቱ በፍጡር ባለመሆኑና ሞት የማያሸንፈው በመሆኑ ንስሐ ፍጹም ሆኗል። ማንም ሊከፍለው ያልቻለውን የአዳምን የበደል ዕዳ እግዚአብሔር ወልድ ሰው ሆኖ ከፈለልን።

እኛ በበደልን እርሱ ፍጹም ካሣን ክሦልን ዐፅመ አዳም ባረፈበት በጎለጎታ ተሰቅሎ የሞትን መውጊያ ሰበረልን።
የመቃብርንም ኃይል ሻረው። ርቀን የነበርነውን አቅርቦ ልጆቼ አለን። (ማቴ 27፥33 ፤ 1ኛ ቆሮ 15፥56) በበደሉ አዝኖና ተክዞ በንስሐ የሚመለስ ሰው ሁሉ ለርስት መንግስተ ሰማያት ተካፋይ እንደሚሆንም ተስፋ ሰጠው።

በሐዋርያት አባቶቻችን ዘመን ንስሐ ከ"እምየት" ጋር የተያያዘ ነበር። ምክኒያቱም ተነሳሕያኑ ከቤተ አይሁድ አልያም ከአሕዛብ ወገን ስለነበሩ አስቀድመው ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰው ልጆችን ለመፈለግ ከቤተልሔም ዋሻ እስከ ቀራኒዮ ጎለጎታ ያለፈበትን የማዳን ጉዞና የፈጸመውን የቤዛነት ሥራ ተምረውና በባሕርይ አምላክነቱ አምነው ንስሐ ይገቡ ነበር። (የሐዋ 2፥28)

እንዲያውም በመጀመሪያዎቹ የሐዲስ ኪዳን ዓመታት ንስሐ በአደባባይ በሕዝብ ፊት ነበር የሚፈጸመው። (ሐዋ 19፥18 ፤ 1ኛ ቆሮ 7፥11 ፤ ያዕ 5፥16) በኋላ ግን የአንዱን ኃጢአት ሌላው ሰምቶ እንዳይሰናከል በማሰብ በምሥጢር ሆነ። በተነሳሒው፣ በመምህረ ንስሐውና በእግዚአብሔር መካከል የሚቀር ምሥጢረ ንስሐ ነው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->በንስሐ የሚገኙ ጸጋዎች
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ➒❽
1.0K views19:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 22:25:48 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
፫.፭, #ምሥጢረ_ንስሐ
፫.፭.፩, #የንስሐ_ትርጉም
ንስሐ ሥርው ቃሉ "ነስሐ" የሚለው የግዕዝ ግሥ ሲሆን ትርጓሜውም ተጸጸተ፣ ተቆረቆረ ማለት ነው።

ንስሐ ሊሠራት ስለማይገባ ሥር ወይም ስለ ኃጢአት ማዘን፤ ምነው ባልሠራሁት፣ ምነው ባላደረግሁት፣ ምን ቀን ጣለኝ ብሎ መቆጨት ነው።

የንስሐ ልብ ያለው፣ ንስሐ በመግባት ፍሬ ማፍራት የሚችለው በሥነ ፍጥረት የሰው ልጅ ብቻ ነው። ሌሎች ፍጥረታት የመጸጸት ፍጥረት የላቸውም።

፫.፭.፪, #የንስሐ_ምንነት
ክርስቲያን በጥምቀት ከዓለም ክፉ ሥራዎች ሁሉ የተለየና የሞተ ነው። ሕይወቱ በሙሉ ለክርስቶስ የተሰጠ ነውና። "እንግዲህ ወንድሞቼ ሆይ ሰውነታችሁን እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝና ሕያው ቅዱስም መሥዋዕት አድርጋችሁ ታቀርቡ ዘንድ በእግዚአብሔር ርኅራኄ እለምናችኋለሁ።" (ሮሜ 12፥1-2) ተብሎ እንደተጻፈ የክርስቲያን አካሉ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያም ነው ተብሏል። (1ኛ ቆሮ 6፥19)

ይሁን እንጂ የሰው ልጅ ስሑት/የሚሳሳት በመሆኑ ከኃጢአት የተነሣ ንጽሐ ሥጋውና ንጽሐ ነፍሱን ያሳድፋታል። በኃጢአት ወድቆ ፈጣሪውን ይበድላል።

ከዚህም የተነሣ የክርስቲያኖች ጉዞ ፈተና የበዛበት እየወደቁ እየተነሡ የሚጓዙት እንጂ ኃጢአት ሳይሠሩ እንደመላእክት በንጽሕና አልያም ወድቀው ለዘላለም እሳት እንደተጠበቁት አጋንንት ተስፋ የሚቆርጥበት ሕይወት አይደለም።

አበው "ቅዱሳንን ቅዱሳን ያስባላቸው ኃጢአትን ሠርተው ባለመውደቃቸው ሳይሆን ወድቀው በንስሐ መነሣት መቻላቸው ነው።" ማለታቸው የክርስትናን ኑሮ ይልቁንም የንስሐን ምንነት ፍንትው አድርጎ የሚያስረዳን ነው።

ከላይ በትርጓሜው እንደተመለከትነው ንስሐ ኃጢአተኞች ተጸጽተው ከእግዚአብሔር ጋር የሚታረቁበት ደገኛ ሥርዓት ነው። የተባለውም ለዚህ ነው።

ምሥጢር ያስባለውም ለካሕናት በተሰጣቸው በዓይን የማይታየው ሥልጣን አማካይነት በንስሐ ተመላሾች የሚያገኙት የኃጢአት ሥርየት ስላለ ነው። "ንስሐ መግባት" ማለትም በተሠራው ኃጢአት መጽናናትና ዳግመኛ ያንን ኃጢአት መልሶ ላለመሥራት መወሰን ነው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->የንስሐ አመሠራረት፦
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ➒❼
1.2K viewsedited  19:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 22:45:22 ፫.፬, ምሥጢረ ተክሊል – Telegraph
https://telegra.ph/%E1%88%9D%E1%88%A5%E1%8C%A2%E1%88%A8-%E1%89%B0%E1%8A%AD%E1%88%8A%E1%88%8D-08-26


ምሥጢረ ተክሊል-ክፍል (፬)

ገፅ ❾❻
1.3K viewsedited  19:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 22:31:26 https://telegra.ph/%E1%88%9D%E1%88%A5%E1%8C%A2%E1%88%A8-%E1%88%9C%E1%88%AE%E1%8A%95-08-25


ምሥጢረ ተክሊል-ክፍል (፫)

ገፅ ❾➎
1.5K viewsedited  19:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 23:42:09 ፫.፬, ምሥጢረ ተክሊል – Telegraph
https://telegra.ph/%E1%88%9D%E1%88%A5%E1%8C%A2%E1%88%A8-%E1%89%B0%E1%8A%AD%E1%88%8A%E1%88%8D-08-23


ምሥጢረ ተክሊል-ክፍል (፪)

ገፅ ❾❸
1.5K viewsedited  20:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 23:04:32 ፫.፬, መምሥጢረ ተክሊል – Telegraph
https://telegra.ph/%E1%88%98%E1%88%9D%E1%88%A5%E1%8C%A2%E1%88%A8-%E1%89%B0%E1%8A%AD%E1%88%8A%E1%88%8D-08-22

ምሥጢረ ተክሊል-ክፍል (፩)

ገፅ ❾❷
1.7K viewsedited  20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 23:00:30 https://telegra.ph/%E1%88%A5%E1%88%AD%E1%8B%93%E1%89%B0-%E1%89%85%E1%8B%B3%E1%88%B4-08-21


ገፅ ❾❶
1.8K viewsedited  20:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ