Get Mystery Box with random crypto!

የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የሰርጥ አድራሻ: @tewahdo_haymanotie
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.40K
የሰርጥ መግለጫ

✍️"አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች ❹፥➎)✅
✍️ጥንታዊቷንና እውነተኛዋን ሃይማኖት ለመማር ከ1️⃣ኛ ዓመት ጀምሮ ኮርሶች እየተሰጡበት ያለ የእግዚአብሔር ቤት ነው።
✍️የማንኛውም ሃይማኖት ተከታይ ገብቶ መማር ይችላል። 🌹ቅድሚያ ለነፍስዎ ይኑሩ!🌹
ኮርሶች👇
t.me/Tewahdo_Haymanotie/703
አገልጋዮችን ለማግኘት
@Dingl_Ruhruhitu_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-07-04 22:02:52 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#የቅኔ_ማሕሌት_ንዋያተ_ቅዱሳት
...
፪. ጽናጽል፦ ጸነጸለ መታ ካለው ግሥ የተገኘ ነው። ጽናጽላት ስንል ብዛትን፤ ጽናጽል ስንል ነጠላን የሚያመለክት ሲሆን ትርጉሙም ሻኩራ፣ ቃጭል እንደማለት ነው።

ጽናጽል ከነሐስ፣ ከብርና ከሌሎችም ማዕድናት ሊሠራ የሚችል የዜማ መሣሪያ ነው። ጽናጽል ያማረ ድምጽ ያለው ሆኖ መልክና ልዩ ጌጥም አለው።

በጥንት ዘመን ግብጻውያን እግዚአብሔርን ያመሰግኑበት እንደነበር ይነግረናል። (መዝ 150፥5 ፤ 2ኛ ሳሙ 6፥5)

አሠራሩም ከላዩ ቀስተ ደመና ይመስላል፤ ከታች መጨበጫው አንድ ሆኖ የላም ምስል ነበረበት።
ዕብራውያንም ይገለገሉበት ነበር።

በኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ጽናጽል ላዩ ቀስተ ደመና መስሎ መሠራቱ "እሰይም ቀስትየ በውስተ ደመና" ለዘላለም የማደርገው የቃል ኪዳን ምልክት ይህ ነው። (ዘፍ 9፥12) ብሎ በተናገረው መሠረት እግዚአብሔር ለኖኅ የገባለት ቃል ኪዳን ምሳሌ ነው።

አራቱ ዘንጎች የአራቱ ባሕርያተ ሥጋ (ነፋስ፣ እሳት፣ መሬት፣ ውሃ)፤ በአራቱ ዘንጎች ውስጥ ያሉት ቅጠሎች ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ የተፈጠረ ፍጥረት በሙሉ ምሳሌ ናቸው።

እነዚህም ሲንቀሳቀሱ ከአራቱ ባሕርያተ ሥጋ የተፈጠሩትን ፍጥረታት ሰውንም አላጠፋም ብለህ ቃል ኪዳን ሰጥታሃልና ኪዳንህን አስብልን በኃጢአታችን አታጥፋን ብለው ማመስገናቸውን የሚያመለክት ነው።

መሰላሉ ያዕቆብ በፍኖተ ሎዛ ተኝቶ ያየው መሰላል ምሳሌ ነው። (ዘፍ 28፥11-13... ህልምም አለመ እንሆ መሰላል በምድር ላይ ተተክሎ ራሱም ወደ ሰማይ ደርሶ እንሆም የእግዚአብሔር መላእክት ይወጡባት ይወርዱባት ነበር።) እንዳለ በግራና በቀኝ በሉት ዓምዶች መካከል ያሉት ሁለት ቀጫጭን ጋድም ዘንጎች የመሰላል፤ በዘንጎቹ ላይ ያሉት ቀጠሎች የመላእክታን፤ በቀኝና በግራ ያሉት ሁለቱ ዓምዶች የብሉይ ኪዳንና የሐዲስ ኪዳን ምሳሌዎች ናቸው።
አንድም ሁለቱ አግድሞች የፍቅረ እግዚአብሔር እና የፍቅረ ቢጽ/ሰው ምሳሌ ናቸው።

፫. መቋሚያ፦ መደገፊያ፣ መመርኮዣ ማለት ነው።
አገልግሎቱም በቅዳሴ ጊዜ ምእመናኑ፤ በማህሌቱ ጊዜ ካህናት በከበሮና በጽናጽል እንዲሁም በመቋሚያ እግዚአብሔርን ያመሰግኑበታል/ያገለግሉበታል።

እግዚአብሔር ለአዳም ተስፋ አድርጎ የሰጠው የመስቀል ምሳሌ ነው። በመሆኑም ቅዱስ ያሬድና አባ እንጦንስ በማህሌትና በጸሎት ወይም በሰዓታት ጊዜ መቋሚያ እንዲያዝ አድርገዋል። ቅዱስ እንጦንስ በጸሎት ጊዜ፤ ቅዱስ ያሬድ በማህሌት ጊዜ መቋሚያን ተጠቅመዋል።

እንዲሁም ሙሴ ባህረ ኤርትራን የከፈለበትንና በትረ መስቀልን በትክሻው ይዞ (ንሴብሆ ለእግዚአብሔር ስቡሃ ዘተሰብሃ) በማለት ያመሰገነውን ምስጋና የሚያሳስብ እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክረስቲያን ያስተምራሉ።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->የንዋያተ ቅዱሳት የአቀማመጥና የአጠቃቀም ሥርዓት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❽
2.4K views19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-03 22:29:06 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#የቅኔ_ማሕሌት_ንዋያተ_ቅዱሳት
፩. ከበሮ፦
አታሞ፣ ነጋሪት፣ ለክብረ በዓል የሚመታ፣ ትእምርተ ክብር፣ ጯሂ፣ ተሰሚ ማለት ነው።

መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትውፊትና ምሳሌነት አለው (መዝ 150 ፤ ኤር 38፥4 ፤ ዳን 3፥10 ፤ ኢሳ 5፥12 ፤ 2ኛ ሳሙ 6፥5 ፤ ዘጸ 15፥20)

ከበሮ ከከብት ቆዳ ተጠፍሮ ከእንጨት ወይም ከብር የሚሠራ የዜማ መሣሪያ ነው።

ከበሮ የጌታችንን መካራ የምናስታውስበት የኢየሱስ ክረስቶስ ምሳሌ ነው።
●ከበሮ ግራና ቀኝ ሲመታ፦ ኢየሱስ ክረስቶስ ግራና ቀኝ በአይሁድ "አሁን ማነው የመታህ ትንቢት ተናገር እያሉ" የመቱትን ያስታውሰናል። (ማቴ 27፥21)
●እየተንቀሳቀሱ (እያሸበሸቡ) መምታት፦ አይሁድ ጌታችንን አያንገላቱ ወደ ቀራኒዮ የመውሰዳቸው ምሳሌ ነው።
●ከእርጋታ ወደ ፍጥነት እያሸጋገሩ መምታት፦ ይህም በመጀመሪያ እያፌዙ በኋላም ሰንበት እንዳይገባባቸው፤ በጲላጦስም ተመርምሮ እንዳያድነው በማለት እያዳፉ እያንገላቱ በፍጥነት የመምታታቸው ምሳሌ ነው።
●መሬት አስቀምጦ መምታት፦ ጌታችን በዕለተ አርብ በምድር ላይ ወድቆ የመንገላታቱ ምሳሌ ነው። እንዲሁም አካሉ በብር ወይም በእንጨት የሚሠራው የተቀበረበት መቃብር ምሳሌ ነው።

●ከበሮ የሚለብሰው ጨርቅ፦ በዕለተ አርብ አይሁድ ጌታችንን ያለበሱት "ቀይ ከለሜዳ" ጨርቅ በመሆኑ ይህንን ምሳሌ በማድረግ ልብሱን ገፈው ቀይ እንዳለበሱት (ማቴ 26፡28) የምናስበው ነው፡፡
●በከበሮው ላይ የተለጠፈው ጠፍር፦ ይህን ስንመለከት በጌታችን ጀርባ ላይ የታየው (6666) የግርፋት ሰንበር ምሳሌ ነው። "እጆቼንና እግሮቼን ቸነከሩኝ አጥንቶቼ ሁሉ ተቆጠሩ" ተብሎ እንደተጻፈ አጥንቶቹ እስኪቆጠሩ ድረስ መገረፉን እናስብበታለን።
●የከበሮው ማንገቻ፦ ጌታችንን አሥረው የጎቶቱበት ገመድ ምሳሌ ነው።
የከበሮውን ማንገቻ በአንገታችን የምናስገባው ይህ እውነት በጌታችን ላይ የተፈጸመ መሆኑን አይሁድ ስለኛ መከራን የተቀበለውን ጌታችንን ወደ ቀራኒዮ ሲወስዱት የእጁን መጋፊያና መጋፊያ እስኪገጥም በገመድ የእንግርግሪት አስረው አንገላተውታል። በከበሮው ላይ ያለውን ገመድ ስንመለከት ይህንን እውነት እናስብበታለን።

●የከበሮው አፍ አንደኛው ሰፊ መሆኑ የመይመረመር ረቂቅ፣ ሰፊ፣ ምሉዕ በኩላኄ፣ በሁሉ ቦታ ያለ መለኮታዊ ባሕርይውን ሲያጠይቅ ሌላኛው ጠባብ መሆኑ በጠባብ ደረት በአጭር ቁመት የማይወሰነው መወሰኑን መወለዱን ያጠይቃል።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->የቅኔ ማሕሌት ንዋያተ ቅዱሳት (ጽናጽል)
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❼
2.3K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-02 22:21:17 https://t.me/Tewahdo_Haymanotie
2.0K views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 21:53:06 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#በቅዳሴና_በሌሎች_የጸሎት_ጊዜያት_የሚያገለግሉ_ንዋየ_ቅዱሳት
...
፲፫. ዣንጥላ፦ ከነጭ ወይም ወርቃማ ቀለም ካለው ይሠራል። ዘንጉ ከብረት፣ ከብር ይሠራል።
አገልግሎቱ፦ ታቦት ወደ አውደ ምሕረቱ ሲወጣ፣ ካህናቱ መሥዋዕቱን ለማክበር ወደ ቤተልሔም ሲወርዱ እና ከቤተልሔም ወደ ቤተ መቅደስ ሲመለሱ... ይጠቀሙበታል።

እስራኤላውያን በሲና ምድረ በዳ ሲጓዙ ይጋርዳቸው የነበረው ደመና እና ሙሴ ከእግዚአብሔር ጽላተ ኪዳኑን ሲቀበል የጋረደው ዳመና ምሳሌ ነው።

፲፬. ተቅዋመ ወርቅ (መቅረዝ)፦ የሚቆም ወይም የመንጠለጠል ባለ ብዙ አጽቅ የመብራት እቃ፣ የቀንዲል፣ የሻማ ማኖሪያ ነው።

፲፭. ድባብ፦ እንጨቶች እንደ እንደ ምሰሶ ቆመው በላዮ ጨርቅ በመስፋት የሚሠራ ትልቅ ጥላ ነው። ላዩ በነሐስ፣ በብር በመሳሰሉት ይሰራል። በክብር በዓላት ጊዜ ከፊት ተዘርግቶ ይሄዳል።

፲፮. መነሳንስ (ጭራ)፦ ከጻሕልና ከጽዋው ውስጥ ተሕዋስያን እንዳይገቡ ለመከላከያነት የሚያገለግል ነው።

፲፫. ምንጣፍ፦ በቤተ መቅደስ ውስጥ የሚነጠፍ ልብስ ነው። እስራኤላውያን እሽሆ እንዳይወጋቸው እንቅፋት እንዳይመታቸው እግዚአብሔር አምላክ ከእግራቸው በታች ያነጠፈላቸው ደመና ምሳሌ ነው።

ዝጋጃ/ምንጣፍ ከቤተ ምቅደስ ውጭ በቅድቱና በቅኔ ማሕሌቱም ይነጠፋል።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->የቅኔ ማሕሌት ንዋያተ ቅዱሳት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❻
2.3K views18:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 22:21:26 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#በቅዳሴና_በሌሎች_የጸሎት_ጊዜያት_የሚያገለግሉ_ንዋየ_ቅዱሳት
(ከትላንቱ የቀጠለ)
...
፰. ሙዳይ፦ ሙዳይ ማለት መኖሪያ፣ መጨመሪያ ማካተቻ ማለት ነው። ልዩ አገልግሎቱም የእጣን ማስቀመጫ/ማቅረቢያ ነው።

በሥርዓተ ቅዳሴ ጊዜ ካህኑ የመጀመሪያውን ቅዳሴና የሁለተኛውን ቅዳሴ ከመጀመሩ በፊት አምስት የእጣን ፍሬዎችን መርጦ ያስቀምጣል።

ሙዳዩ የእመቤታችን እጣኑ የጌታችን ምሳሌ ሲሆን አምስቱ እጣኖች የአምስቱ ኪዳናት ምሳሌ ናቸው።
አምስቱ ኪዳናት የሚባሉት፦ ኪዳነ/ቁርባነ አቤል፣ መሥዋዕተ ኖኅ፣ ኂሩተ አብርሃም፣ መብዐ ይስሐቅና ተልዕኮተ ሙሴ ወአሮን ናቸው።

፱. አትሮኖስ፦ ከእንጨትና ከብረት የሚሠራ መጽሐፍ ሲነበብ የሚዘረጋበት ነው። በቅዳሴ ጊዜ መጽሐፍትን ያነቡበታል። አትሮኖስ የእመቤታችን ምሳሌ ሲሆን መጽሐፉ ደግሞ የጌታችን ምሳሌ ነው።

፲. መሶበ ወርቅ፦ መሥዋዕቱን ወይም ኅብስተ ቁርባኑን ከቤተልሔም ወደ ቀራኒዮ ምትመስለው ቤተመቅደስ የሚወስዱበት ነው።

መሶበ ወርቅ ከስንደዶ፣ ከአክርማና ከአለላ፣ ከወርቅና ከብር ይሠራል።

መሶቡ የእመቤታችን ባለዩ ላይ ያለው መና የጌታችን ምሳሌ ነው።

፲፩. ቃጭል (ቃለ ዓዋዲ) መረዋ፦ በቅዳሴ ጊዜ የሚደወልና ድምጽ የሚሰጥ ነው። ከደወል ያነሰ ሲሆን ከብረት፣ ከመዳብ፣ ከብር፣ ከነሐስና ከመሳሰሉት ይሠራል።

የሚደወልበትም ጊዜ፦ ቀዳሲያን ከቤተልሔም ወደ ቤተ መቅደስ ሲገቡ (ፃዑ ንዑስ ክርስቲያን) ሲባል፤ በእግዚኦታ ጊዜ፤ ድርገት ሲወርዱ፤ በምሕላ ጊዜ ይመታል። በሰሞነ ሕማማት ጊዜም አገልግሎት ላይ ይውላል።

"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ" እያለ በምድረ በዳ ሲናገር የነበረው የመጥምቁ ዮሐንስ ስብከት እና ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በመስቀል ሥር ሆኖ የአለቀሰው ለቅሶ ምሳሌ ነው።

፲፪. መቁረርት ወይም ኩስኩስት፦ ቆረ ቀዘቀዘ ካለው የግእዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም ማብረጃ ማለት ነው። አገልግሎቱ ለምእመናን የቅዳሴ ጸበል ማደያ ነው። እንዲሁም በቅዳሴ ጊዜ ካህኑ እጁን የሚታጠብበት ቅዱስ ንዋይ ነው። በብሉይ ኪዳን ሙሴ እንዲሠራው ታዞ ነበር። (ዘጸ 30፥17)

ጲላጦስ "እኔ ከደሙ ንጹሕ ነኝ" ብሎ የታጠበበት እና ጌታችን በዕለተ ሐሙስ የደቀ መዛሙርቱን እግር ያጠበበት ምሳሌ ነው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->በቅዳሴና በሌሎች የጸሎት ጊዜያት የሚያገለግሉ ንዋየ ቅዱሳት...
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❺
2.3K views19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 18:56:50 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#በቅዳሴና_በሌሎች_የጸሎት_ጊዜያት_የሚያገለግሉ_ንዋየ_ቅዱሳት
(ከትላንቱ የቀጠለ)
...
፭. ዐውድ፦ በድርገት ጊዜ ጻሕሉ የሚቀመጥበት ሰፋ ያለ ትልቅ ሰሐን ነው። ሥጋው እንዳይነጥብ (እንዳይወድቅ) የሚያገለግል ሲሆን ከነሐስ፣ ከብረትና ከእንጨት ይሠራል።

ዐውድ ስሙ እንደሚያመለክተው አደባባይ ማለት ስለሆነ ጌታችን የተፈረደበት የጲላጦስ አደባባይ ምሳሌ ነው።

፮. አጎበር፦ አጎበር ማለት "ከፍ ያለ" ማለት ሲሆን በዐውዱ ላይ የሚደፋ አራት ማዕዘን ሦስት እግር ያለው እንጨት ወይም ብረት ሊሆን ይችላል። ይህም ሥጋውን ልብሱ እንዳይነካው ከፍ አድርጎ ልብሱን የሚይዝ ነው። እንዲሁም መጎናጸፊያውን ከፍ አድርጎ ክብሩን የሚገልጽ ነው።

፯. ጽንሐሕ፦ የዕጣን ማጠኛ ወይም ማሣረጊያ ማለት ነው። ከወርቅ፣ ከብር፣ ከብረትና ከነሐስ ሊሠራ ይችላል።

በኦሪት የወርቅ ማዕጠንት እንዲሠራ ለሙሴ እግዚአብሔር ያዘዘው ነው። (ዘጸ 30፥6-10) በዚህ ምሳሌ ዛሬ ድረስ ይሠራል።

የእመቤታችን ምሳሌ ነው። አጣኑ የትስብእት/የሥጋ፤ ፍሕሙ የመለኮት፣ የወርቅ ዘንጉ የመንፈስ ቅዱስ፤ ምሳሌ ነው።

የጽንሐሕ የተለያዩ ክፍሎችና ምሳሌያዊ ትርጉማቸው፦
1, ሙዳይ የሚመስለው የጽንሐሕው ክፍል፦ እጣንና እሳቱ የሚዋህዱበት ክፍል ነው። ክዳን ከበላዩ አለው። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ማኅጸን ምሳሌ ነው። እሳቱ በዚህ ክፍል ተቀምጦ ጽንሐሕውን እንደማያቃጥለው ሁሉ እመቤታችንም እሳተ መለኮቱን በማኅጸንዋ ተሸክማው አላቃጠላትም።

2, የሙዳዩ መክደኛ፦ በክዳኑ በላይ መስቀል አለበት ይህም የቀራኒዮ ምሳሌ ነው።
3, በመካከል የሚገኝ አንድ ዘንግ፦ በሦስቱ ዘንጎች መካከል የሚገኝ አንድ ዘንግ አለ። የቅድስት ሥላሴ አንድነታቸው ምሳሌ ነው።
4, ሽኩራዎችን የያዙ ሦስት ዘንግ፦ እግዚአብሔር በመለኮት፣ በሕልውና፣ በአገዛዝ አንድ ቢሆንም በስም፣ በግብርና በአካል ሦስት መሆኑን የሚያመለክቱ ናቸው።
የመካከለኛውን ዘንግ አይተን አንድነቱን ስናስብ በዳር ያሉትን ሦስት ዘንጎች ተመልክተን ሦስትነቱን እናስባለን።
5, በዘንጎቹ ላይ የሚገኙት ሽኩራዎች፦ በቁጥር 12 ወይም 24 መሆን አለባቸው። 12 ከሆኑ የአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት፤ 24 ከሆኑ የሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ምሳሌ ናቸው።
ጽንሐሕው ሲወዛወዝ የሚያወጣው ድምጽ የሐዋርያት ስብከት ምሳሌ ነው። ወይም የ24 ሰማያውያን ካህናት ምስጋና ምሳሌ ነው። (ራእ 4፥7)
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->በቅዳሴና በሌሎች የጸሎት ጊዜያት የሚያገለግሉ ንዋየ ቅዱሳት...
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❹❹
2.2K views15:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:44:59 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#በቅዳሴና_በሌሎች_የጸሎት_ጊዜያት_የሚያገለግሉ_ንዋየ_ቅዱሳት
፩. መንበረ ታቦት፦ የጽላት ወይም የታቦት መቀመጫ ዙፋን ነው። መሥዋዕተ ኦሪቱ ይሠዋበት በነበረው ፈንታ በመንበሩ የገባ ስለሆነ ከታቦቱ ጋር "መሥዋዕ" ይለዋል። ትርጉሙም መሠዊያ ማለት ነው።

፪. ጻሕል፦ ጻሕል ከላይ እንደገለጽነው የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክረስቶስ ቅዱስ ሥጋው ማስቀመጫና ማቅረቢያ ነው። ይኸውም ከወርቅ፣ ከብር፣ ከነሐስና ከብረት ሊሠራ ይችላል።

የተለየ ቅርጽ የተለየ ምልክት ያለው ሲሆን ክረስቶስ የተወለደበትን በረት እና የታዘለበትን የእመቤታችንን ጀርባ ያመለክታል።

፫. ጽዋዕ፦ ጽዋዕ የኢየሱስ ክረስቶስ ክቡር ደም የሚቀርብበት ንዋየ ቅዱስ ነው። ይህም ከወርቅ፣ ከመዳብ፣ ከብር፣ ከነሐስ፣ ከብረት፣ ይሠራል።

ምሳሌነቱ፦ በዕለተ ሐሙስ "ይህ ደሜ ነውና ሁላችሁ ጠጡት" ብሎ የሰጠበትን ጽዋዕ የሚያስታውስ ነው። (ማቴ 26፥27)

ሌንጌኖስ በጦር ጎኑን በወጋበት ጊዜ የፈሰሰውን ውሃና ደም እና የተደባለቀውንም ፈሳሽ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤል በጽዋ ብርሃን ተቀብሎ ዓለምን የረጨበት ጽዋዕ ምሳሌ በማድረግ ነው።

ዛሬም ዲያቆናቱ በጦር በተመሠለው እረፈ መስቀል ለምዕመናኑ ደሙን ያቀብሉበታል።

ጽዋው የሚሸፈንበት ልብስ አይሁድ ጌታችንን በኩርኩምና በጥፊ ሲመቱት ዓይኑን የሸፈኑበትና ያሰሩበት ጨርቅ ምሳሌ ነው።

፬. ዕርፈ መስቀል፦ ዕርፈ መስቀል የሚባለው እንደ ማንኪያ ያለ ሆኖ ከበስተ ኋላው የመስቀል ቅርጽ ያለው ለክቡር ደሙ ማቀበያነት የሚያገለግል ነው።

እሄ በእጅ ማያዣው በኩል መስቀል የሆነ ጎድጓዳ ማንኪያ ሚመስል ንዋየ ቅዱስ የሚሠራው ጽዋዕ ከሚሠራባቸው ነው።

ምሳሌነቱም የሱራፊ ጉጠት ነው። ኢሳይያስን ከለምጽ ያዳነበት ነውና ዛሬም እኛ ከኃጢአት በሽታ የምንድንበትን የክርስቶስን ክቡር ደም እንቀበልበታለን። (ኢሳ 6፥6-8)
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->በቅዳሴና በሌሎች የጸሎት ጊዜያት የሚያገለግሉ ንዋየ ቅዱሳት...
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹➌
2.1K views18:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 22:37:28 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#አልባሳት
...
፫. ማኅፈድ፦ ማኅፈድ ማለት መሸፈኛ ማለት ነው። ብዙውን ጊዜ ከጥቁር ጨርቅ የሚሠሩ ናቸው። በቅዳሴ ጊዜ የሚቀርቡ ማኅፈዳት ወይም መሸፈኛዎች አምስት ናቸው።
◆አንደኛው በጻሕሉ ሥር በታቦቱ ላይ ይነጠፋል። ጻሕል ማለት የክረስቶስን ሥጋ ማቅረቢያ ነው።
◆ሁለተኛው በጻሕሉ ላይ ይነጠፋል። ሕብስቱ የሚጠቀለልበት ነው።
◆ሦስተኛው የመሥዋዕቱ ልብስ ነው። ቁመቱ ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ ሁኖ ይለብሳል።
◆አራተኛው ከሰሜን ወደ ደቡብ ሆኖ ይለብሳል።
◆አምስተኛው ከመስዕ (ሰሜን ምሥራቃዊ) ወደ አዜብ (ደቡብ ምዕራብ) ሆኖ ይለብሳል።

ክርስቶስ በበረት ሲወለድ በጨርቅ መጠቅለሉንና በበለስ ቅጠል መሸፈኑን የሚያስታውስ በተለይም ዮሴፍና ኒቆዲሞስ በድርብ በፍታ የገነዙትን የሚያመለክት ምሳሌ ነው።

፬. መንጦላዕት፦ በሦስቱም የመቅደስ በር የሚጋረዱ መጋረጃዎች ናቸው። ለመቅደሱ ክብርን የሚሰጡ ናቸው። መጋረጃዎቹ የሚከፈቱበትና የሚዘጉበት ጊዜ አለ።

● በመጀመሪያ ቅዳሴ "አእኑየ" ከሚለው ምዕዳን ጀምሮ እስከ "ሚመጠን" ሚለው ድረስ ይዘጋል።
● "ስገዱ" ተብሎ ከታወጀ እና "ፍትሐት ዘወልድ" ፣ "በእን ቅዱሳት" ሲጸለይ ጀምሮ እስከ ፍሬ ቅዳሴ ድረስ ይከፈታል።
● ከፍሬ ቅዳሴ እስከ ሦስተኛው "ጸሎተ ፈትቶ" ማለትም "አርህው ኖኅተ መኳንንት" ብሎ ንፍቁ ዲያቆን ማሳሰቢያ እስከ ሚሰጥ ድረስ ይዘጋል።
●"አርህው ኖኅተ መኳንንት" በሚል ጊዜ ግን ይከፈታል።
●በቁርባን ጊዜ ደግሞ ይዘጋል።

፭. ልብሰ ታቦት (መጎናጸፊያ)፦ ይህ ለአክብሮተ ሥጋውና ደሙ በቅዳሴ ጊዜ መንበሩ ወይም መሠዊያው የሚለብሰው ወይም ታቦት በወጣ ጊዜ የሚለብሰው ነው። ስለዚህ መጎናጸፊያ ይባላል።

፮. ቀጸላ፦ ለታቦቱ ክብር ከመጎናጸፊያው በላይ የሚደረብ ባለ ዘርፍ ልብስ ነው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->በቅዳሴና በሌሎች የጸሎት ጊዜያት የሚያገለግሉ ንዋየ ቅዱሳት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❷
2.2K viewsedited  19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-26 22:53:27 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#አልባሳት
፩. የቀሳውስት ልብስ
“አሮንንና ልጆቹንም ወደ መገናኛው ድንኳን ደጃፍ አቅርበህ በውኃ ታጥባቸዋለህ። የተቀደሰውንም ልብስ አሮንን ታለብሰዋለህ፤ በክህነትም ያገለግለኝ ዘንድ ቀብተህ ትቀድሰዋለህ። ልጆቹንም አቅርበህ ሸሚዞችን ታለብሳቸዋለህ፤ በክህነትም ያገለግሉኝ ዘንድ አባታቸውን እንደ ቀባህ ትቀባቸዋለህ፤ መቀባታቸውም ለልጅ ልጃቸው ለዘላለም ክህነት ይሆንላቸዋል።” (ዘጸ 40፥12-15) በተባለው የእግዚአብሔር ቃል መሠረት የክህነት አልባሳት ለእግዚአብሔር የተለዩ አገልግሎታቸውም ልዩ ነው።

እንዲሁም በዘጸ 39፥1 - ፍጻሜው “እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው በመቅደሱ ለማገልገል ከሰማያዊ፣ ከሐምራዊም፣ ከቀይ ግምጃም በብልሃት የተሠራ ልብስ ለአሮንም የተቀደሰውን ልብስ አደረጉ። እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው ኤፉዱን ከወርቅ ከሰማያዊም ከሐምራዊም ከቀይ ግምጃም ከተፈተለም ከጥሩ በፍታ አደረገ። ወርቁንም ቀጥቅጠው እንደ ቅጠል ስስ አድርገው እንደ ፈትል ቈረጡ። ብልህ ሠራተኛም እንደሚሠራ ሰማያዊ ሐምራዊም ቀይም ግምጃ የተፈተለም ጥሩ በፍታ ከእርሱ ጠለፉ። ሁለቱ ወገን እንዲጋጠም በሁለቱ ጫንቃዎች ላይ የሚጋጠም ልብስ አደረጉት። በላዩም መታጠቂያ ሆኖ በብልሃት የተጠለፈው የኤፉዱ ቋድ እንደ እርሱ ከእርሱም ጋር አንድ ነበረ ከወርቅና ከሰማያዊ ከሐምራዊ ከቀይ ግምጃም ከተፈተለም ከጥሩ በፍታ የተሠራ ነበረ። እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው፥ በወርቅ ፈርጥ የተያዙ የመረግድ ድንጋዮች ሠርተው እንደ ማኅተም ቅርጽ የእስራኤልን ልጆች ስም ቀረጹባቸው።... በቀሚሱም ታችኛ ዘርፍ ከሰማያዊ ከሐምራዊም ከቀይም ግምጃ፥ ከተፈተለ በፍታም ሮማኖች አደረጉ።" ይላልና በትውፊትና በምሳሌ ዛሬም ቀሳውስትና ዲያቆናት የሚለብሱት ልብሰ ተክህኖ አለ። እነዚህንም እንደሚከተለው እንመለከታለን።

ቀሚስ፦ በጥንት ዘመን አብደላከኒ የሚባል የካህናት ቀሚስ ነበር አሁን ግን ጌጥነት ካላቸው ጨርቆች የሚሠራ ነው።

በመጀመሪያ የሚለበስ ልብስ ነው። በልክ እንዲሆን የታዘዘ ሲሆን ከረዘመ ማሳጠሪያ፤ ሰውነትን ማጠናከሪያ የሚሆን መታጠቂያ አለው።

ካባ ላንቃ፦ መደረቢያው ልብስ ካባ ላንቃ ይባላል። ከካባው ጋር ለምድ አብሮ ተሰፍቶ ስለሚገኝ ነው "ካባ ላንቃ" የተባለው። የለምዱ እግር ወይም ዘርፍ በየቦታው እንደ ላንቃ ስለሚወርድ ካባ ላንቃ ተባለ።

ልዩ ልዩ ቀለማት ካላቸው ጨርቆች የሚሠራ ነው። ወርቅና ሐሩ አብሮ ተፈትሎ ከተሠራ ጨርቅ ሊሠራ ይችላል።

ሞጣሕት፦ በአንገት ተጠልቆ ፊት ለፊት የሚወርድ የደረት ልብስ ነው። ይህም በኦሪቴ ኤፉድ የሚባለው የአሮን ልብስ አምሳል ነው። ካባ ላንቃ በተሠራበት መንገድ የሚሠራ ይሆናል።

ቆብ ወይም ቀጸላ/ሕባኔ፦ በሥርዓተ ቅዳሴ ጊዜ ካህኑ ወይም ቄሱ በራሱ ላይ ደፍቶ የሚገባው ነው።


፪. የዲያቆናት ልብስ
ቀሚስ፦ ጌጥነት ካላቸው ጨርቆች የሚሠራ ነው። በመጀመሪያ የሚለበስ ልብስ ነው። በልክ እንዲሆን የታዘዘ ሲሆን ከረዘመ ማሳጠሪያ፤ ሰውነትን ማጠናከሪያ የሚሆን መታጠቂያ አለው።

ለምድ ላንቃ፦ በቀድሞ ዘመን ለምድ ለብቻ ቀሚስ ለብቻ ይዘጋጅ ነበር። አሁን ግን ለምዱ ከቀሚሱ ጋር አብሮ ይሠፋል።

ከፋይ ድግድጋት፦ ከግብጽ ቤተክርስቲያን የተወሰደ ሲሆን ዲያቆናት አንዳንድ ጊዜ ለምድና ቀሚስ በመልበስ ፈንታ ቀሚስ ብቻ ለብሰው በከፋይ መታጠቂያ በመስቀለኛ ቅርጽ ስለሚታጠቁና ስለሚያደገድጉ ከፋይ ድግድጋት ይባላል።

በአሁን ጊዜ ዲያቆናቱ እየተውት ሰንበት ተማሪዎች ሲጠቀሙት ይታያል።

አክሊል ወይም ቆብ፦ በሥርዓተ ቅዳሴ ጊዜ ዲያቆን አክሊል ወይም ቆብ አድርጎ ይቀድሳል።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ማኅፈዳት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❶
2.3K views19:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-25 22:46:54 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#በቤተ_መቅደስ_ውስጥ_ለአገልግሎት_የሚውሉ_ንዋያተ_ቅዱሳት
...
፫. ማኅቶተ ቤተ ከርስቲያን/ የቤተክርስቲያን መብራት

ማኅቶት ማለት ብርሃን፣ መብራት ማለት ነው። በቀድሞ ጊዜ ለሙሴ ሥርዓት አድርጎ ሰጥቶታል። (ዘጸ ፵፥፪-፬) “እግዚአብሔርም ሙሴን እንዳዘዘው መቅረዙን በመገናኛው ድንኳን ውስጥ፥ በገበታው ፊት ለፊት፥ በማደሪያው በደቡብ በኩል አኖረ።” (፵፥፳፬...) መቅረዝ ማለት ሻማ ማለት ነው።

በአሁኑ የቤተ ክረስቲያን ሥርዓት ጡዋፍና ዘይት ነው (ፍት አንቀጽ 1) ዘይቱ የወይራ ዘይት ነው። ይህም ቀንዲል ይባላል ቃሉ የላቲን ሲሆን መብራት ማለት ነው።

በቤተ ክርስቲያናችን ብዙ መብራት እንዲበራ ታዙዋል።
በተለይ ቅዱሳት መጽሐፍት ማለትም የጳውሎስ መልእክታት፣ የሐዋርያት መልእክታት፣ ግብረ ሐዋርያት ሲነበቡ ቤተክርስቲያኑ በጣም የበራ እንዲሆን ታዟል። ይልቁንም ወንጌል ሲነበብ እጅግ በጣም መብራት ማብዛት እንደሚገባ ተሠርቶአል። (ፍት አንቀጽ ፩)
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->አልባሳት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹⓪
2.2K views19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ