Get Mystery Box with random crypto!

የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የሰርጥ አድራሻ: @tewahdo_haymanotie
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.40K
የሰርጥ መግለጫ

✍️"አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች ❹፥➎)✅
✍️ጥንታዊቷንና እውነተኛዋን ሃይማኖት ለመማር ከ1️⃣ኛ ዓመት ጀምሮ ኮርሶች እየተሰጡበት ያለ የእግዚአብሔር ቤት ነው።
✍️የማንኛውም ሃይማኖት ተከታይ ገብቶ መማር ይችላል። 🌹ቅድሚያ ለነፍስዎ ይኑሩ!🌹
ኮርሶች👇
t.me/Tewahdo_Haymanotie/703
አገልጋዮችን ለማግኘት
@Dingl_Ruhruhitu_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-21 23:42:23 @Tewahdo_Haymanotie
1.8K viewsedited  20:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 05:05:44 https://telegra.ph/%E1%88%9D%E1%88%B5%E1%8C%A2%E1%88%A8-%E1%89%81%E1%88%AD%E1%89%A3%E1%8A%95-08-20

የ2014 ዓም ኮርሶችን በዚህ ዓመት ለማጠናቀቅ ሲባል በአንድ ገፅ ብዙ ትምህርቶችን መልቀቅ ስለስገደደን Instant view ሚለውን በመንካት ሚለቀቁትን ትምህርቶች በሚገባ አንብባችሁ ሚለቀቁትን የመወዳደሪያ ጥያቄዎች እንድትመልሱ። መልካም ቀን

ገፅ ❾⓪
2.0K viewsedited  02:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-19 22:04:40 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#ቅብዐ_ሜሮን-የሚያስገኘው_ጸጋ
አካሉ አንድ ሲሆን ስጦታው ልዩ ልዩ የሆነ መንፈስ ቅዱስ (፩ቆሮ. ፲፪፥፬)

ምእመናንን ለልዩ ልዩ አገልግሎት የሚያዘጋጃቸው፣ የሚሰጠውን ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና
የሚያጸናው በዚሁ ዕለት በሜሮን አማካኝነት በሚቀበሉት (በሚያድርባቸው) የመንፈስ ቅዱስ
ጸጋ ነው። (፩ኛ ቆሮ ፲፪፥፳፯-ፍጻ) (ሐዋ ፰፥፲፬-፲፰)

አዲሱ ተጠማቂ የቤተ ክርስቲያን ልጅ፣ የእግዚአብሔር ማደሪያ ስለሚሆንም ለተፈጠረበት ዓላማ የሚሠራ ሆኖ ይዘጋጃል፡፡

የክርስቶስ አካልነቱ የቤተ ክርስቲያንም አባልነቱ የተረጋገጠ ክርስቲያን ይሆናል፡፡

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ሥጋችሁም ለእግዚአብሔር ነው እንጂ ለዝሙት አይደለም፤ እግዚአብሔርም ለሥጋችሁ ነው። ሥጋችሁ የክርስቶስ አካል እንደሆነ አታውቁምን? እንግዲህ የክርስቶስን አካል ወስዳችሁ የአመንዝራ አካል ታደርጉታላችሁን? አይገባም፡፡ ከአመንዝራ ጋር የተገናኘ ከእርስዋ ጋር አንድ አካል እንዲሆን አታውቁምን? መጽሐፍ፣ ‛ሁለቱ አንድ አካል ይሆናሉ’ ብሎአልና፡፡ ከእግዚአብሔር ጋር የተዋሐደ ግን ከእርሱ ጋር አንድ መንፈስ ይሆናል፡፡ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር ለተቀበላችሁት በእናንተ አድሮ ላለ ለመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደሆነ አታውቁምን? ለራሳችሁ አይደላችሁም፡፡ በዋጋ ተገዝታችኋልና፤ ስለዚህም እግዚአብሔርን በሥጋችሁ አክብሩት፡፡” (፩ቆሮ. ፮፥፲፫-ፍጻ)

በማለት ያስተማረን ይህን የሚያጎላና ሌሎች ምሥጢራትንም አካቶ የያዘ ነው።

ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ተወልደን የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስ መሆን የጀመርነው ከተጠመቅንበትና በሜሮን ከከበርንበት ዕለትና ሰዓት ጀምሮ የእግዚአብሔርን የክብር ዕቃ፣ ማደሪያ መቅደሱንም በጥንቃቄ የማይዙና የሚያቃልሉ ሁሉ የሚቀጡ መሆኑን ማወቅ ያስፈልጋል።

የመቅደሱ ባለቤት እግዚአብሔር ለቤቱና ለሥርዓቱ ቀናዒ ነው።

መቅደሱ የኃጢአት ሸቀጥ ማራገፊያና መነገጃ ሲሆን ዝም ብሎ አያይም። (ማቴ. ፳፩፥፲፪-፲፰)

ንጉሡ ብልጣሶር አባቱ ናቡከዳናፆር ከኢየሩሳሌም ቤተ መቅደስ ማርኮ በቤተ መንግሥቱ ዕቃ ቤት በክብር ያኖራቸውን ንዋያተ ቅድሳት አስመጥቶ በማቃለል ጣዖታትን እያመለኩ እንዲበሉባቸውና እንዲጠጡባቸው አደረገ፡፡

እንዲህ አድርጎ በንዋየ ቅድሳቱ በተሳለቀባቸው ዕለትም ተገድሎ አደረ። (ዳን. ፭፥፩-ፍጻሜው) እግዚአብሔርንና የሱ የሆኑትን ሁሉ የማያከብሩ ሰዎች ለማይገባ አዕምሮ ተላልፈው እንደሚሰጡ ማወቅ ጠቃሚ ነው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ምሥጢረ ቁርባን
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽➒
1.8K views19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 21:25:25 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#የቅብዐ_ሜሮን_አፈጻጸም
ቅብዐ ሜሮን በዋነኛ ምሥጢራዊ አገልግሎቱ ከምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም አይለይም።

በእኛ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ከላይ እንደገለጥነው የሜሮን አቀባብ ወዲያ ከጥምቀት አያይዞ ይፈጸማል።

ይህም ማለት ተጠማቂው ሰው ጥምቀት ከተፈጸመለት በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ጥምቀቱን እንደተቀበለ ሜሮን ይቀባል።

ሜሮን ሲቀባም በመንፈስ ቅዱስ መጠመቁን፣ ከውኃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለዱንን፣ መንፈስ ቅዱስን እንዳደረበት ይረጋገጥለታል፤ ተጠማቂው ተጠምቆ ሜሮን መቀባቱ መንፈስ ቅዱስን መቀበሉን ያመለክታል፡፡

የአቀባቡም ሥርዓት የተጠመቀው ሕጻን እንደኾነ በክርስትና ዋሱ እቅፍ እንዳለ ይቀባል። አዋቂ እንደኾነ ከማጥመቂያው ወጥቶ እንደቆመ ቄሱ ሜሮኑን በአውራ ጣቱ እየጠለፈ “እቀብአከ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያለ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም በትዕምርተ መስቀለ ያትመዋል በመጀመሪያ ግንባሩን ያትመዋል አዕምሮው የተባረከ እንዲኾን ግራ ቀኝ አይኖቹን ያትመዋል ዓይኖቹ የእግዚአብሔርን እውነት እንዲያዩ፣ ግራ ቀኝ ጆሮቹን ያትመዋል ጆሮዎቹ የእዚአብሔርን ቃል እንዲሰሙ፣ አፉን ከናፍሩን ያትመዋል፣ እውነት እንዲናገር የእግዚአብሔርን ጥበብ እንዲማር፣ ደረቱን ያትመዋል፡፡ ልቡ ቅን እንዲያስብ፣ ግራ ቀኝ እጆቹን ይቀባዋል፡፡

እጆቹ ለመልካም ሥራ እንዲፋጠኑ፣
ግራ ቀኝ እግሮቹን ይቀባዋል እግሮቹ ወደ መልካም ሥራ እንዲፋጠኑ።

በአጠቃላይ መላ ሰውነቱን ይቀባዋል በኋላ ሰውነቱ የእግዚአብሔር ማደሪያ እንዲሆን።

በሜሮን የሚታተሙ በሜሮን የሚቀደሱ አዲስ ክርስቲያኖች ብቻ አይደሉም፡፡ አዲስ ቤተ ክርስቲያን ተሰርቶ ካለቀ በኋላ አገልግሎት የሚጀመርበት በሜሮን ከተቀባ በኋላ ነው፡፡

የቤተ ክርስቲያን የውስጥ ንዋያተ ታቦት፣ ጻህል፣ ጽዋ፣ ዕርፈ መስቀል፣ መሶበ ወርቅ፣ ማዕጠንት፣ ማህፈድ፣ መንበር፣ እነዚህና የመሳሰሉትም ለአገልግሎት ከመቅረባቸው በፊት በሜሮን ይታተማሉ ልዩ ጸሎትና ቡራኬም ይፈጸምባቸዋል ከዚያ በኋላ ተራ ሥራ አይሰራባቸውም፡፡

በግሪክና በሌሎች መለካውያን አቀባቡ ከእኛው ጋር ተመሳሳይነት አለው ከጥምቀት ጋር አያይዘው ይቀባሉ ሲቀቡ ግን “ማህተመ ፀጋ ዘመንፈስ ቅዱስ ዝውእቱ” እያሉ ነው። የሚቀባው ቄሱ ነው።

በዚህም መሠረት በእኛ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት የተወሰኑትን የአቀባብ ሥርዓቶች ከዚህ በታች እንመልከት።

በዕለተ ጥምቀት ሜሮን በጳጳሳት ከተባረከ በኋላ ለአገልግሎት የተሰየመው ቄስ በእጁ ይዞ ይጸልይበታል።

መጽሐፈ ክርስትናንም ይደግማል (ያነባል)። የተጠማቂውን ፴፮ ሕዋሳት በታዘዘው መሠረት ክፍል ክፍሉን እየለየ ይቀባል።

ቅብዐ ሜሮኑን በአውራ ጣቱ እየጠቀሰ (እያስነካ) በትእምርተ መስቀል አምሳል
እቀብዐከ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ እያለ ተጠማቂውን ይቀባዋል፡፡
በሥርዓተ ጥምቀት እንደገለጽነው ንዑሰ ክርስቲያን ሴት ከሆነች ልብስ ለብሳ
ከአንገቷ በላይ ኤጲስ ቆጶሱ (ቄሱ) ይቀባታል፡፡ በኋላም ከአንገት በታች ያሉትን ቀሪ ሕዋሳት ጳጳሱ ወይም ቄሱ ተጋርዶ (ተሸፍኖ) ዲያቆናዊት የቄሱን እጅ ይዛ እየመራች ይቀባታል፡፡

የተጠማቂው ፴፮ቱ ሕዋሳት በሜሮን ሲከብሩ በሥርዓተ ቤተክርስቲያን
የአቀባባቸው ቅደም ተከተል የታወቀ ነው፡፡

ከላይ እንደገለጽነው ሁሉም በትእምርተ መስቀል አምሳል የሚታተሙ (የሚቀቡ) ናቸው።
ግንባሩን ግራና ቀኝ ሁለት ቦታ ይቀባና በፊቱ ላይ እፍ ይገልበታል..........1
ሁለቱን የአፍንጫ በሮች፣ …........2
ሁለቱን ከናፍር፣ ……………………...2
ሁለቱን ጆሮዎች፣ ……………....2
ሁለቱን ዓይኖች፣ ……………….2
ደረቱን፣.………………………….....1
ልቡን፣ ……………..………………….1
ከመሐል አናት እስከ ወገብ ያለውን አካል፣ ………….1
መሐል ጀርባውን፣……………….1
እንብርቱን፣ ……………………….1
ሁለቱን እጆች፣ ……………….….2
የእጆቹን መገናኛዎች፣………....2
ትከሻዎቹን፣……………………….2
ማጅራቱን፣…..…………………….1
አንገቱን፣ …………………...……1
ክርኖቹን፣ …………..….….….2
የእጆቹን ውጪያዊ ክፍሎች (መዳፎች)፣ ……………....………2
የእጆቹን ውስጣዊ ክፍሎች (መዳፎች)፣ ………………...2
የእግር መገናኛዎቹን (መዳፎች)፣ …………..…2
ጉልበቶቹን፣ …………...………….2
የእግሮቹን ውጪያዊ ክፍሎች (ጣቶች)፣ ………….…….….2
የእግሮቹን ውስጣዊ ክፍሎች (ጣቶች)፣ ………....……...…2
በድምሩ 36 ሕዋሳት ይሆናሉ፡፡

እነዚህን ሕዋሳት በቅደም ተከተል ከቀባ በኋላ በተጠማቂው ላይ እጁን ጭኖ “በሰማያውያን በረከት የተባረክህ ሁን” እያለ ይባርከዋል፡፡

ሠላሳ ስድስቱ የተጠማቂው ሕዋሳት በዚህ መልክ በቅብዐ ማሮን ታትመው የእግዚአብሔር ገንዘቦች (ማደሪያዎች) ይሆናሉ፡፡ ከተጠማቂዎች ሌላ ቅብዐ ሜሮን ለሁለት ምሥጢራት ማክበሪያነት (ማተሚያነት) ያገለግላል። እነዚህም ምሥጢረ ክህነትና ምሥጢረ ተክሊል ናቸው።

በምሥጢረ ክህነት ካህናት ከቄሱ ጀምሮ ወደ ላይ ያሉት ማለትም ጳጳስና ቄስ በቅብዐ ሜሮን ከብረው ካህናተ እግዚአብሔር ይሆናሉ።

ይህም በብሉይ ኪዳን “እኔንም በክህነት እንዲያገለግሉኝ ትቀድሳቸው ዘንድ የምታደርግላቸው ነገር ይህ ነው፤ የቅብዐትንም ዘይት ወስደህ በራሱ ላይ ታፈሰዋለህ፤ ትቀባውማለህ፡፡

ልጆቹንም ታቆርባቸዋለህ፤ ቀሚሶችንም ታለብሳቸዋለህ፤ በመታጠቂያም ታስታጥቃቸዋለህ፤ ቆብንም ታደርግላቸዋለህ፤ ለዘለዓለም ሥርዓትም ክህነት ይሆንላቸዋል፡፡ እንዲሁም የአሮንና የልጆቹን እጆች ትቀባቸዋለህ፡፡
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ቅብዐ ሜሮን የሚያስገኘው ጸጋ
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽❽
1.9K viewsedited  18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 21:14:37 # አስተምህሮ
የሐዲስ ኪዳን ሥርዓተ ሜሮን መነሻውና ምሳሌው የብሉይ ኪዳን ቅብዓ ዘይት ነው።
የሐዲስ ኪዳኑ ቅብዓ ሜሮን መነሻው ከላይ እንደገለጽነው ይህ የብሉይ ኪዳኑ ቅብዓ ዘይት አጠቃቀምና አገልግሎት ነው።

ፈቅዶና መመሪያ ስጥቶ ያስጀመረውም ራሱ እግዚአብሔር ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በሐዲስ ኪዳን በቅብዐ ሜሮን የሚታደለውን የመንፈስ ቅዱስ ስጦታ ሲያብራራ እንዲህ ይላል "እናንተስ ከቅዱሱ ያገኛችሁት ቅብዐት ቅባት አላችሁ፣ ሁሉንም ታውቃላችሁ ። እውነትን የምታውቁ ስለሆናችሁ፣ ውሸት ሁሉ ከእውነት እንዳልሆነ ስለምታውቁ እንጂ እውነትን እደምታውቁ አድርጌ አልጸፍላችሁም።" ( ፩ ዮሗ 2÷20-22።) በማለት አሰተምሮናል።

ሐዋርያው ቅዱስ ጰውሎስል እንዲህ በሎናል '' ከእናንተ ጋር በክርሰቶስ ስም የሚያጸናንና የቀባን እግዚአብሔር ነው።
ደግሞም ያተመንና የመንፈስ ቅዱስን ፈለማ በልቡናችን የሰጠን እርሱ ነው። (፪ ቆሮ. 1÷21-23።)

የቅብዓ ሜሮን አገልግሎት የሚውለው ለአንድ አይነት ተግባር ብቻ አይደለም ። በብሉይ ኪዳን እዳየነው ሁሉ በአዲስ ኪዳንም ቅብዓ ሜሮን ሦስት አይነት አገልግሎቶች አሉት።
➲እነዚህም

፩ኛ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል ፦ አዲስ አማንያን (ተጠማቂዎች) ከተጠመቁ በሗላ በሜሮን ተቀብተውና ከብረው ሀብተ መንፈስ ቅዱስ እዲያድርባቸው ያደርጋል።

፪ኛ የእግዚአብሔር አገልጋዮች (ካህናትን) ለመሾም ፦ ካህናት አባቶች የእግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያን ወይም ህዝብ ለማገልገልየሚችሉበት ስልጣን (ሹመት)፣ ማስተዋል (ጥበብ)፣ ኃይል (ብርታት)፣ ትግስትና ጸናት የሚያጎናጽፋቸውን ጸጋ መንፈስ ቅዱስ ለመቀበል እንዲችሉ በሚሾሙበት ጊዜ በሜሮን ይቀባሉ (ይከብራላ)።

፫ኛ ለአዲስ ህንፃ ቤተ ክርስቲያንና ለንዋየ ቅድሳት ማክበርያ፦ አዲስ ህንፃ ቤተ ክርስቲያንና ንዋየ ቅድሳቱ የእግዚአብሔር ገንዘቦች እዲሆኑ በሜሮን ተቀብተው እዲከብሩ ይደረጋል።

◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈◈
የተዋህዶ ቤተሰቦች ኮርስ መስጫ
"አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች ❹፥➎)

@Dingl_Ruhruhitu_bot
https://t.me/Tewahdo_Haymanotie
ገፅ ➑❾
2.2K views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 11:48:36 3.2 ምሥጢረ ሜሮን
ምሥጢረ ሜሮን ከምሥጢረ ጥምቀት ቀጥሎ ወዲያውኑ የሚፈጸም ማህተም መንፈስ ቅዱስ ነው። በተጨማሪም የአጠቃቀም ሥርዓቱና ጸሎቱ የተለየ ሆኖ ቅብዓ ሜሮን ለምሥጢረ ክህነትና ለምሥጢረ ተክሊል ማክበሪያነት ያገለግላል።
ገፅ ➑➑
2.0K views08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 22:27:48 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
፫.፪ #ምሥጢረ_ሜሮን
ሜሮን ቃሉ የጽርዕ ነው። ሜሮን ማለት ቅባት ማለት ነው። ይህም ሽታው የሚጣፍጥ፣ ልብ የሚመስጥ፣ መዓዛ ያለው ቅዱስ ቅባት ነው። መልኩ ዘይት ይመስላል። ይህም መልካም መዓዛ ከሚሰጡ ዘይትነት ከአላቸው እፅዋት ተነጥሮ የሚወጣ ቅብዕ ነው። ሲሠራ በፓትርያርክና በጳጳሳት ጸሎት ይባረካል፤ ይከብራል።

ከብዙ እፅዋት እየተቀመመ በማንጠር እስከ አሁን እየተሠራ መጥተዋል። (ዮሐ 2፥27)

ምሥጢረ ሜሮን ከጥምቀት ጋር ተያይዞ ከጥምቀት ቀጥሎ የሚፈጸም፤ መንፈስ ቅዱስን የሚያሳድር፤ በመንፈስ ቅዱስ መጠመቃችንን፤ ከውሃና ከመንፈስ ቅዱስ መወለዳችንን የሚያረጋግጥልን ታላቅ ምሥጢር ነው።

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ፤ በእደ ዮሐንስ ተጠምቆ ሲወጣ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል ወርዶ በራሱ ላይ ባረፈ ጊዜ የአብ የባሕርይ ልጅነቱ በባሕርይ አባቱ ምስክርነት ተረጋግጧል። እንደዚሁም ሁሉ አማኞች ተጠምቀው ሲወጡ በቅዱስ ቅብዐት በሜሮን ከብረው የጸጋ ልጅነት ማግኘታቸው ይረጋገጣል። ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ፣ ከማኅጸነ ዮርዳኖስ መወለዳቸው ይታወቃል።

#አመሠራረት
ምሥጢረ ሜሮንን የመሠረተልን ራሱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክረስቶስ ነው።

አስቀድሞ በብሉይ ኪዳን ምሳሌ ሲመሰልለት የነበረ በኋላም በሐዲስ ኪዳን ሐዋርያት አበው የደነገጉትና ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ከዘመናችን ያደረሱት ምሥጢር ነው።

መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ “እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸከም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይልቅ ይበረታል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ በእሳትም ያጠምቃችኋል፤” (ማቴ 3፥11) በማለት እንደመሰከረለት በመንፈስ ቅዱስና በእሳት የሚያጠምቅ እርሱ መድኃኒዓለም ክርስቶስ ብቻ ነው።

ለሐዋርያትም ተስፋ እንዳረገላቸው በበዓለ ሃምሳ ከአብ የሠረፀ መንፈስ ቅዱስን ላከላቸው፤ በመንፈስ ቅዱስ አጠመቃቸው። (ሐዋ ፩፥፭ / ፪፥፩-፲፬)

በደቀ መዛሙርቱ ላይ እፍ ባለባቸው ጊዜ ደግሞ የመንፈስ ቅዱስን ፀጋ ተቀበሉ። (ዮሐ ፳፥፳፩-፳፬) ከዕርገቱ በፊትም ደቀ መዛሙርቱን እስከ ቢታንያ አውጥቶ እጁን አንሥቶ በላያቸው ጭኖ ባርኳቸዋል። (ሉቃ ፳፬፥፶)

በዚሁ መሠረትም ቅዱሳን ሐዋርያት የተቀበሉትን የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ ለተከታዮቻቸው በአንብሮተ ዕድ ያድሉ ነበር። አዳዲስ ተጠማቂዎችም በሐዋርያትና በተከታዮቻቸው አንብሮተ ዕድ እየተደረገላቸው በልጅነት ይከብሩ ነበር። (ሐዋ 10፥14-17 / 19፥5-5)

ከጊዜ በኋላ ተጠማቂዎች እየበዙ ሲመጡ ለአባቶቻችን እግዚአብሔር ገልጾላቸው ቅብዐ ሜሮኑን በአንብሮተ ዕድ እያከበሩ ለአብየ ክርስቲያናት በማከፋፈል ምሥጢረ ሜሮን በአክብሮተ ዕድ ምትክ እንዲፈጸም ማድረግ ጀመሩ።

ይህንንም የቤተ ክርስቲያን አባቶች በሎዶቅያ ጉባኤ ወስነው አጸኑ።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->የቅብዐ ሜሮን አፈጻጸም
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽❼
2.2K viewsedited  19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 23:38:43 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
፫.፩ #ምሥጢረ_ጥምቀት
#አፈጻጸም
...
፲፪. ሥርዓተ ቅዳሴውን አድርሰው፣ መጽሐፈ ክርስትናውን ደግመው ማዩን ከባረኩ በኋላ ነው ማጥመቅ የሚጀምሩት። የ፵ እና የ፹ ቀን ሕጻናት ከተጠመቁ በኋላ ንዑሰ ክርስቲያን ወንዶችና ሴቶች ይጠመቃሉ።

የሚያጠምቁበትም ጊዜ "አጠምቀከ/ኪ በስመ አብ፡ አጠምቀከ/ኪ በስመ ወልድ፡ አጠምቀከ/ኪ በስመ መንፈስ ቅዱስ፡ ስምከ/ኪ ይሁን እገሌ/ሊት" በማለት ሲሆን አስቀድመው መስቀል ግንባሩ ላይ አድርገው የሰየሙትን ስም ክርስትና የሚያጸኑት በዚያው ሰዓት ነው ማለት ነው።

፲፫. ከተጠመቁ በኋላ ካህኑ ሚሮን ይቀባቸዋል። የተዘጋጀላቸውን ነጭ ልብስ ለብሰው ቅዳሴ አስቀድሰው ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉ። በሜሮን ከከበሩም በኋላ ሦስት ኅብረ ቀለማት ያሉት ማተብ ይታሰርላቸዋል። ኅብረ ቀለማቱም ነጭ፣ ቀይ፣ ጥቁር/ቢጫ ናቸው።

፲፬. የክርስትና አባት/እናት አብረው ጾመውና ተገቢውን ዝግጅት አድርገው በዕለቱ ሥጋውን ደሙን ይቀበላሉ።

፲፭. በዕለቱ ክርስትና የተነሡ/የተጠመቁ የሕጻናትና ንዑሰ ክርስቲያን የነበሩ አዳዲስ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ከሌሎች ቆራቢያን አስቀድመው ቅዱሳን ቁርባን ይቀበላሉ።

፲፮. ወንዶች ሴቶችን፣ ሴቶችም ወንዶችን ክርስትና አያነሡም።

፲፯. የምትጠመቀዋን ንዑሰ ክርስቲያን ሴት ቅብዓ ቅዱሳንና ሜሮኑን ኤጲስ ቆጶሱ ከአንገትዋ በላይ ከቀባት በኋላ ሌላውን ሰውነትዋን የምትቀባት ዲያቆናዊት ሴት ናት (ፍት. መን. አን. 3፤ድስቅ.34)

፲፰. የተጠማቂዎችን ራስ የሚያጠልቅ ማይ (ውሃ) በቤተክርስቲያን የማይገኝ ከሆነ ማዩን በእጁ እየዘገነ በሥላሴ ስም ያጠምቃቸዋል።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ምሥጢረ ሜሮን
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽❻
2.0K views20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-11 21:34:44 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
፫.፩
#ምሥጢረ_ጥምቀት
#አፈጻጸም
...
፬. ጥምቀቱ በትንሣኤ ከሆነ በዶሮ ጩኸት ጊዜ፤ በሌላ ቀንም ከሆነ መጠመቂያው ሰዓት ሲደርስ ተጠማቂዎችን በመካነ ጥምቀቱ ያቆማቸዋል። ያውም ካልሆነ ካህኑ ማዩን በብርት አድርጎ ሥርዓተ ጸሎቱን ያደርሳል።

፭. ከሰይጣን ቁራኝነት በሚለይበት በቅብዓ ቅዱሱ ላይ ጸልዮ በተራዳኢው ቄስ ይሰጥና ከተጠማቂዎች በስተግራ ያቆመዋል።

፮. ልጅነት በሚያሰጠውና መንፈስ ቅዱስን በሚያሳድረው በሜሮኑ ላይ ይጸልይና በሁለተኛው ቄስ ሰጥቶ ከተጠማቂዎች በስተቀኝ ያቆመዋል።

፯. ተጠማቂዎችን በማዘዝ ፊታቸውን ከምሥራቅ ወደ ምዕራብ፤ ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ ይመልሳቸውና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ማመናቸውን ያረጋግጣል።

፰. አንዱ ቄስ የተጠማቂዎችን እጅ እየያዘ ሕጻናትም ከሆኑ ዲያቆኑ (ቄሱ) አቅፎ ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ ይመልሳቸዋል። ይህም ሰይጣንን ክደው በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ማመናቸውን በምሳሌ የሚያረጋግጥበት መንገድ ነው። ምዕራብ የማኅደረ ዲያቢሎስ ምሥራቅም የማኅደረ ሥላሴ ምሳሌ ምሳሌዎች ናቸውና።

፱. ከዚህ በኋላ ቅብዓ ቅዱሱን ቀብቶ ያጠምቃቸዋል። ሲያጠምቃቸውም ልብሳቸውንና ማንኛውንም ጌጣ ጌጥ አውልቀውና ሴቶችም ሹርባቸውን ፈትተው ነው። ከዚያም በመጠመቂያው ፫ ጊዜ ብቅ ጥልቅ ያደርጋቸዋል። ምቹ መጠመቂያ ከሌለም ማዩን በላያቸው ላይ ሦስት ጊዜ እያፈሰሰ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠምቅሃለሁ(ሻለሁ) እያለ ያጠምቃቸዋል። ከመጠመቂያው በወጡም ጊዜ በንፍሐት ልጅነትን ያሳድርባቸዋል።

፲.ሴት በምትጠመቅበት ዕለት የወር አበባ ግዳጅ ከመጣባት እስክትነጻ ሳትጠመቅ ትቆያለች።

፲፩ ተጠማቂዎች መናገር ከቻሉ ራሳቸው፤ ካልቻሉም የክርስትና አባት (እናት) የሆኑት ክርስቲያኖች የተጠማቂውን አውራ ጣት ይዘው ጸሎተ ሃይማኖትን በማንበብ ሃይማኖታቸውን ይመሰክራሉ።...
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->...
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽❺
1.9K viewsedited  18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 22:23:55 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
፫.፩ #ምሥጢረ_ጥምቀት
#አፈጻጸም
ምሥጢረ ጥምቀት የሚፈጸመው በቤተክርስቲያንና በካህናት አማካኝነት ብቻ ነው። አጥማቂው ኤጲስ ቆጶስ ወይም ቄስ ሲሆን ዲያቆናት ደግሞ በተራዳኢነት ይፋጠናሉ። (ፍትሐ ነገሥት ፫፥፳፩)

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አስቀድሞ ወንጌለ መንግሥትን እያስተማሩ አሕዛብን ሁሉ እንዲያስተምሩና በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እንዲያጠምቋቸው ቅዱሳን ሐዋርያትን ማዘዙ እና ለቅድስት ቤተክርስቲያን መመሪያ መስጠቱ ይታወቃል።

እንዲህ ሲል "እንግዲህ ሂዱና በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ አሐዛብን ሁሉ አስተምሩ፤ ያዘዝኋችሁንም እንዲጠብቁ አስተምሯቸው፤ እኔም እስከ ዓለም ፍጻሜ በዘመኑ ሁሉ ከእናንተ ጋር እኖራለሁ።" (ማቴ ፳፰፥፲፱-፳)

በዚህም የአጥማቂነት ሥልጣን ለቅዱሳን ደቀ መዛሙርቱና በእነርሱም አማካይነት እስከ ዓለም ፍጻሜ ለሚነሱ ካህናት ሁሉ የተሰጠ ሀብት መሆኑን እንረዳለን።

በተጨማሪም ጥምቀት በሥላሴ ስም መሆን እንደሚገባውም በዚህ አንቀጽ አስተምሮናል።

ዋና ዋናዎቹ የምሥጢረ ጥምቀት አፈጻጸም ሥርዓትን የሚመለከቱ ነጥቦች ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ናቸው።

፩. ንዑሰ ክርስቲያን የሚጠመቁት የትንሣኤ ዕለት ከሆነ ተገቢውን ትምህርት ቀድመው ተምረውና ንስሐ ገብተው በሰሙነ ሕማማት ሐሙስ ልብሳቸውን አዘጋጅተውና ሰውነታቸውን ታጥበው በመጾም ቅዳሜ ሌሊቱን ለእሑድ አጥቢያ ይጠመቃሉ። በሌላ ቀን ከሆነ ደግሞ በዋዜማው ታጥበውና ጾመው ይዘጋጁና የመቁረቢያ ልብሳቸውን በንጽሕና አዘጋጅተው በዕለቱ ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው ይጠመቃሉ።

፪. ኤጲስ ቆጶሱ (ቄሱ) የሚጠመቁትን ሰብስቦ ራሳቸውን ወደ ምሥራቅ እንዲያዘነብሉ ያዛቸዋል። እጁንም በላያቸው ዘርግቶ ይጸልይላቸዋል።

፫. መሐላውን አስምሎ ማለትም ሰይጣንን አስክዶና ክርስቶስን አሳምኖ ከፈጸመ በኋላ በዐራቱም መዓዘን ለአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ በፊታቸው ላይ እፍ ይልባቸዋል፤ አካላቸውንም በመስቀል ምልክት አማትቦ ይባርካቸዋል።...
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->...
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽❹
1.9K viewsedited  19:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ