Get Mystery Box with random crypto!

የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ

የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የቴሌግራም ቻናል አርማ tewahdo_haymanotie — የተዋህዶ ቤተሰቦች✝ ኮርስ መስጫ
የሰርጥ አድራሻ: @tewahdo_haymanotie
ምድቦች: ቴሌግራም
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 5.40K
የሰርጥ መግለጫ

✍️"አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት" (ወደ ኤፌሶን ሰዎች ❹፥➎)✅
✍️ጥንታዊቷንና እውነተኛዋን ሃይማኖት ለመማር ከ1️⃣ኛ ዓመት ጀምሮ ኮርሶች እየተሰጡበት ያለ የእግዚአብሔር ቤት ነው።
✍️የማንኛውም ሃይማኖት ተከታይ ገብቶ መማር ይችላል። 🌹ቅድሚያ ለነፍስዎ ይኑሩ!🌹
ኮርሶች👇
t.me/Tewahdo_Haymanotie/703
አገልጋዮችን ለማግኘት
@Dingl_Ruhruhitu_bot

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-09 23:40:20 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#ምዕራፍ-፫_ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን
ምሥጢራት የተባሉበት ምክኒያት ላመኑት እንጂ ላላመኑት ሥለማይሰጥ፤ በዓይን የሚታየው በእጅ የሚዳሰሰው ግዙፉ ነገር በግብረ መንፈስ ቅዱስ ሲለወጥ ስለማይታይ፤ በሚታይ፣ በሚሰማና በሚዳሰስ አገልግሎት የማይታይ፣ የማይሰማና ያማይዳሰስ ሰማያዊ ፀጋ ስለሚያሰጥ ነው።

እነዚህ በግብር አምላካዊ ለሰው ልጆች የሚታደለው ጸጋ እግዚአብሔር ሰባቱ ብቻ ናቸው ማለት አይደለም። ነገር ግን እነዚህ እንደ አርእስት ሁነው የተቀሩትንም ጨምረው ሲያድሉ ይኖራሉ። "የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤ አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤ አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው።" (1ኛ ቆሮ 12፥4-6) እንዲል።

በምዕራፍ ፩ ስለ ሰባቱ ምሥጢራት ባሕርያት፣ ስለ ሚደገሙትና ማይደገሙት፣ ለምን ሰባት እንደሆኑ ስለተብራራ ሊንኩን በመንካት ማንበብ ትችላላችሁ t.me/Tewahdo_Haymanotie/656

በነገረ ሃይማኖት ኮርስ ደግሞ እንዲሁ በ3ኛውና በመጨረሻው ምዕራፍ አምስቱ እዕማደ ምሥጢራት ተብለን ተምረናል። እነዚህም፦
ምሥጢረ ሥላሴ
ምሥጢረ ጥምቀት
ምሥጢረ ሥጋዌ
ምሥጢረ ቁርባን
ምሥጢረ ተንሣኤ ሙታን ናቸው።

ሰባቱ ምሥጢራተ ቤተክርስቲያን በመባል ያሚታወቁትና አሁን የምናማራቸው ደግሞ፦
፩, ምሥጢረ ጥምቀት
፪, ምሥጢረ ሜሮን
፫, ምሥጢረ ቁርባን
፬, ምሥጢረ ክህነት
፭, ምሥጢረ ተክሊል
፮, ምሥጢረ ንስሐ
፯, ምሥጢረ ቀንዲል ናቸው።

ከእነዚህ መካከል ምሥጢረ ጥምቀትና ምሥጢረ ቁርባን ስለሚደገሙ ትርጉማቸውን/ምንነታቸውን አመሠራረታቸውን፣ ጥቅማቸውን በነገረ ሃይማኖት ስለተቀመጠ አሁን ሥርዓታቸውን ወይም አተገባበራቸውን ብቻ ጽፈንላችሁ እናልፋለን። ማንጽፍላችሁን t.me/Tewahdo_Haymanotie/68 በመንካት ማጥናት ትችላላችሁ።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->፩. ምሥጢረ ጥምቀት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❽❸
2.1K views20:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-13 22:33:52 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#ለሥርዓተ_ቤተክርስቲያን_የሚደረግ_ክብርና_ጥንቃቄ
ቤተክረስቲያን፦ ለአምልኮተ እግዚአብሔር ተሰብስበን ጸሎታችንንና ምስጋናችንን ለእግዚአብሔር የምናቀርብበት፣ በጥምቀተ ክርስትና ከእግዚአብሔር በፀጋ የተወለድንባት፣ ሥርየተ ኃጢአትን የምናገኝባት፣ ፀጋ መንፈስ ቅዱስን የተቀበልንባት፣ በሥጋ ወደሙ የዘላለም ሕይወትን የምንታደልባት፣ በንስሐ በደላችንን አስወግደን ከእግዚአብሔር የምንታረቅባት፣ የምሕረትና የድኅነት አደባባይ ስለሆነች እጅግ የከበረች የእግዚአብሔር ቤተመንግሥት ቤተክህነት ናት።

ቤተክርስቲያን ክቡር እግዚአብሔር በደሙ ፈሳሽነት ያከበራት ወደ እረሱ የቀረቡትንም የምታከብር ቅድስት ክብርት ናት። በመሆኑም በሚገባ ክብርና ጥንቃቄ ያስፈልጋታል።

ስለዚህ ማንኛውም ክብሯን ለመጎናጸፍ የሚሻ/የሚፈልግ ክረስቲያን የሚገባውን ክብር ሊያደርግ ይገባዋል። በሌላ አነጋገር ሥርዓቷን በመጠበቅና በማስጠበቅ ሁሉም የተቻለውን ማድረግ ይጠበቅበታል።

ለቤተክረስቲያን የሚደረግ ጥንቃቄና ክብር ማለት ለሥርዓተ ቤተክረስቲያን የሚደረግ ማለት ሲሆን እነዚህም፦
➺የልቦና ዝግጅት
➺ንጹሕ ልብስ መልበስ
➺ልብስን ማደግደግ ወይም በትእምርተ መስቀል መልበስ
➺ነጭ ልብስ መልበስ
➺መባዕ ይዞ ወደ ቤተክርስቲያን መምጣት
➺ሌሎችንም በዝርዝር እናያለን
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->የልቦና ዝግጅት
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❺❸
854 views19:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 23:05:08 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#ቤተ ክርስቲያን ስትባረክ
በሐዲስ ኪዳን አንድ ቤተክርስቲያን እስካሁን ባየነው መልክ ተሠርቶ ካለቀ በኋላ ሌሊት የማኅሌቱ ሥርዓት እንዳለቀ ታቦቱ ከመቃኛው ሳለ በዚያ ውስጥ ውዳሴ ማርያም፣ መልክአ ማርያም፣ መልክአ ኢየሱስ፣ ሰባቱ ኪዳናት ይጸለያል።

ከዚህ በኋላ ምንባብ ይነበባል። ከምንባቡ በኋላ ዕዝል አቡን ተብሎ ታቦቱ ይወጣል። ቀጥታ ወደ ምዕራብ ይሄድና በምዕራብ አሁንም ምንባብ ምስባክ ወንጌል አቡን ይባላል። በዚህ ጊዜ ጳጳሱ የምዕራቡን በር መስኮት ቅኔ ማኅሌቱንና ቅድስቱን በሙሉ አጽቅ አጽቁን በሜሮን በትምዕርተ መስቀል ይቀቡታል። ቤተክርስቲያን በሜሮን እንጅ በሌላ አትቀባም።

ሲፈጽሙ ወደ ደቡብ ሂደው እንዲሁ እስከ ውስጥ ድረስ ሂደው ይቀቡታል። እንዲህ እያደረጉ ዙሪያውን ቀብተው ሲፈጽሙ ታቦቱ ወደ መቅደስ ይገባል። በዚህ ጊዜ መቅደሱና መንበሩን ቀብተው ታቦቱ ከመንበሩ ይቀመጣል። ወንጌለ ዮሐንስ በታቦቱ ላይ ወይም በጎን ሆኖ ይነበባል። ከዚህ በኋላ ቅዳሴ ይገባል። ቤተ ክረስቲያኑ በተባረከ ዕለት በውስጡ ይቀደስበታል። የቅብአ ሜሮን ሥርዓቱ ግን ምንጊዜም ሌሊት ከቅዳሴ በፊት እንጂ ማታ አይሆንም።

ኤጲስ ቆጶሱ ቅዳሴ ቤተክረስቲያን በሚያደርግበት ጊዜ ከእርሱ ጋር ለተራድኦ 7 ቀሳውስት እንዲገኙ ታዘዋል።

ኤጲስ ቆጶሱ ሳይመጣ ቀሳውስትና ዲያቆናት ሳይሰበሰቡ ቅዳሴ ቤተክርስቲያን አይደረግም።

ከዚህም በኋላ እንደሌሎች ቤተክረስቲያናት አገልግሎቷን ትቀጥላለች።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ለሥርዓተ ቤተክርስቲያን የሚደረግ ክብርና ጥንቃቄ
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❺➋
1.2K views20:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-11 21:14:07 እንዴት ዋላችሁ የተዋህዶ ፍሬዎች።

ትንሽ አልመቸን ስላለ ኮርሶች በሥርዓቱ አልተለቀቁላችሁም። ይቅርታ እሽ

ነገ ከዚህ በላይ ክፍት የሆኑት በሙሉ ስለሚሞሉ እንድትከታተሉ።

መልካም በዓል
1.5K views18:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 22:46:04 t.me/Tewahdo_Haymanotie/631
1.6K views19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 22:29:10 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#እንደ_ቤተክርስቲያኑ_አቅም_ሊሠሩ_የሚገባቸው_ቤቶች
◆የሰበካ ጉባኤ ጽ/ቤት
◆የሰንበት ትምህርት ቤቶች
◆የምእመናን መማሪያ የስብከተ ወንጌል አዳራሽ
◆የእንግዶች የካህናት ማረፊያ ቤቶች
◆የመንፈሳዊ ትምህርት ቤትና የተግባረ እድ መማሪያ ክፍሎች
◆ቤተ መጽሐፍት
◆የመገልገያ እቃዎችና ጧፍ፣ እጣን ሽያጭ ክፍሎች ናቸው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->ቤተ ክርስቲያን ስትባረክ
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❺❶
1.7K viewsedited  19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 21:49:37 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#በቤተክርስቲያን_ዙሪያ_የሚሠሩ_አገልግሎት_የሚሰጡ_ቤቶች
ቤተክረስቲያን ሲሠራ የሚሠራው አንድ ቤት ብቻ አይደለም። በቤተክርስቲያኑ አካባቢ የሚሠሩ ከቤተክርስቲያኑ ጋር አብረው አገልግሎት የሚሰጡ ቤቶች አሉ። እነዚህም በሁለት ይከፈላሉ።
የግድ ከቤተክርስቲያኑ ሳይለዩ አብረው የሚሠሩ አስፈላጊ ቤቶች።
እንደ ቤተክርስቲያኑ አቅም ሊሠሩ የሚገባቸው ቤቶች።

#የግድ_ከቤተክርስቲያኑ_ሳይለዩ_አብረው_የሚሠሩ_አስፈላጊ_ቤቶች
፩. ቤተልሔም፦ በቤተክረስቲያኑ በምሥራቅ በኩል የሚሠራ ቤት ነው።
●ዲያቆናቱ ለመሥዋዕት የሚሆነውን ኅብስትና ወይን የሚያዘጋጁበት ቤት ነው።
●ስያሜው የተወሰደው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተወለደበት በቤተልሔም ዘይሁዳ ምሳሌ ነው።

ምሥጢሩና ቁም ነገሩ ደግሞ ዲያቆናት ኅብስቱን በቤተልሔም አዘጋጅተው ወደ ቤተክረስቲያን ለመሥዋዕት መምጣቱ፤ በቤተልሔም የተወለደው ጌታችን ኢየሱስ ክረስቶስ ክረስቶስ ለመሥዋዕት ወደ ጎለጎታ የመምጣቱ ምሳሌ ነው። መቅደስ የጎለጎታ ምሳሌ ነውና።

፪. የግብር ቤት፦ ለመሥዋዕት የሚሆነው ስንዴ/መገበሪያ የሚሰየምበት የሚደቅቅበት ወይም የሚፈጭበት በቤተክረስቲያኑ ቅጽር ግቢ የሚሠራ ቤት ነው። ስንዴው መገበሪያ ተብሏልና መፍጨቱ ደግሞ መሰየም ይባላል። ይህም የመሥዋዕቱ አቀራረብ ቋንቋ ነው።

፫. እቃ ቤት፦ የቤተ ክረስቲያን ንዋየ ቅድሳት የሚቀመጥበት ቤት ነው። የቤተክርስቲያኑ መገልገያ የሆኑት አልባሳትም፣ መጽሐፍትም የሚቀመጡት በዚህ ቤት ነው።

፬. የማጥመቂያ ቤት፦ ሥርዓተ ጥምቀት የሚፈጸምበት ቤት ነው። ይህም ወንዶች በ40 ቀን ሴቶች በ80 ቀን ከሥላሴ ልጅነት ያገኙ ዘንድ ሥርዓተ ጥምቀት የሚፈጸምበት ቤት ነው።

፭. ደጀ ሰላም፦ ደጀሰላም ከቤተክርስቲያኑ በስተ ምዕራብ በኩል ይሠራል። የሚሠራውም በቤተክርስቲያኑ ቅጽር ሲሆን የሚሠጠው አገልግሎት እንደ አካባቢው ሊለያይ ይችላል።
➺ለጸሎተ ፍትሐት
➺ለካህናት ማረፊያ
➺ለእንግዳ መቀበያ... ወዘተ አገልግሎት ይውላል።
ደጀ ሰላም የገነት ምሳሌ ነው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->እንደ ቤተክርስቲያኑ አቅም ሊሠሩ የሚገባቸው ቤቶች
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!

ገፅ ❺⓪
2.0K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 19:41:02
@Tewahdo_Haymanotie
1.9K viewsedited  16:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 22:57:47 @Tewahdo_Haymanotie
2.0K views19:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 23:25:06 "፮ኛ ኮርስ "የቤተ ስርስቲያን ሥርዓትና ምጢራት"

#በስመ_አብ_ወወልድ_ወመንፈስ_ቅዱስ_አሐዱ_አምላክ_አሜን

►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►►
#የንዋያተ_ቅዱሳት_የአቀማመጥና_የአጠቃቀም_ሥርዓት
የሥርዓት ባለቤት የሆነች ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ለሁሉም ነገር ሥርዓት ያላት እንደመሆኑ መጠን ንዋያት ቅድሳቷንም እንዴት መጠቀም እንዳለባትና የት ማስቀመጥ እንዳለባት ሥርዓት ሠርታለች።

የንዋያተ ቅድሳት የቀጠቃቀም ሥርዓት
●ከንዋያት ቅድሳት ውስጥ ካህኑ የሚጠቀምባቸው ዲያቆኑ ግን የማይጠቀምባቸው አሉ።
●ካህኑ የሚነካቸው/የሚዳስሳቸው ዲያቆኑ ግን ሊነካቸው የማይገባ አሉ።
የካህናት ልብሰ ተክህኖ እና አክሊል ከዲያቆናት የተለየ ነው።
●ልዑካኑ በመጠቀም የሚለያዩባቸው ንዋያተ ቅዱሳት ለምሳሌ፦
➺ማዕጠንቱን ካህናት ይጠቀሙበታል ዲያቆናት ግን አይጠቀሙበትም።
➺መንበሩን ካህናት ይነኩታል ዲያቆናት ግን አይነኩትም
➺ታቦተ ሕጉን ካህናት ይዳስሱታል ለዲያቆናት ግን አይፈቀድም።
➺እንዲሁም በአገልግሎት ጊዜ ለምሳሌ በቅዳሴ ልብሰ ተክህኖ በአንድ ላይ ሆኖ ከአበው ታላቅ የሆነ አባት ባርኮ ይሰጣል። ልዑካኑም መጠናቸውን ተመልክተው ይለብሳሉ። ከለበሱ በኋላ ረዘመብኝ አጠረብኝ ብሎ ማውለቅ አይፈቀድም። ልብሰ ተክህኖው እስከ ተረከዛቸው ሊሆን ይገባል። ልብሰ ተክህኖው ነጭ ሊሆን ይገባል።

እነዚህንና የመሳሰሉትን ሥርዓቶች ቤተክርስቲያን ሠርታለች።


የንዋያተ ቅዱሳት የአቀማመጥ ሥርዓት
ንዋያተ ቅዱሳት ተጸልዮባቸው ንዋያተ ቅዱሳት ሚለውን ስያሜ ካገኙ በኋላ፦
●በዕቃ ቤት ውስጥ ይቀመጣሉ።
●በዕጣን ይታጠናሉ።
●ብል እንዳያበላሻቸው በየጊዜው ይጎበኛሉ/ንፋስ ያገኛሉ።
●የሚታጠቡት ይታጠባሉ የማይታጠቡት ይወለወላሉ።
●ከቅጽረ ቤተክረስቲያን ውጪ ከማንኛውም ቤት አይቀመጡም።
●ለሥጋዊ ተግባር መገልገያ ማድረግ ተገቢ አይደለም። (ፍት አንቀጽ 12) እንደዚህ አይነት የአቀማመጥ ሥርዓት አላቸው።
◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄◄

@Tewahdo_Haymanotie
#ቀጣይ_ትምህርታችን-->በቤተክርስቲያን ዙሪያ የሚሠሩ ቤቶች
#ወስብሀት_ለእግዚአብሔር_ወለወላዲቱ_ድንግል_ወለመስቀሉ_ክቡር_ይቆየን!!


ገፅ ❹❾
2.3K views20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ