Get Mystery Box with random crypto!

Tebazu Bekele Official

የቴሌግራም ቻናል አርማ tebazushows — Tebazu Bekele Official T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tebazushows — Tebazu Bekele Official
የሰርጥ አድራሻ: @tebazushows
ምድቦች: ሙዚቃ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 910
የሰርጥ መግለጫ

251916091904
251934140013

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-20 22:14:13 ክፍል=አንድ
ጽድቅ_ምንድነው? (መግቢያ)

"ጽድቅ" የሚለው ቃል በአዲስ ኪዳን ግሪክ "ዲካይሱኔ" የሚባል ሲሆን ቃሉ "ዲኬ" ከሚለው ስርወ-ቃል (Root Word) የመጣ ነው። "ዲኬ" ማለት "ትክክል" (Right) ማለት ነው። እንዲሁም በዕብራይስጥ "ጸዴቅ" የሚል ሲሆን ትርጉሙ "ትክክል፣ ንጹሕ" ማለት ነው። እንግዲህ በቃሉ ትርጉም መሰረት አንድ ሰው ጸደቀ ማለት "ትክክል" ወይም "በደል-የለሽ" ሆነ ማለት ነው።

ሮሜ 3(አዲሱ መ.ት)
²¹ አሁን ግን ሕግና ነቢያት የመሰከሩለት፣ ከሕግ ውጭ የሆነ፣ የእግዚአብሔር ጽድቅ ተገልጦአል።
²² ይህ የእግዚአብሔር ጽድቅ ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው። ልዩነት የለም፤

ጽድቅ ማለት በእግዚአብሔር ፊት ትክክለኛ መሆን ማለት ነው። (Righteousness is right standing with God.)

በሕግ እና በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር ጽድቅ ያለ ሕግ የተገለጠ የእግዚአብሔር ማንነት ነው።
ጽድቅ የእግዚአብሔር ብቸኛው ማንነት ሲሆን በሰው ስራ እና ጥረት የማይገኝ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሆነ ነው።

የእግዚአብሔር ጽድቅ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ ጽድቅ ነው፤ ይህ የእግዚአብሔር ጽድቅ መቀበል የሚቻለው በእምነት ብቻ የተገለጠው ኢየሱስ ክርስቶስ ማመን ነው።

የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠው በሙሴ ሕግ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገለጥ እምነት ነው።

የእግዚአብሔር ጽድቅ በሀይማኖታዊ ስርዓት ኖረን የምንቀበለው ሽልማት ሳይሆን በኢየሱስ ክርስቶስ ባለው እምነት የሚገኝ ነው።

እውነተኛ የእግዚአብሔር ጽድቅ የተገለጠው በእግዚአብሔር ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ በማመን የሚገኝ መሆኑን በግልጽ ይናገራል።

Tebazu Bekele Official
Join
https://t.me/tebazushows
https://t.me/tebazushows
75 viewsTebazu Bekele, 19:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 12:33:19 #ተቀብሎናል!!

በክርስቶስ ኢየሱስ ያላችሁ ሁላችሁ ... እግዚአብሔር ተቀብሏችኋል!! የምስራች ...በፊቱ ሞገስ አግኝተናል!! በልጅነት ማዕረግ ተቀብሎናል!! ከክብር ጋር ተቀብሎናል!! ቅዱሳን ልጆቹ ሆይ ደስ እያላችሁ በፍቅሩ ተራመዱ!!

በእርሱ ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት አሁን የምንሠራው ሥራ የለም!! በክርስቶስ የመስቀል ሥራ ተቀባይነት አግኝተናል!! ተቀብሎን ... በእርሱ ውስጥ እየኖርን ነው፤ ከክርስቶስ ውጭ አይደለንም!! ተቀብለነው ... በእኛ ውስጥ እየኖረ ነው!!

በአሮጌው ኪዳን ...ሊቀ ካህናቱ ስለሕዝቡ ስለራሱም ኃጢአት መስዋዕት ያቀርባል። እርሱና መስዋዕቱ በእግዚአብሔር ተቀባይነት ካገኘ ሕዝቡም ተቀባይነት ያገኛሉ!! እርሱን ባይቀበለው ወይም በሞት ቢቀጣ ለሕዝቡ የመከራ ዓመት ይሆናል። የሕዝቡ ተቀባይነት የተወሰነው በእነርሱ ሥራ ሳይሆን በሊቀካህናቱ ሁኔታ ነው!! (ዕብራውያን 5፥3፤ 9፥25)። ይህ ተቀባይነት እስከ ቀጣዩ የስርየት ቀን ለአንድ ዓመት ብቻ የሚቆይ ነው!!

የኛ ሊቀካህናት ኢየሱስ ድካም የለበትም፤ መስዋዕቱም (ራሱ) ነውር የለበትም። እርሱም መስዋዕቱም ለዘላለም ተቀባይነት አግኝቷል!! በእርሱ እኛም ተቀባይነት አግኝተናል!! በኢየሱስ ሥራ ስለመጣን አብ ያለ ፀፀት ተቀብሎናል!! የተቀበለን ልጁን አይቶ ነው!!

ራሳችንን መጠየቅ ያለብን፦ እግዚአብሔር የልጁን የኢየሱስን ሥራ ተቀብሎታል? ኢየሱስ ላንተ እንደሠራ ተቀብለሃል? ኢየሱስ ላንቺ እንደሠራ ተቀብለሻል? መልሳችን አዎን እና አሜን ከሆነ ኢየሱስን ስንቀበል እግዚአብሔር ተቀብሎናል!!

በፊቱ ለመቆም ድፍረት የሚሰጠንን ሥራ በክርስቶስ ሠርቷል!! በዚህ ሥራ ያለ ነቀፋ ያለ ኩነኔ በፊት መኖር ተሰጥቶናል!! የኛ ሥራ በፊቱ ሕያው መሆን አልቻለም ነበር። ለዚያ ነው እንዲቀበለን የሚያደርገውን ሥራ በልጁ የሠራው!! የተወደዳችሁ ልጆቹ ሆይ #የሠራችሁትን ሳይሆን #የተሠራላችሁን ተመልከቱ!!

❝እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል።❞ —1ኛ ጴጥሮስ 2፥10።

ከመቀበል አልፎ የእግዚአብሔር ወገን ሆነናል!! ምሕረት አግኝተናል!! ኢየሱስ መስቀል ላይ እያለ ..ለምን ተውከኝ? ማለቱ ትዝ አላችሁ? እርሱን ሲተወዉ እኛ ተቀባይነት አገኘን፤ ከእርሱ ፊቱን ሲያዞር ...ዞሮ ያዬው እኛን ነው!! የያሕዌ ዓይኖች በእኛ ላይ ናቸው!! ኢየሱስ የተተወዉ በእኛ ስፍራ ሆኖ ነው፤ እኛም የተገኘነው በእርሱ ሆነን ነው!! ኢየሱስ ትኩረት የሚሰጠው አጥቶ ነበረ፥ ትውልድ ፊቱን አዙሮበታል፥ እግዚአብሔር ትቶታል!! ሰማይ ምድሩ ለእኛ ትኩረት የሰጠዉ፥ ተቀባይነት ያገኘነው በዚህ ምክንያት ነው!!

@tebazushows
@tebazushows
167 viewsTebazu Bekele, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 00:42:54 ሰላም ለእናንተ ይሁን እንዴት ዋላቹ

ከመሞትክ በፊት ቀድመክ አትሙት

በድሮ ጊዜ ሁለት አገልጋዮች ትልቅ ጥፋትን ያጠፉና ለፍርድ በንጉሱ ፊት ይቀርባሉ፡፡ ንጉሱም የጥፋታቸውን ከባድነት ከተረዳ በኀላ ሁለቱም በሞት እንዲቀጡ ይወስንባቸዋል፡፡ ለመሞትም ሁለቱም መርዝ እንዲጠጡ ያዛል፡፡ እናም ለሁለቱም በዋንጫ ተቀድቶ ይሰጣቸውና ግጥም አድርገው ይጠጡታል፡፡

ከሰከንዶች በኀላ አንደኛው አገልጋይ እዛው ተንፈራፍሮ ይሞታል፡፡ አንደኛው ግን ምንም ሳይሆን ይቀራል፡፡ ለካ ንጉሱ ምንም እንኳን አገልጋዮቹ ከባድ ጥፋት ቢያጠፉም በሞት ሊቀጣቸው አላሰበም ነበር፡፡ ይልቁንም ምን ያህል መንፈሰ ጠንካራ መሆናቸውን ለመፈተን ሲል ሁለቱንም መርዝ ጠጥታችሁ ትሞታላችሁ በማለት ንፁ ወይን በዋንጫ እንደሰጣቸውና እንዲጠጡ ነበር ያደረገው፡፡

ነገር ግን ምንም እንኳን የጠጡት ንፁ ወይን ቢሆንም አንደኛው አገልጋይ ገና መርዝ ጠጥቶ እንደሚሞት ሲነገረው ልቡ እና መንፈሱ ቀድሞ በመሞቱ ምንም መርዝ በሌለበት ወይን ጠጥቶ ሞቷል፡፡

ወደ እኛ ህይወትም ስንመጣ ተመሳሳይ ነው፡፡ ብዙዎቻችን በየቀኑ በሚገጥሙን ጥቃቅን ውጣውረዶች የተነሳ ምንም የሚገድል ነገር በሌለበት ቀድመን እንሞታለን፡፡ ችግሮቻችን የቱንም ያህል የገዘፉ ቢሆንም የፈጠረን እና የማይተወን አምላክ ክንዶች ደሞ ከችግሮቻችን ሺ እጥፍ የበረቱና የገዘፉ መሆናቸውን እናስብ፡፡

መልካም አዳር
@biblicaldoctrine
@biblicaldoctrine
@biblicaldoctrine
162 viewsTebazu Bekele, 21:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 00:32:58 ሰላም ለእናንተ ይሁን እንዴት ዋላቹ

ከመሞትክ በፊት ቀድመክ አትሙት

በድሮ ጊዜ ሁለት አገልጋዮች ትልቅ ጥፋትን ያጠፉና ለፍርድ በንጉሱ ፊት ይቀርባሉ፡፡ ንጉሱም የጥፋታቸውን ከባድነት ከተረዳ በኀላ ሁለቱም በሞት እንዲቀጡ ይወስንባቸዋል፡፡ ለመሞትም ሁለቱም መርዝ እንዲጠጡ ያዛል፡፡ እናም ለሁለቱም በዋንጫ ተቀድቶ ይሰጣቸውና ግጥም አድርገው ይጠጡታል፡፡

ከሰከንዶች በኀላ አንደኛው አገልጋይ እዛው ተንፈራፍሮ ይሞታል፡፡ አንደኛው ግን ምንም ሳይሆን ይቀራል፡፡ ለካ ንጉሱ ምንም እንኳን አገልጋዮቹ ከባድ ጥፋት ቢያጠፉም በሞት ሊቀጣቸው አላሰበም ነበር፡፡ ይልቁንም ምን ያህል መንፈሰ ጠንካራ መሆናቸውን ለመፈተን ሲል ሁለቱንም መርዝ ጠጥታችሁ ትሞታላችሁ በማለት ንፁ ወይን በዋንጫ እንደሰጣቸውና እንዲጠጡ ነበር ያደረገው፡፡

ነገር ግን ምንም እንኳን የጠጡት ንፁ ወይን ቢሆንም አንደኛው አገልጋይ ገና መርዝ ጠጥቶ እንደሚሞት ሲነገረው ልቡ እና መንፈሱ ቀድሞ በመሞቱ ምንም መርዝ በሌለበት ወይን ጠጥቶ ሞቷል፡፡

ወደ እኛ ህይወትም ስንመጣ ተመሳሳይ ነው፡፡ ብዙዎቻችን በየቀኑ በሚገጥሙን ጥቃቅን ውጣውረዶች የተነሳ ምንም የሚገድል ነገር በሌለበት ቀድመን እንሞታለን፡፡ ችግሮቻችን የቱንም ያህል የገዘፉ ቢሆንም የፈጠረን እና የማይተወን አምላክ ክንዶች ደሞ ከችግሮቻችን ሺ እጥፍ የበረቱና የገዘፉ መሆናቸውን እናስብ፡፡

መልካም አዳር
@biblicaldoctrine
@biblicaldoctrine
@biblicaldoctrine
130 viewsTebazu Bekele, 21:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-10 00:31:15 Channel name was changed to «Biblical Doctrine»
21:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 21:58:51 "፤ ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።"
(የማቴዎስ ወንጌል 26: 41)
Join us
@gototheworld1
@gototheworld1
232 viewsTebazu Bekele, 18:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 09:37:37
https://t.me/gototheworld1
215 viewsTebazu Bekele, edited  06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 09:37:35
https://t.me/gototheworld1
194 viewsTebazu Bekele, edited  06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 01:17:22 ወንጌል ለምን እንመሰክራለን?

  ሰዎች ሁሉ ከእግዚአብሄር ጋር በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ባለ እምነት ታርቀው የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ ካለን ልባዊ ፍላጎት  የተነሣ ወንጌልን እንሰብካለን። ሰዎች የምስራቹን ካልሰሙ በኃጢአታቸው ምክንያት የዘላለም ሞትን ይሞታሉ። የእግዚአብሄርም ቁጣ በአለማመናቸው ምክንያት በእነሱ ላይ ይኾናል። የምንመሰክርበትን አንኳር ምክንያት በሁለት መንገድ ማስቀመጥ እንችላለን።  ሰዎችን በክርስቶስ ፍቅር ስለምንወድዳቸው ወንጌልን እንነግራቸዋለን። “..የክርስቶስ ፍቅር ግድ ይለናል..” (2ቆሮ.5፡14)። የተካፈልንውን የክርስቶስ ፍቅር ፣ ያገኘንውን የዘላለም ህይወት ለሰዎች ማካፈል ደስታችን ነው (1ዩሐ.1፡1-4)። ወንጌልን መመስከር ከፍቅር የተነሣ የምናደርገው ተግባር ነው። ሰዎች በኃጢአታቸው እንዳይጠፉ፣ የዘላለምን ህይወት እንዲያገኙ ስለምንፈልግ ወንጌልን እንመሰክራለን።

ሌላው ምክንያት ወንጌልን መመስከር ከጌታ የተሰጠን ትዕዛዝ ስለሆነ እንመሰክራለን። የምስክርነት ተግባር በአራቱም ወንጌላት እና በሐዋርያት ስራ ተጠቅሷል (ማቴ.28፡18-20፣ ማርቆ.16፡15፣ሉቃ.24፡47 ፣ ዩሐ.20፡21 ሐዋ.1፡8)። ወንጌልን ለፍጥረት ሁሉ ለማድረስ ለሆነው አገልግሎት በእግዚአብሄር  ተልከናል።

በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሄር ጋር የተራቁ ሰዎች ሁሉ ሌሎች እንዲታረቁ የማስታረቅን አገልግሎት ተቀብለዋል፣ “እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን..”(2ቆሮ.5፡19-20)። ይሄ አገልግሎት በእግዚአብሄር ለሁላችንም ተሰጥቶናል።

ከጨለማው ዓለም የጠራንን፣ የዘላለም ህይወት የሰጠንን፣ ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ ያልተገባንን ቸርነት ያደረገልንን የጌታን በጎነት ለሌሎች መናገር የምድር ቆይታችን አገልግሎት ነው። ሐዋርያው ጴጥሮስ ስለዚህ አገልግሎታችን እንዲህ ብሎ ይናገራል፣ “እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ..”(1ጴጥ 2፡9-10)።
Join us
  @gototheworld1
@gototheworld1
174 viewsTebazu Bekele, edited  22:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 00:47:11
አስደሳች ዜና
Go to the world
ሂዱ ወደ ዓለም የወንጌል አገልግሎት
አላማችን ትውልዱን ከሀሰት አስተምህሮ መታደግና እውነተኛ መጽሐፍ ቅዱሳዊ አስተምሮትን በማስተማር በየአመቱ GO በሚል መሪ ቃል ትውልዱን ወደ አለም ሁሉ በወንጌል እንዲደርሱ ማሰማራት ነው።
በዚህ አገልግሎት ከእኛ ጋር ለማገልገል ከፈለጉ በዚህ ስልክ ቁጥሮች በቴሌግራም ውስጥ ያናግሩን እንዲሁም በመመዝገብ በቅርብ ቀን በቴልግራም ቻናላችን መሰጠት የሚጀምረውን የወንጌል ስልጠና መከታተል ይጀምሩ!!
+251916091904
+96170286091
አሁኑኑ ይመዝገቡ!!
በአንድ ነፍስ አንድ ነፍስ!
Join Us telegram
https://t.me/gototheworld1
https://t.me/gototheworld1
140 viewsTebazu Bekele, edited  21:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ