Get Mystery Box with random crypto!

ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ)

የቴሌግራም ቻናል አርማ sigewe — ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ)
የቴሌግራም ቻናል አርማ sigewe — ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ)
የሰርጥ አድራሻ: @sigewe
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 7.53K
የሰርጥ መግለጫ

❤ በየቀኑ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በስንክሳር የሚታሰቡ የቅዱሳን ታሪክ፣ የኢትዮጵያኑ ቅዱሳን በየበዐላቸው ቀን አስደናቂ፣ አስገራሚ ገድላቸው፣ ቃል ኪዳናቸው፣ የቅዱሳን ሰላምታ፣ የየቀኑ የቅዳሴ መልዕክታ፣ የሐዋርያት ሥራ፣ የወንጌል ጥቅስ እና ምስባክ ይቀርብበታል።
❤ የፌስቡክ አድራሻዬ ሊንክ https://www.facebook.com/profile.php?id=100063896616886

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-27 21:54:07 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

+ + +
"ካዕበ ይቤላ ካልእ እምነቢያት ወአንቲኒ ቤተ ልሔም ምድረ ኤፍራታ ኢትቴሐቲ እምነገሥተ ይሁዳ እስመ እምኔኪ ይወጽእ ንጉሥ ዘይርዕዮሙ ለሕዝብየ እስራኤል"። ትርጉም፦ ዳግመኛም ከነቢያት አንዱ ሚክያስ "አንቺ የኤፍራታ ክፍል የሆንሽ ቤተ ልሔም ከይሁዳ ነገሥታት መሳፍንት አገር አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቃቸው ንጉሥ ካንች ይወጣልና"። ሚክ 5፥2 አባ ኤፍሬም የሐሙስ ውዳሴ ማርያው።

በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA
811 viewsAschalew Kassaye, 18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 16:56:50
828 viewsAschalew Kassaye, 13:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 16:56:41 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

እንኳን ለማዕከለ ክረምት ለዕጒ(ጓ)ለ ቋዓትና ደስያት ለሚታሰብበት ሳምንት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።

+ + +
የዚህ ሳምንት መዝሙ፦ ሃሌ ሉያ "ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ ይሁበነ ዝናመ በጊዜሁ ወይሁበነ እክለ በረከት፤ አዝ፣ ያርኁ ክረምተ ይገብር ምሕረተ ወይሁበነ ዝናመ በረከት፤ አዝ፣ ከሢቶ ዐይኖ ሰፊሖ የማኖ ይፌኑ ሣህሎ ወበዘአእመረ ይሴባሕ፤ አዝ፣ ወሠርዐ ሰንበት ለሰብእ ዕረፍተ ወብውህ ሎቱ ይኅድግ ኀጢአተ ዐይነ ኵሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ ኪያሁ ይሁቦሙ ሲሳዮሙ በጊዜሁ"። ትርጉም፦ ዝናመ ምሕረቱን በጊዜው ይሰጠናል፤ እክለ በረከቱንም በጊዜው ያድለናል፤ አንቀጸ ክረምትን ይከፍታል (ያመጣል) ምሕረትንም ያደርጋል፤ የበረከት ዝናምንም ይሰጠናል፤ የፍቅር ዓይኖቹ ከፍቶ የምሕረቱን ቀኝ እጁን ዘርግቶ ቸርነቱን ይቅርታውን ይልካል፤ እርሱ ባወቀ ይመሰገናል፤ ለሰው ልጅ ዕረፍት እንዲሆን ሰንበትን ሠራ ኃጢአትን ይቅር ይል ዘንድ የሁሉም ዓይን አንተን ተስፋ ያደርጋል፤ እርሱም በጊዜው ምግባቸውን ይሰጣቸዋል። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ።

+ + +
ዕጕ(ጓ)ለ ቋዓት፦ ይህ ክፍለ ክረምት ከነሐሴ 10 እስከ ነሐሴ 27 ቀን ድረስ ያሉት ዕለታት የሚጠሩበት ነው። በዚህ ክፍል ክረምት ፍጥረታትና በባሕር የተከበቡ ደሴቶች የሚታወሱበት ሲሆን ወቅቱም ዕጕ(ጓ)ለ ቋዓት ይባላል። ዕጕ(ጓ)ለ ቋዓት የሚለው ቃል ቁራን ሲያመለክት፤ ቁራ ሲወለድ ያለ ፀጉር (ያለላባ) በሥጋ ብቻ ይወለዳል። እናትና አባቱም እነርሱን ባለመምሰሉ ደግንጠው ይሸሻሉ፤ በዚህ ጊዜ የሚንከባከበው ያጣል፤ ምግብ በሚያስፈልገው ሰዓት አፉን ከፈት ያደርጋል፤ እግዚአብሔር በረድኤት ተሕዋስያንን ብር ትር እያደረገ ከአፉ ያስገባለታል ይመግባል።

አባታች ኢዮብ "ልጆቹ ወደ እግዚአብሔር ሲጮኹ የሚበሉትም አጥተው ሲቅበዘበዙ ለቁራ መብልን የሚሰጠው ማን ነው?" ኢዮ 38፥41 ብሎ እንደ ገለጠው ያ ዕጕ(ጓ)ለ ቋዓት እግዚአብሔር የሰጠውን እየተመገበ ቆይቶ ሲጠነክር እንደ እናቱና እንደ አባቱ ፀጉር ያወጣል። በዚህ ጊዜ እናትና አባቱ ቀርበው ይንከባከቡታል።

በሥነ ፍጥረት አቆጣጠር በክንፍ የሚበሩ የሰማይ አዕዋፍን ሁሉ ይወክላል። ይህን አምላካችን እግዚአብሔር ለፍጥረት ሁሉ የሚያስብ በመሆኑ ርኅርኄ ለተመላው አምላክነቱና ከሃሊነቱ መታሰቢያ እንዲሆን ይህን ወቅት ቤተ ክርስቲያን "ዕጒ(ጓ)ለ ቋዓት" በማለት ታስታውሰዋለች።

+ + +
ደስያት፦ ማለት በውኃ የተከበቡ ቦታዎች ማለት ነው። እነዚህን ቦታዎች በውኃ እንዲሸፈኑ አድርጎ በውስጣቸው ያሉትን ሰዎች፣ እንስሳት፣ አራዊትና አዕዋፍ ሁሉ የሚጠብቃቸው፤ በወርኃ ክረምት የወንዞች ሙላት የአብሕርትና የውቅያኖስ መነዋወጥ አይሎ እንዲያጠፋቸው ሁሉም ከልኩ እንዳያልፍ በማድረግ በደስያት ውስጥ የሚኖሩትን ፍጥረታት በተስፋና በእምነት አበርትቶ የሚያኖራቸው እግዚአብሔር ነው። ይህን ድንቅ ሥራ ያዩ ሰዎች እግዚአብሔርን ያመሰግናሉ፤ ከሃሊነቱን ያደንቃሉ።

እንደዚሁ በደሴት (በቤተ ክርስቲያን) የተጠጉ ሁሉ ከሞተ ሥጋና ከሞተ ነፍስ ይጠበቃሉ። በዚህ ወቅት ክፍለ ክረምቱ እንደተገባደደ ውኃው እየጠራ፣ መሬቱ እየረጋ፣ ደመናውና ጉሙ እየቀለለ፣ የወንዙ ሙላት እየጎደለ፣ የክረምት ምግባቸውን ይዘው በየዋሻው የከረሙ ጭልፊቶችና አሞራዎች ድምፃቸውን እያሰሙ ምግብ ፍለጋ ሲወጡ የሚታዩበት ወቅት ነው። ምንጭ፦ ኆኅተ ስብከት ዘቅዱስ ያሬድ ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ።

+ + +
የዕለቱ ምስባክ፦ "ዐይነ ኵሉ ነፍስ ይሴፎ ኪያከ። እንተ ትሁቦሙ ሲሳዮሙ በጊዜሁ። ትሰፍሕ የማነከ ወታጸግብ ለኵሉ እንስሳ ዘበሥርዓትከ"። መዝ 144፥15-16። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 3፥1-ፍ.ም፣ ያዕ 5፥1-12፣ የሐዋ.ሥራ 22፥1-22። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 6፥41-ፍ.ም። የሚቀደሰው የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ቅዳሴ ነው። መልካም የነቢዩ የቅዱስ ሚክያስ የዕረፍትበዓል። ለሁላችን ይሁንልን።

በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA
826 viewsAschalew Kassaye, edited  13:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 16:46:18
630 viewsAschalew Kassaye, 13:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 16:44:11 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

ነሐሴ ፳፪ (22) ቀን።

እንኳን ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ለሆነው ለታላቁ ለሞራት ልጅ ለነቢዩ ለቅዱስ ሚክያስ ለዕረፍት በሰላም አደረሰን።

+ + +
የሞራት ልጅ ታላቁ ነቢይ ቅዱስ ሚክያስ፦ ይህም ነቢይ በይሁዳ ነገሥታት በኢዮአታም፣ በአካአዝና በሕዝቅያስ ዘመን ትንቢት በመናገር አስተማረ።

ስለጌታችን መውረድም እንዲህ አለ። "እነሆ እግዚአብሔር ከልዑል መንበሩ ወደዚህ ዓለም ይወርዳል"።

ሁለተኛም ስለ ልደቱ እንዲህ ብሎ ተናገረ "የኤፍራታ ዕጣ የምትሆኚ አንቺ ቤተ ልሔም የእስራኤል ነገሥታት ከነገሡባቸው አገሮች አታንሺም ወገኖቹን የሚጠብቃቸው የእስራኤል ንጉሥ ከአንቺ ይወጣልና"።

ስለ ምኵራብ መቅረት፤ ስለ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ሁሉ መታነፅ ትንቢት ተናግሮአል። ዳግመኛም ስለ ሕገ ወንጌል መሠራት "ከጽዮን የእግዚአብሔር ቃል ከኢየሩሳሌም ይወጣል" አለ። የትንቢቱም ወራት ሲፈጸም ወደ በጎ ሽምግልና ደርሶ ወደ ወደደው እግዚአብሔር ሔደ።

የትንቢቱ ዘመን ከጌታችን መምጣት በፊት በስምንት መቶ ዓመት ነው። ማርታ በምትባልም ቦታ ተቀበረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የነቢዩ የቅዱስ ሚክያስ በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የነሐሴ 22 ስንክሳር።

+ + +
"ሰላም ለሚክያስ ነባቢተ ትንቢት ልሳኑ። ዘይከውን በበዘመኑ። እንዘ ይብል ከመዝ ኂሩተ አምላክ ይዜኑ። መኑ ከማከ እግዚኦ አምሳለ አማልክት ዘኮኑ። አበሳ ርስቱ ዘይትነሐይ መኑ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የነሐሴ 22።


በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA
801 viewsAschalew Kassaye, 13:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:49:02
1.0K viewsAschalew Kassaye, 18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:48:36 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

ነሐሴ ፳፩ (21) ቀን።

እንኳን ለኢትዮጵያዊ ጻድቅ ኤርትራ አገር የሚነኘው ደብረ ጥሉል ገዳምን ለመሰረቱ በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበረውን የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት ላለማየት ሳይወለዱ በእናታቸው ማኅፀን 7 ዓመት ከ6 ወር ለቆዩት ለታላቁ አባት አቡነ አብራኒዮስ ዓመታዊ ለዕረፍት በዓላቸው በሰላም አደረሰን።

+ + +
አቡነ አብራኒዮስ፦ አባታቸው ወልደ ክርስቶስ እናታቸው ወለተ ትንሣኤ የሚባሉ ደጋግ ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ የተወለዱት በ1624 ዓ.ም ምሥራቅ ጎጃም አካባቢ ልዩ ስሙ እነብሴ ይሁን እንጂ ተጋድሏቸውን ያደረጉትና ገዳማቸውን የገደሙት በዛሬዋ ኤርትራ ውስጥ ነው፡፡ ገዳሙ ኤርትራ ውስጥ ዞባ ድባርዋ ደቂ ድግና በተባለ አካባቢ ይገኛል፡፡ የገደሙት ጻድቁ በ1705 ዓ.ም ነው፡፡

አቡነ አብራኒዮስ የተፀነሱት በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል አብሳሪነት ነው፡፡ ነገር ግን ቀደም ብዬ እንደጠቀስኩት ጻድቁ በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበረውን የቤተ ክርስቲያንን ጥፋት ላለማየት ሳይወለዱ በእግዚአብሔር ፈቃድ በእናታቸው ማኅፀን 7 ዓመት ከ6 ወር ተቀምጠዋል፡፡ በዚህም ወቅት እሳት ልትጭር ከጎረቤቷ የመጣች አንዲት ሴት የአቡነ አብራኒዮስ እናት "የማትወልጂው ምን ሆነሽ ነው?" ብላ ስትናገር ጻድቁ በእናታቸው ማኅፀን ሆነው "…ለምን ክፉ ትናገሪያለሽ?" ብለው መልስ ሰጥተዋታል፡፡ ይህም ቅዱሳን ልክ እንደ ነቢዩ ኤርምያስ ገና በእናታቸው ማኅፀን ሳሉ እንደሚመረጡ አንድ ማሳያ ነው፡፡

በርካታ ምእመናንን በሰማዕትነት ከገደሉ በኋላ በመጨረሻም ዐፄ ሱስንዮስ በመቅሰፍት ተመተው ሊሞቱ ሲሉ "ሃይማኖት ይመለስ፣ ፋሲል ይንገሥ" ብለው የቤተ ክርስቲያን ሰላም መልሰው ንስሓ ገብተው ሞቱ፡፡ አቡነ አብራኒዮስም ይህ የቤተ ክክርስቲያን የመከራ ዘመን ሲያልፍና ሃይማኖት ሲመለስ ተወለዱ፡፡ ገና በ5 ዓመታቸው ከጥንቆላ መጻሕፍት በቀር ሁሉንም የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትንና ምሥጢራትን ሁሉ ተምረው ዐወቁ፡፡ በ12 ዓመታቸው መነኰሱ፡፡ ዲቁና ሲሾሙም ጳጳሱ "ገና ሕፃን ነው፣ አሁን አልሾመውም" ሲሉ የሰማይ መላእክት "ይባዋል" ብለው መስክረውላቸዋል፡፡

በልጅነታቸውም መነኰሳቱ ወደ ጫካ ሔደው ዕንጨት እንዲሰብሩ ሲያዟቸው ጌታችን ግን ለአቡነ አብራኒዮስ ኃይል ሰጥቷቸው በነፋስ ሠረገላ እየሔዱ የ6 ሰዓቱን የእግር መንገድ እሳቸው ግን ዕንጨቱን ሰብረው በቶሎ ይመለሱ ነበር፡፡ ይህም ሲታወቅባቸው ውዳሴ ከንቱን ንቀው ከዚያ ገዳም ወጥተው ወደ አቡነ ተጠምቀ መድኅን ዘንድ ሔዱ፡፡ በዚያም በታላቅ ተጋድሎ ከኖሩ በኋላ አቡነ ተጠምቀ መድኅን "በአንተ ምክንያት ብዙ ነፍሳት ይድናሉ፣ ክፍልህ በዚያ ነው" ብለው አሁን ገዳማቸውን ወደገደሙበት ቦታ (ኤርትራ) ላኳቸው፤ ሲመጡም ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል እየመሯቸው እንደመጡ ገድላቸው ይናገራል፡፡ ጻድቁ ወደዚህ ገዳም ሲመጡ በፊት ይቀመጡባት የነበረችው ትልቅ ድንጋይ በተኣምር ከመሬት 7 ክንድ ከፍ ብላ አብራቸው መጥታለች፡፡ ድንጋይዋ ዛሬም ድረስ በገዳማቸው በክብር ስለተቀመጠች ምእመናን እየዳሰሷት ይባረኩባታል፣ መካኖች ይወልዱባታል፣ ሕሙማን ይፈወሱባታል፡፡

አቡነ አብራኒዮስ በቅዳሴ ጊዜ ጌታችንን በዕለተ ዐርብ እንደተሰቀለ ሆኖ ይመለከቱት ስለነበር በኀዘን በተመስጦ ሆነው ይቆዩም ስለነበር ሕዝቡም "በቅዳሴ ሰዓት ይተኛል" እያሉ ያሟቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ ጻድቁ ወደ አካለ ጉዛይ በመሔድ በዘንዶ ላይ አድሮ ይመለክ የነበረውን ሰይጣን በጸሎታቸው አጥፍተው ዘንዶውን ገድለው ሕዝቡንም አስተምረው በንስሓ መልሰው አጥምቀዋቸዋል፡፡ ወደ ታላቁ ገዳም ደብረ ቢዘንም ሲሔዱ 6400 አጋንንትን አግኝተው በጸሎታቸው አጥፍተዋቸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት አቡነ አብራኒዮስ "ሰዳዴ አጋንንት-አጋንንት አባራሪ" ተብለዋል፡፡

አቡነ አብራኒዮስ ወደ ሌላ ቦታ ሔደው ሰለዳዋ የምትባል ቦታ ላይ ሆነው ሳለ አንድ ሰው ወደ ገዳማቸው ገብቶ አንዲትን ዛፍ ሲቆርጥ በመንፈስ ቅዱስ መነጽርነት አዩት፡፡ ቆራጩም ሰው "ተው አትቁረጥ" የሚል የአባታችንን ድምፅ ሰማ፣ በአካል የሉም ብሎ እምቢ አለ፣ ነገር ግን በመቅሠፍት ተመቶ ወዲያው ሞተ፡፡ በአንድ ዕለትም ልጃገረዶች እየዘፈኑ ሲሔዱ ብዙ አጋንንት በዘፈናቸው ተደስተው አብረዋቸው ሲጨፍሩ አባታችን በመንፈስ ተመልክተው ለልጃገረዶቹ ዘፈን የአጋንንት መሆኑን እንዳስተማሯቸው ገድላቸው ይናገራል፡፡

ለአቡነ አብራኒዮስ ለዕፍታቸው ሲደርስ ክብርት እመቤታችን ተገልጻ "ቤተ ክርስቲያን በስሜ አንጽልኝ" አለቻቸው፡፡ እርሳቸውም ውብ አድርገው በእመቤታችን ስም አነጹ ነገር ግን ፍጻሜውን ሳያዩ በዕለተ ቀኗ ነሐሴ 21 ቀን ዐረፉ፡፡ በዕረፍታቸውም ወቅት ጌታችን ተገልጦ ታላቅ ቃልኪዳን ሲሰጣቸው "...ዋስ እፈልጋለሁ፣ ዋስ ስጠኝ" አሉት፡፡ ጌታችንም "ሐዋርያት፣ ሰማዕታት፣ ከአንተ በፊት የነበሩ ጻድቃን ያልጠየቁኝን አንተ እንዴት ጠየከኝ?" አላቸው፡፡ እርሳቸውም "አምላኬ ሆይ! አንተ መሐሪና በጽድቅ ፈራጅ ቃልህም የማይለወጥ እንደሆንክ አውቃለሁ" አሉት፡፡ ጌታችም ፍግግ ብሎ "ይሁን የምትሻውን አላሳጣህም" በማለት ከፈጣሪ በታች ከፍጡራን በላይ የሆነች ክብርት እመቤታችንንና ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ዋስ አድርጎ ቃል ኪዳን ከገባላቸው በኋላ ነሐሴ 21 ቀን 1713 ዓ.ም በሰላም ዐረፉ። ከታላቁ ጻድቅ ከአባታች አቡነ አብራኒዮስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፣ በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት።

በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA
1.0K viewsAschalew Kassaye, 18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:15:27
785 viewsAschalew Kassaye, 18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:15:16 "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"።

ነሐሴ ፳፩ (21) ቀን።

እንኳን ለኢትዮጵያዊቷ ንግሥት ታቦተ ጽዮንን ወደ አገራችን ላመጣ ለንጉሥ ምኒልክ ቀዳማዊ እናት ለንግስት ማክዳ ወይም ለንግስተ ሳባ (አዜብ) ለልደት በዓል፣ ለንጉሥ ቆስጠንጢኖስ እናት ለንግሥት እሌኒ የልደት በሰላም አደረሰን።

+ + +
"ሰላም ለእሌኒ ንግሥት ዘከሠተት መስቀለ በጎልጎታ ለክርስቲያን ዘይከውን ወልታ፤ እምኀበ ወጽአ ጢስ በሃይማኖታ፤ ወዓዲ ረከበት ቅንዋተ መስቀሉ ለክርስቶስ፣ ወአግበረት ልጓመ ፈረስ በከመ ይቤ ዘካርያስ"። ትርጉም፦ ጢስ በሃይማኖቷ ከወጣ ዘንድ ለክርስቲያን ጋሻ የሚኾን መስቀልን በጎልጎታ ያወጣች ለኾነች ለንግሥት እሌኒ ሰላምታ ይገባል፤ ዳግመኛም የክርስቶስን የመስቀሉን ችንካሮች አገኘች፤ ዘካርያስ እንደተናገረው ለፈረስ ልጓም አሠራች። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ።

+ + +
ንግሥት ቅድስት ዕሌኒ፦ ይቺም ቅድስት በፊት የአንድ ነጋዴ ሰው ሚስት ነበረች እርሱም በነገረ ሠሪ ንጽሕት ሁና ሳለች ወደ ባሕር ጣላት። የክብር ባለቤት በሆነ በጌታችን ፈቃድም ሮሐ ከሚባል አገር ደርሳ የበራጥያ ንጉሥ ቊንስጣ አገኛት። ውበቷንና ደምግባቷንም አይቶ አገባት። ለክርስቲያን ነገሥታት መጀመርያቸው የሆነውን ቈስጠንጢኖስን ወለደችው ምግባርንና ሃይማኖትን በማስተማር በመልካም አሳደገችው።

ልጇም በነገሠ ጊዜ "ወደ ኢየሩሳሌም ሔደሽ የክብር ባለቤት የሆነ የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ግለጪ የከበሩ ቦታዎችንም ሥሪ" የሚላትን በሕልሟ አይታ እንዴት እንዳየች ይህን ለልጇ ነገረችው እርሱም ከብዙ ሠራዊቱ ጋራ ሰደዳት። በደረሰችም ጊዜ የክብር ባለቤት ስለሆነ ስለ ጌታችን መስቀል መረመች አዳኝ የሆነ መስቀሉንም ሁለት ወንበዴዎች ከተሰቀሉባቸው መስቀሎች ጋራ አገኘችው። የክብር ባለቤት የኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል የትኛው እንደሆነ ታውቅ ዘንድ በወደደች ጊዜ ከራሱ በላይ "ይህ የናዝሬቱ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው" የሚል በእንጨት የተቀረጸበት ጽሑፍ ያለው እንደሆነ የኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ቅዱስ መቃርስ ነገራት።

ከዚህም በኋላ ከእርሱ ምልክት ታይ ዘንድ ፈለገች የሞተ ሰውም አግኝታ መስቀሎችን በበድኑ ላይ አኖረች አልተነሣም። ከዚህ በኋላ ሦስተኛውን መስቀል በላዩ አኖረች። ያን ጊዜ ያ ምውት ተነሣ ሃይማኖቷም ጸና ደስታዋም በዛ።

ከዚህ በኋላ ዜናቸው በመስከረም ወር በዐሥራ ሰባት የተጻፈ በከበሩ ቦታዎች ውስጥ አብያተ ክርስቲያናትን ትሠራ ዘንድ ጀመረች። ለአባ መቃርስም በከበሩ ቦታዎች ሁሉ አብያተ ክርስቲያናትን እንዲሠራ ብዙ ገንዘብ ሰጠችው።

ከዚህ በኋላ ወደ ልጇ ተመልሳ የሆነውን ሁሉ ነገረችው የከበረ መስቀል በመገኘቱ እጅግ ደስ አለው። ይቺም ቅድስት በጎ ገድላሏን ከፈጸመችና እግዚአብሔርንም ከአገለገለች በኋላ ስለ ካህናትም ልብስና ቀለብ ለአብያተ ክርስቲያናትና ለገዳማት ብዙ ጉልቶችና ርስቶችን ለድኆችና ለምስኪኖችም እንዲሁ ከሠራችና ከተከለች በኋላ ግንቦት9 ቀን በሰላም ዐረፈች መላ ዕድሜዋም ሰማንያ ሆነ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ዕለኔ በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ የግንቦት9 ስንክሳር።

+ + +
ንግሥተ ሳባ፦ ይህቺ ኢትዮዽያዊት ንግሥት ከ3 ሺ ዘመናት በፊት የነበረች ደግ እናት ናት። በሥጋዊ ደረጃ ከታንዛንያ እስከ የመን ያስተዳደረች ስመ ጥር ንግሥት ስትሆን በመንፈሳዊው ደረጃ ደግሞ እግዚአብሔር የቀባውን ሰው ፍለጋ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዛለች።

ከዚያውም አምልኮተ እግዚአብሔርን ከሥርዓተ ኦሪት ጋር አምጥታለች። ድንግልናዋን ለታላቁ ንጉሥ ሰሎሞን ሰጥታ ቀዳማዊ ምኒልክን ወልዳለች።

ይህቺ ንግሥት በጌታችን (በፈጣሪ) አንደበትም ተመስግናለች። (ማቴ. 12፥42) በስምም ሳባ፣ አዜብና ማክዳ ተብላ ትታወቃለች። ዛሬ ዕለተ ልደቷ ነው። ምንጭ፦ ከዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ።

በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት።

@sigewe

https://t.me/joinchat/AAAAAFGQ22bI0Ij80hYpFA
943 viewsAschalew Kassaye, 18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:35:23
980 viewsAschalew Kassaye, 11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ