Get Mystery Box with random crypto!

ሥርዓተ ቤተክርስቲያን Tube

የቴሌግራም ቻናል አርማ seratebtkrstian — ሥርዓተ ቤተክርስቲያን Tube
የቴሌግራም ቻናል አርማ seratebtkrstian — ሥርዓተ ቤተክርስቲያን Tube
የሰርጥ አድራሻ: @seratebtkrstian
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 36.08K
የሰርጥ መግለጫ

https://www.youtube.com/channel/UCyyw8be1uLS-PdwVLd-zyKw
#subscribe ያርጉ ይቀላቀሉ እና ይማሩ👆👆👆

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-19 09:57:21 ከእናንተ የመጣ ጥያቄ 249

ጥያቄው?
ሰላመ እግዚአብሔር ካንተ ጋ ይሁንና
የኔ ጥያቄ.....


.ስንፍና ፣በነገሮች መሰላቸት ፣ አለመፀለይ፣ አለመስገድ፣ቤተክርስቲያን የመሄድ ፍቅር መጥፋት፣ ሰዉ መጥላት፣ ወዘተ...
  እነዚህ ስሜቶች በምን ማጥፋት ይቻላል?
አመሰግናለዉ

የዲያቆን መልስ ትክክል ነው በምን አይነት እይታ እንዳነበብነው አላውቅም ለማንኛውም በተረዳሁ ልሞክር

ስንፍናን በጉብዝና ማለቱ ከመስነፍ ይልቅ ስንፍናን የሚያመጣብን ዲያቢሎስ. ስለሆነ መትጋት
ነገሮችን መሰላቸት ባለመሰልቸት ማለት እንድንሰለች የሚያደርገን   በአይምሮአችን ጸሎቱ ብዙ እንደሆነ ቶሎ እንደማያልቅ አድርጎ ያሳየናል  እንድንሰለቸው የሚያደርገን ጠላታችን ስለሆነ መበርታት ነው

እንድሁም እንዳንሰለች በመጀመሪያ የዘወትርንና የእመቤታችን ውዳሴዋን መጸለይ ማለትም አንዳንድ ጊዜ ብዙ ጹሎት እናበዛና ወደመሰላቸት ይወስደናል በተለይ ጸሎት ማድረግ የጀመርን ሰሞን የማንጸልየው ጸሎት የለም  እየቆየን ስንሄድ ስለሚበዛ ወደመሰልቼት እንሄዳለን   ይህም ማለት ትንሽ ትንሹን እየጸለይን ቀስ በቀስ የጸሎትን ጣዕሙን ስናውቀው እያደግን እንሄዳለን 
አለመጸለይን በመጸለይ ማለት እንዳንጸልይ የሚያደርገን እርኩስ መንፈስን የምናሸንፈው በመጸለይ ነው በጸሎት ብንዝል በስግደት
እንኳንስ ስመ እግዚአብሔርን እየጠራን ሰግደን ትዝ አይላችሁም ትምህርት ቤት ስንማር ስልችት ሲለን መምህሩ ተነሱና ተቀመጡ እያለ ድክም  ያለንን መንፈስ ሲያስለቅቅልን

ስለዚህ እንድንጸልይ የሚያደርገንን እርኩስ. መንፈስ በስግደት አለመስገድን በመስገድ ማለት ምን እንዳንሰግድ የሚያደርገንን በስግደት ማሸነፍ ነው
ከቤተ ክርስቲያን መቅረትን በመሄድ ማለትየመዝሙረኛው ዳዊትን ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ የሚለውን የእግዚአብሔር ቃል በማሰብ ቤተክርስቲያን በ መሄድ በጉባኤው ተገኝቶ  ቃሉን መማር
ሰው መጥላትን በመውደድ
እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት። ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም። እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ ብታደርጉ እናንተ ወዳጆቼ ናችሁ። ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ
እነዚህን ስሜቶች ማጥፋት ይቻላል!የሚለውን የጌታን ትእዛዝ እያሰብን


በመጀመሪያ ጸሎት  እንዳንጸልይ እንድንሰለች
ሰውን እንድንጠላ ወደቤተክርስቲያን እንዳንሄድ ያደረገን ማነው ቢሉ ጥንተ ጠላታችን ዲያብሎስ ነው  ለጸሎት እጃችን በዘረጋን ጊዜ እንድንሰላች ያደርገናል በዚህን ጊዜ ብድግ ብለን  በስግደት መትጋት  እንዳለብን ነው 


ሌላው  አንድ ነገር ማስተዋል አለብን  የእግዚአብሔር 10ቱን  ህግጋትንእንድ ጠብቅ ታዘናል አይደል
  ጠላታችንም 10ቱ ህግጋት እንዳሉት አባቶች ያስተምራሉ
ማስተዋል ያለብን   ጥንተ ጠላታችን  ዲያቢሎስ እንደሚያሰራን ነው እንዴት ቢሉ  እሱም አስርቱህግጋትን  ተተቃራኒው ያሰራናል

1. ከእግዚአብሔር ሌላ አማልክት አታምልክ የሚለውን በየጠንቋይ ቤቱ  በየምኑ ሲያሮጠን ይውላል

2. የእግዜብሔርን ስም በከንቱ አትጥራ የሚለውን በከንቱ ሲያስጠራን
3. የሰንበትን ቀን አክብር የሚለውን ሲያሽረን
4. እናት እና አባትህን አክብር የሚለውን ለወላጆች እንዳንታዘዝ ሲያደርገን
5. አትስረቅ የሚለውን  ስንሰርቅ
6. አትግደል የሚለውን ስንገድል
7. አታመንዝር የሚለውን ስናመነዝር
8. በሃሰት አትመስክር የሚለውን በሀሰት ስንመሰክር
9. የባልንጀራህን ገንዘብ አትመኝ የሚለውን ሲያስመኘን
10. ባልንጀራህን እንደራስህ ወደድ የሚለውን ሲያጣላን 

እንድሁም ንጉስ ዳዊት ወደቤተክርስቲያን እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስስ አለኝ የሚለውን ትተን ወደ ጭፈራው እንድንሄድ ያደርገናል



ስለዚህ ስንፍናን   የምናርቀው  ወንጌላዊው ቅዱስ. ማቴወስ  ወደፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ  ብሎ በወንጌል እንደጻፈውን  አስታውሰን ስንፍናን ባለመስነፍ የሚለውን ያስረዳናል
አንድም በማቴዎስ ወንጌል እንደምናገኘው  በጸሎት  ተግተው  መብራታቸውን(ዘይታቸውን ሞልተው)የጠበቁትን አምስቱደናግልን ስንመለከት በጸሎት ያልበረቱት ደግሞ ሂዱአላውቃችሁም ተብለው በር ሲዘጋባቸው
አይተናል እንደዛ እንዳንሆን መትጋት ያስፈልጋል
    
ስለዚህ በጸሎት እንበርታ ስንፍናን እናስወግድ ስንጸልይ እንቅልፍ እንቅልፍ ሊለን ይችላል በስግደት


አንድ እውነታ ልንገራችሁ የሆነ ጊዜ መዝሙረ ዳዊትን ጸሎት እያደረስኩ ብዙ ስለሆነ ግማሽ ሲቀረኝ  እንቅልፍ አስቼገረኝ ከዛም በቀዝቃዛ ውሃ ፊቴን ታጥቤ እንደገና አማትቤ ጸሎቴን ጨረስኩ ይሄንን ያልኳችሁ ስንፍናን ወይም መሰላቸትን በቀላል መንገድ ማስወገድ እንደምንችል ለመጠቆም ያህል ነው

እስኪ ወደጸሎቱ መለስ እንበል
ጸሎት ማለት ጸለየ ከሚለው የግዕዝ ግሥ የወጣ ሲሆን ትርጉሙም፦
ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋገረ፣ ለመነ፣ አመሰገነ፣ ዘመረ ማለት ነው።
በጸሎት ውስጥ ልመነ አለ፤ ጸሎት ውስጥ ምስጋና አለ፤ ጸሎት ውስጥ ዝማሬ አለ።

ባጠቃላይ ጸሎት ማለት ሰው ከልኡል እግዚአብሔር ጋር የሚገናኝበት ፍፁም
ፍቅር ነው።
እግዚአብሔር የንፁሆችን ብቻ
ሳይሆን የደካሞችንም ፀሎት ይቀበላል።
ጸሎት ግን ንፁህ ከአምላኩ ጋር የሚያገናኝ
ፍፁም ፍቅር ልኖረው ያስፈልጋል።
በሃያ አራት(24) ሰዓት ሰባት ጊዜ በፊቱ ለፀሎት ስንቆም መጀመርያ ፊታችንን
በውኃ መታጠብ ያስፈልጋል። ከዚያም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሃዱ አምላክ ብሎ ማማተብ። ከመኝታችን ተነስተን ፣ከስራ ውለን ዝም ብለን ወደ ጸሎት ከሄድን ስንፍና የማይኖርበት ምንም ምክንያት የለውም
መዝሙረኛው ቅዱስ ዳዊት እንዳስተማረን ፊትን ወደ ምስራቅ መመለስና መቆም።
መዝ.67(68) ቁ.33 በምስራቅ በኩል ወደ ሰማይ ሰማያት ለወጣ
ለእግዚአብሔር ዘምሩ። እንዲል
እንዲሁም  ወንጌላዊ ሉቃስ በወንጌሉ 12:35 በፊቱ ለመቆም ወገባቸው የታጠቁ
መብራታችሁ የበራ ይሁን ይላልና።ወደድ የሚለውን ብ ስንፀልይ ዓይኖቻችን ወደ ሰማይ አቅንተን
ማያት እንዳለብን እንዳለብን መጽሐፍ ይነግረናል።
ዮሐ 11:41 ኢየሱስ ክርስቶስ
ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አንስቶ አባት ሆይ ስለሰማህኝ አመሰግንሃለሁ ብሎ
ፀሎይል።
ጸሎት፡- እሳትን ውኃ አንበሳን በግ ታደርጋለች
ጦርነትን ታስቀራለች የሞት ሰንሰለትን ትበጥሳለች ፤የመንግሥተ ሰማያትን ደጅ ትከትበጥሳለች
ዌአትን ታርቃለች፤ሁከትን ታቀዘቅዛለች
አጋንንት እንደ ትቢያ በነው እንደ ጢስተነው እንዲጠፉ ታደርጋለች
ብዙ ከተሞችን ከመፍረስ ትጠብቃለች
ሐሰትን ታርቃለች፤የነፍስ የሥጋ ንውጽውታን ታረጋጋለች፡፡
ጸሎትን የምንጸልየው እግዚአብሔር የማያውቀው ነገር ኖሮ ለመንገር ወይም የረሳው ነገር ኖሮ ለማስታወስ አይደለም፤ ወደ እርሱ እንድንቀርብ፣ ቀርበን ወዳጆቹ እንድንኾን፣ ዘወትር እንዲረዳን፣ ራሳችንን ዝቅ ለማድረግ፣ ኃጢአታችንንም እንድናሰብ ነው።
አሳ ከባህር ከወጣ ለደቂቃ በህይወት መኖር እንደማይችል ሁሉ እኛም በጸሎት ወደ እግዚአብሔር ካልቀረብን  እንደአሳው መሆናችን   መሆናችን ግድነው
እንዴት  ወደ ቤተክርስቲያን እን ቅርብ የሚለውን ስናይ በመጀመሪያ ጓደኛ መምረጥ.  ይኖርብናል ውሎአችን ማወቅ
1.4K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, 06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 07:44:36
የርዕሰ ሊቃውንት መጋቤ ብሉይ ወሐዲስ አባ ገብረኪዳን ትምህርቶች

ድንቅ፣ኃያል፣ርትዕት፣ጥንታዊት የሆነች የኦርቶዶክስን ሃይማኖት ከሚሰብኩ እናም ዕንቁ ከሚባሉት መካከል ቀዳሚው አባት ርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረኪዳንን ትምህርት የሚያገኙት ብቸኛው ቻናል ነው ይግቡ።


@abagebrekidan
@abagebrekidan
@abagebrekidan
1.6K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 04:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-19 07:40:32
እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው
በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!!!
መልካም የትንሣኤ በዓል

ከትንሳኤ በኋላ ያለው ሳምንት ሰባቱም ቀን እያንዳንዱ ትርጉም አለው ትርጉሙን ለማወቅ

https://t.me/+RkglPUfilfs4MDFk
https://t.me/+RkglPUfilfs4MDFk
1.6K viewsዲያቆን አቤንዔዘር ሙሉ, 04:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 14:28:34 ተወዳጆች ሆይ ከእኔ ምን ተማራችሁ?

1 ንስሓ አባት መያዝ እንደለባችሁ!

2 ንስሓ አባት መጠየቅና መጎብኘት እንዳለባችሁ!

3 ንስሓ አባታችሁን እንኳን አደረሳችሁ ብላችሁ እቤታቸው ከቻላችሁ የአክፋይ ካልቻላችሁ እጅ እና እግራችሁን ይዛችሁ መሄድ እንዳለባችሁ!

4 እሳቸው ጋር ስትሄዱ በዛው አንዳንድ ትምህርቶችን ቀስማችሁ እንደምትመጡ!

5  እንደ እናንተ አባታቸውን ሊጠይቁ የመጡ ልጆች ጋር ትግባባላቹ ትተዋወቃላቹ ወንድም እና እህት ስለሆናችሁ ማለት ነው!
ወዘተ.......

እኔ ሕማማት የሚለውን የዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ መጽሐፍ ልወስድ ነው እናንተ ደግሞ መጽሐፍ ሥዕለ አድኅኖ ጥምጥም ጋቢ ካባ መስቀል  መነኩሴ ከሆኑ ቆብ ቀሚስ ወዘተ....

ደስ ያላችሁን ውሰዱ! ይሄ በውዴታ እንጂ በግዴታ አደለም! ባዶ እጃቹንም ብትሄዱ አሪፍ ነው ግን ዋናው ነገር መሄዳቹ ነው!

በሉ ልሄድ ነው መልካም ምሽት!.... መጽሐፍ መደብር እንገናኝ የለም ከተባለ ግን ተናድጄም አላቆም በሉ ቻው!

ንስሓ አባቴ መጣሁልዎት

አዘጋጅ ዲያቆን ፍቅረ አብ

ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን Tube ቻናል ተከታታዮች የተዘጋጀ!

https://www.youtube.com/channel/UCyyw8be1uLS-PdwVLd-zyKw

#subscribe ያርጉ ይቀላቀሉ እና ይማሩ

@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   


     join
2.9K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, 11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 13:51:19 በቃ ወስኛለሁ! መጽሐፍ እሰጣቸዋለሁ! ከዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ መጻሕፍት መካከል የቱን ልውሰድ ህማማት ይሻላል ወይስ የብርሃን እናት ? ሁለቱም በጣም የምወዳቸው መጻህፍት ናቸው! ግን ሙምረጡ ከበደኝ! ምረጡልኝ!
2.5K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, 10:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 13:41:10 እኔ ምላቹ ዛሬ ንስሓ አባቴ ጋር አክፋይ ልሄድ ነው! እስቲ አማክሩኝ ምን ይዤ ልሂድ? ምን ተይዞ ነው ሚኬደው?
2.4K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, edited  10:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 13:08:15 እኔ ምላቹ ዛሬ ንስሓ አባቴ ጋር አክፋይ ልሄድ ነው! እስቲ አማክሩኝ ምን ይዤ ልሂድ? ምን ተይዞ ነው ሚኬደው?
2.5K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, edited  10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 10:40:36 ምጽዋትስ አምላካዊ ብድር ናት!
በምትችለው አቅም መጽውት!

መልካም ቀን
2.7K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, edited  07:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 21:18:11 ክፍል ሁለት


በመጨረሻ ከማስተርቤሽን እና ይህንን ከመሰሉ የዝሙት ርኩሰት መንገዶች የምታመልጠው
በተቀደሰው ጋብቻ አማካኝነት ነው። ይህንን በተመለከተ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል ፦ "
ነገር ግን ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራስዋ
ባል ይኑራት።" (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7: 2) ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ዝሙትን ጠንቅ
ብሎ ነው የጠራው በወጣትነት ወራታችን ከዲያብሎስ ከሚወረወሩ ፍላጻዎች መካከል አንዱ
የዝሙት ፍላጻ ነው ይህንን ፍላጻ ለመመከት ጋብቻ መመከቻ ጋሻ መሆኑን ከገጸ ንባቡ
እንረዳለን። በእውነት ከሴጋ የኃጢአት ዓለም ወጥተን በተቀደስ ጋብቻ ለመኖር ማሰባችን
የሚመሰገን መንፈሳዊ ውሳኔ ቢሆንም ጋብቻችንን ግን በትህትና በተሰበረ ልብ ልንፈጽም
መዘጋጀት ይኖርብናል።
አንዳንድ ሰዎች ማስተርቤሽን ሲፈጽሙ ከኖሩ በኋላ የንስሐ አባቴ ፈቅደውልኛል በማለት
ተክሊል ለመፈጸም ሲዳፈሩ ይታያል። እነዚህ ሰዎች ሰለ ማስተርቤሽን በጥልቀት ለንስሐ
አባታቸው ሳይናገሩ በሥጋ ብቻ ድንግል መሆናቸውን አጉልተው በማምታታት /
በማድበስበስ/ ኑዛዜ ፈጽመው ወደ ተክሊል ለመምጣት የሚያደርጉት ጥረት ለመአት ካልሆነ
የበረከት መንገድ አለመሆኑ ግልጽ ጉዳይ ነውና መጠንቀቅ ያስፈልጋል።
ተወዳጆች ከድፍረት የሚገኝ ምንም አይነት መንፈሳዊ በረከት የለም። ድፍረት መንፈሳዊ
ኪሳራን ያስከትላል ለዚህ ነው ቅዱስ ዳዊት እንዲህ ያለው " የድፍረት ኃጢአት እንዳይገዛኝ
ባሪያህን ጠብቅ የዚያን ጊዜ ፍጹም እሆናለሁ ከታላቁም ኃጢአት እነጻለሁ።" (መዝሙረ
ዳዊት 19: 13) ምን አልባት አንዳንድ ካህናት ሰለዚህ አይነት ኃጢአት ግንዛቤ ሳይኖራቸው
ቀርቶ ተክሊል ፍጽሚ ተክሊል ፈጽም ቢሉን እንኳን ራሳችንን ዝቅ በማድረግ አይገባኝም ልንል ያስፈልጋል።

አዘጋጅ ዲያቆን ፍቅረ አብ

ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን Tube ቻናል ተከታታዮች የተዘጋጀ!

https://www.youtube.com/channel/UCyyw8be1uLS-PdwVLd-zyKw

#subscribe ያርጉ ይቀላቀሉ እና ይማሩ

@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   


     join
3.1K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, 18:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 21:18:10 ሴጋ /ማስተርቤሽን/ የፈጸመ ሰው ተክሊል ይገባዋል?

ክፍል አንድ

በወጣትነት ወራት ሰለ አባል ዘር ሥራና ውጤት ለማወቅ ካለ ጉጉትና ለተቃራኒ ፆታ የሚኖር
ዝንባሌ ከመጨመሩ የተነሣ ወንዶችም ይሁኑ ሴቶች የመራቢያ አካላቸውን በመነካካት
ጾታዊ ሰሜት እንዲሰማቸውና የስሜት እርካታ እንዲያገኙ ሆን ተብሎ የሚፈጸም ተግባር
ሴጋ ወይም ግለ ወሲብ በመባል ይታወቃል።
የዚህ ጽሑፍ ዓላማ ሰለ ግለ ወሲብ በዝርዝር ማብራራት ሳይሆን ማስተርቤሽን የተባለውን
የዝሙት ኃጢአት የፈጸመ ሰው ተክሊል መፈጸም ይችላል ወይስ አይችልም የሚለውን
ጥያቄ ለመመለስ ነው። ተወዳጆች እያወራን ያለነው ከወንድ ጋር በአካል ዝሙት ፈጽማ
የማታውቅ ነገር ግን የዝሙትን ጣዕም ለማጣጣም ራሷን በራሷ ለማርካት ማስተርቤሽን
ቪዲዮ ሰለፈጸመች ኦርቶዶክሳዊ ሴት ወይም ከሴት ጋር በአካል ዝሙት ፈጽማ የማያውቅ
ነገር ግን የዝሙትን ጣዕም ለማጣጣም ራሱን በራሱ ለማርካት ማስተርቤሽን ሰለፈጸመ
ኦርቶዶክሳዊ ወንድ ነው። እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ከተቃራኒ ጾታ ጋር ምንም አይነት
ግንኙነት ሳያደርጉ ለእንደዚህ አይነት የዝሙት ተግባር በመጋለጣቸው ከሚያነሷቸው
ጥያቄዎች መካከል አንዱ ከወንድ ጋር በምንጣፍ አንድ አልሆንኩም ነገር ግን ማስተርቤሽን
ፈጽሚያለሁ ድንግል ልባል እችላለሁ ለደናግላን የሚፈጸመው ሥርዓተ ተክሊልስ ለእኔ
ልፈጸምልኝ ይችላል? የሚለው ዋነኛ ነው።
ይህ ጥያቄ በራሱ ተገቢነት የሌለው ትሕትና በማጣት ዲያቢሎስ እየፈተነን መሆኑ ማስረጃ
ነው። አንድ ኦርቶዶክሳዊ ከማንኛውም የዝሙት ተግባር እርቆ ከኖረ በኋላ ተክሊል
ሊፈጽምለት ሲል አረ አይገባኝም በማለት ራሱን ዝቅ ያደርጋል። ከዚህ በተቃራኒ ራስን በራስ
የማርካት የዝሙት ኃጢአት የኖረ ሰው ተክሊል ይገባሃል ቢባል እንኳን አረ እኔ አይገባኝም
ብሎ በተሰበረ ልብ ሊርቅ ሲገባው በማስተርቤሽን ኃጢአት የዝሙትን ተግባር ሲፈጽም ከኖረ
በኋላ ተክሊል ይገባኛል ብሎ መጠየቅ ልባችን በፈጸምነው ኃጢአት አለመሰበሩን ማረጋገጫ
ነው።
አንዲት ሴት ራሷን የዝሙትን የኃጢአት እርካታ የመራቢያ አካሏን በመነካካት እያረካች
ከኖረች በኋላ እንዴት ባለ ድፍረት ነው ተክሊል ይገባኛል ብላ የምትጠይቀው? ይቺ ሴት
ከወንድ የምታገኘውን የሩካቤ ሥጋ ግንኙነት ከራሷ እያገኘች ከሆነ ከጋብቻ ውጭ ከወንድ
ጋር ዝሙት ከሰሩት ሴቶች በምን ትለያለች? ምንም ከወንድ ጋር በምንጣፋ አንድ ባትሆን
በሕሊናዋ ወንድ ከማሰብ አልፋ በፈቃዷ አፈ ማኅፀኗን እየነካካች የዝሙትን ተግባር
ሰለፈጸመች ድንግል ተብላም አትጠራም።

በሉቃስ ወንጌል ላይ የሚገኝ አንድ ታሪክ አለ። ይህ ሕያው ታሪክ ከአባቱ ተለይቶ የኮበለለው
ልጅ ሕይወትን ያስነብበናል።ይህ ልጅ ከአባቱ ለመለየት መወሰኑ ስህተት መሆኑ ገብቶታል።
ሰለዚህም የሰራውን ስህተት ለማረም ሲነሳ ወደ አባቱ ለመመለስም ሲወስን እንዲህ ብሎ
ነው ያሰበው " ተነሥቼም ወደ አባቴ እሄዳለሁና አባቴ ሆይ በሰማይና በፊትህ በደልሁ ወደ
ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም ከሞያተኞችህ እንደ አንዱ አድርገኝ እለዋለሁ።" (የሉቃስ
ወንጌል 15:18-19 ) ይሄ ልጅ በአባቱ ላይ ማመጹ ኃጢአት መስራቱ ፈጽሞ እንደጸጸተው
የምንረዳው " ወደ ፊትም ልጅህ ልባል አይገባኝም" በሚለው ንግግሩ ነው። ወደ አባቱ ቤት
ሲመለስ ሰለመብቱ እያሰበ አልነበረም በልጅነት ክብር መጠራት እንደማይገባው አምኖል
ወደ አባቱ ቤት የተመለሰው በአባቱ ቤት ከሚሰሩት ሙያተኞች መካከል እንደ አንዱ ሁኖ
በባርነት ለማገልገል ነበር። ማስተርቤሽን ሲፈጽም የኖረም ሰው ኃጢአቱን አምኖ ወደ
እግዚአብሔር ሲመለስ ድንግል ልባል የደናግልና ሥርዓትም ሊፈጸምልኝ አይገባም በሚል
የተሰበረ መንፈስ ነው እንጂ በይገባኛል የሚል የትዕቢት ሐሳብ በልቡ ከያዘ መንፈሳዊ ኪሳራ
ውስጥ መሆኑ ግልጽ ጉዳይ ነው።
ከዚህም በተጨማሪ ማሽተርቤሽን ቪዲዮ ሴክስ ፎን ሴክስ ከፈጸሙ በኋላ " በአካል
ከተቃራኒ ጾታ ጋር ግንኙነት አላደረኩም ተክሊል መፈጸም ይፈቅድልኛል?" የሚል ጥያቄ
በአእምሮቸው የሚፈጠረው ፍቅር እግዚአብሔር ሲጎድልብንና ራስ ወዳድ ስንሆን ነው።
ምክንያቱም ማሽተርቤሽን ቪዲዮ ሴክስ ፏን ሴክስ የመሰለ ብዙ ኅብረ ዝሙት እየፈጸምን
ያሳሰበን በደልነቱ ሳይሆን ተክሊል መፈጸም አለመፈጸም መሆኑ ነው። እንዲህ አይነት
አስተሳሰብ " የቤተ ፈት" አስተሳሰብ ይባላል።
ቤተ ፈት የምትባለው ባል አግብታ እየኖረች ከጊዜ በኋላ ባሏን ፈትታ የኮበለለች ሴት ናት።
ከሄደችበትም ችግር ሲያጋጥማት የሚታያት ባሏን መበደሏ ሳይሆን ከባሏ ጋር በምትኖርበት
ጊዜ የነበራት ምቾትና ክብር ነው። አባታችን አዳምን ግን የቤተ ፈት ልማድ አላገኘውም።
ማለትም ኃጢአት ሠርቶ ከገነት በተባረሩ ጊዜ ፈጣሪዬን አስቀምኩት እያለ ስለ በደሉ ያለቅስ
ነበረ እንጂ የገነት ተድላ ደስታ ቀረብኝ እያለ ስላጣው ነገር አያዝንም ነበር። " አልቦቱ ካልዕ
ሕሊና ለአዳም ዘእንበለ ብካይ ላዕለ ኃጢአቱ ሰለ ኃጢአቱ ከማልቀስ በቀር ለአዳም ዘእንበለ
ብካይ አልነበረውም። የተባለው ሰለዚህ ነው።
እንደዚህ ሁሉ ሰው በልዩ ልዩ የዝሙት ኃጢአት በተስነካከለ ጊዜ "ድንግል ነኝን? ተክሊልስ
ይገባኛል? " እያለ ያጣውንና ያገኘውን እያሰበ ከመተከዝ " አንተን ብቻ በደልሁ በፊትህም
ክፋትን አደረግሁ ።" (መዝሙረ ዳዊት 51: 4) ማለት ኃጢአቱን እያሰበ ቢያለቅስ በንስሐ
አዳምን መስሎታልና የቤተ ፈት ልማድ አላገኘውም ይባላል።

ይቀጥላል.....

አዘጋጅ ዲያቆን ፍቅረ አብ

ከሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን Tube ቻናል ተከታታዮች የተዘጋጀ!

https://www.youtube.com/channel/UCyyw8be1uLS-PdwVLd-zyKw

#subscribe ያርጉ ይቀላቀሉ እና ይማሩ

@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   
@seratebtkrstian   


     join
2.9K viewsⒻⓔⓚⓡⓔ 🇦 🇧 🇪, 18:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ