Get Mystery Box with random crypto!

ቤተ ቅዱስ ሚካኤል

የቴሌግራም ቻናል አርማ saint_mikael — ቤተ ቅዱስ ሚካኤል
የቴሌግራም ቻናል አርማ saint_mikael — ቤተ ቅዱስ ሚካኤል
የሰርጥ አድራሻ: @saint_mikael
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.07K
የሰርጥ መግለጫ

ለእኛ በ አባታችን ቤት መሆን መልካም ነው
ለማንኛውም ሀሳብ እና አስተያየት
@Natnaelleulesegd
@Davedemaria
@natbitgola21
ይላኩልን
👇👇የYoutube Channel ይቀላቀላሉ👇👇
https://youtube.com/channel/UCqIww_vrxOATvuc5K_EDf1A?sub_confirmation=1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-05-09 14:09:33 ++ ሥነጽሑፍ - ግጥም !!

( ለደስታችን_ዜና_ለልደትሽ_ብሥራት )

#ለደስታችን_ዜና_ለልደትሽ_ብሥራት
#ምን_ስጦታ_እናምጣ_ለፈጣሪ_እናት፤
በመኑ ድንግል ሆይ በማን እንመስልሽ
ቃላት ቢረቃቸው አበው ወዳጆችሽ
በአርምሞ ሆነው እንዳመሰገኑ የልጅሽን ስራ
ከትውልዱ የሆንን በልደትሽ ደስታ እኛም ስንጠራ።
ዝም እንበል እንጂ ክብርሽ ቢረቅብን
ላንቺ ያልነው ሁሉ ስጦታ ቀሎብን
እንውደድሽ እንጂ እናድንቅሽ እንጂ በዕንባችን ዘለላ
ለልደት ስጦታ አንቺን የሚመጥን ምንም የለን ሌላ!
#ለደስታችን_ዜና_ለልደትሽ_ብሥራት
#ምን_ሻማ_እናብራልሽ_የብርሃን_እናት፤
ጨረቃችን ማርያም ተስፋችን እኮነሽ
በጨለማ ሳለን ጸሐይን የወለድሽ፤
የጸሐይ ማደርያው በእውነት ጸሐይ ነሽ
ከፍጥረታት ሁሉ መተኪያ የሌለሽ፤
ስለ ልዩ ፍቅርሽ ስለእናትነትሽ ያውም በልደትሽ
ሻማ ብናበራ የብርሃን እናት ከቶም ባይመጥንሽ
ታውቂናለሽና አቅም እንደሌለን አሰናብቺን ባርከሽ
በልደት ስጦታሽ በኛ ተደስተሽ #ለደስታችን_ዜና_ለልደትሽ_ብሥራት #ምን_ቅኔን_እንቀኝ_ለመላእክት_እህት
#ያልታደለ_እኮነው_አንቺን_ያላወቀ
#በሥጋ_እየኖረ_በነፍስ_የደቀቀ፤
አንቺን ለማመስገን ያልታደለስ ወየው
ልቡናው ታውሮ ልደትሽ ያልታየው፤
በቅዱስ ጋብቻ ቢሆንም ልደትሽ
ሰማያዊ ጸጋን አድሎሻል ልጅሽ፤
እንደምድር ልደት የሚያቃልሉሽን
አትነፍጊያቸውም ድንግል ሆይ ምልጃሽን፤
ባያውቁሽ ነው እንጂ እንዲህ ሚያቃልሉሽ
አንቺስ ከመላእክት ሁሉ ትበልጫለሽ
የመላእክት እህት ዛሬ የተወለድሽ
ምን ቃል አለንና ቅኔ እንዝረፍልሽ፤ #ለደስታችን_ዜና_ለልደትሽ_ብሥራት
#ምን_ሻማ_እናብራልሽ_የብርሃን_እናት፤
ያንቺ ልደት ማርያም ለኛም ልደታችን
የተሸነፈበት ሰይጣን ጠላታችን
ልደትሽ ብሥራት ነው ለክርስቶስ ልደት
እግዚአብሔር የሚያውቀው እረቂቅ ነው በእውነት።

አብርሃም በላይ

ከእለታት አንድ ቀን
https://t.me/halhjab2345
1.1K views21, 11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 14:35:41
948 views21, 11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 09:51:00 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡

❀ ሚያዝያ ፳፯ ❀

✞✞✞ እንኩዋን ለታላቁ ሰማዕት "ቅዱስ ፊቅጦር" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+*"+ ማር ፊቅጦር +"*+

=>ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን በደማቸውና በገድላቸው ያስጌጡ ብዙ ሰማዕታት አሉ:: ነገር ግን ከኮከብም ኮከብ ይበልጣልና ማን እንደ ጊዮርጊስና እስጢፋኖስ!

+ከእነርሱ ቀጥለው ከሚጠሩ ሰማዕታት ደግሞ አንዱና ዋነኛው ቤተ ክርስቲያን "ማር" የምትለው ቅዱስ ፊቅጦር ነው:: እስኪ ከበዛው መዓዛ-ገድሉ ጥቂት እንካፈል::

=>ቅዱስ ፊቅጦር አባቱ ኅርማኖስ ይባላል:: አረማዊና ጨካኝ ነው:: እናቱ ግን የተመሰገች ቅድስት ማርታ ትባላለች:: ልጇን እንደሚገባ አሳድጋው 20 ዓመት ሲሞላው የአንጾኪያ ንጉሥ የሠራዊት አለቃና በመንግሥቱ 3ኛ አድርጐ ሾመው::

+የድሮዋ አንጾኪያ (ሮም) እንደ ዛሬዋ አሜሪካ ዓለምን የተቆጣጠረች ሃገር ነበረች:: ቅዱስ ፊቅጦር ደም ግባቱ ያማረ: በጦርነትም ኃይለኛ ስለ ነበር ሁሉ ያከብሩት: ይወዱትም ነበር:: እርሱ ግን ቀን ቀን ሲጾም: ነዳያንን ሲያበላ ይውል ነበር::

+ሌሊት ደግሞ እኩሉን ሲጸልይና ሲሰግድ: እኩሉን የእስረኞችን እግር ሲያጥብ ያድር ነበር:: ይህ ሁሉ ሲሆንኮ እርሱ የንጉሡ 3ኛ: የሠራዊትም አለቃ ነው:: በዘመኑ የሚያገድፍ ምግብና የወይን ጠጅ በአፉ ዙሮ አያውቅም::

+ከነገር ሁሉ በሁዋላ ንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ካደ:: ዘመነ ሰማዕታትም ጀመረ:: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ:: ከ47 ሚሊየን በላይ ክርስቲያኖች በመንኮራኩር ተፈጩ: በመጋዝ ተተረተሩ: ለአራዊት ተሰጡ: በግፍም ተጨፈጨፉ:: ቀባሪ አጥተውም ወደቁ::

+በዚሕ ጊዜ ማር ፊቅጦር እናቱን ቅድስት ማርታን በዕንባ ተሰናብቶ ወደ ንጉሡ ቀርቦ በክርስቶስ ስም ታመነ:: ክፉ አባትም በልጁ ላይ ሞትን መከረ::

+ከዚያም ቅዱሱን አፉን በብረት ለጉመው ወደ ምድረ
ግብፅ አወረዱት:: መሪያቸው እንዳልነበረ ወታደሮቹ
መኳንንቱ ሁሉ
ተዘባበቱበት:: እርሱ ከምድራዊ ንግሥና ሰማያዊ
መንግስትን: በሰዎች ፊት ከመክበር ስለ ክርስቶስ ሲል
መናቅን መርጧልና::

+ለቀናት: ለወራትና ለዓመታት መኳንንቱ እየተፈራረቁ
አሰቃዩት:: በርሱ ላይ ያልሞከሩት የስቃይ ዓይነት
አልነበረም::
አካሉን ቆራርጠዋል: ዓይኖቹን አውጥተዋል: ምላሱንም
ቆርጠዋል::

+በዚሕች ዕለት ግን በሰይፍ አንገቱን ቆርጠውታል::
ስለዚህም እናት ቤተ ክርስቲያን በታላቅ ማክበር
ታከብረዋለች::
እግዚአብሔርም ለቅዱስ ፊቅጦር እንዲህ አለው:-

"እንደ
አቅሙ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ስምህን
ያከበረ:
የብርሃን ልብስ አጐናጽፌ ወደ መንግስተ ሰማያት
አስገባዋለሁ::"

❖ቸሩ አምላከ ፊቅጦር ሁላችንም ይማረን:: ከቃል ኪዳኑ
አሳትፎ ለርስቱ ያብቃን::

❖ሚያዝያ 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ጽኑዕና ኃያል ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
2.ቅድስት ማርታ (የፊቅጦር እናት)
3.ብጽዕት እስጢፋና (በክርስቶስ ስላመነች ከ2
ሰንጥቀው የገደሏት የ15 ዓመት ወጣት)
4.ቅዱሳን ሳሲማና አባ ኖባ (ሰማዕታት)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.የጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በዓለ
ስቅለት
2.አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
3.ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ) 4.ቅዱስ
ያዕቆብ ዘግሙድ
5.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
6.ቅዱስ
ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት

++"+ እግዚአብሔር ቅዱሳንን ስላገለገላችሁ: እስከ
አሁንም ስለምታገለግሏቸው ያደረጋችሁትን ሥራ:
ለስሙም ያሳያችሁትን
ፍቅር ይረሳ ዘንድ ዓመጸኛ አይደለምና:: በእምነትና
በትእግስትም የተስፋውን ቃል የሚወርሱትን እንድትመስሉ
እንጂ ዳተኞች
እንዳትሆኑ ተስፋ እስኪሞላ ድረስ እያንዳንዳችሁ ያን
ትጋት እስከ መጨረሻ እንድታሳዩ እንመኛለን::+"+ (ዕብ.
6:10-13)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://t.me/saint_mikael
935 views21, 06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 22:07:10 ንጉሡም ዳግመኛ ቅዱስ ጊዮርጊስን ‹‹በመንግሥቴ ልሹምህ ለአጵሎን ስገድ›› ቢለው ቅዱስ ጊዮርጊስም ሊያሾፍበት በማሰብ ‹‹እሺ›› ብሎ ወደ ንጉሡ ቤተ መንግሥት ገብቶ የንጉሱን ሚስት ንግሥቲቱን እለእስክንድርያን አስተምሮ አሳምኗታል፡፡ በነጋም ጊዜ ንጉሡ በአዋጅ ሕዝቡን ሁሉ ሰብስቦ ‹‹ጊዮርጊስ ለጣዖቴ ሊሰግድ ነውና ኑ ተመልከቱ›› ብሎ ተናገረ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም በተሰበሰበው ሕዝብ መካከል አንድን ብላቴና ጠርቶ ‹‹የክርስቶስ ኢየሱስ አገልጋይ ጊዮርጊስ ይጠራሃል ብለህ ለጣዖቱ ንገረው›› ብሎ ላከው፡፡ ብላቴናውም ወደ ጣዖት ቤቱ ገብቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እንዳለው ተናገረ፡፡ በዚህም ጊዜ በጣዖቱ ላይ ያደረው ሰይጣን እየጮኸ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለበት ቦታ ድረስ መጣ፡፡ በንጉሡና በሕዝቡም ሁሉ ፊት አምላክ አለመሆኑን ይልቁንም አሳች ሰይጣን መሆኑን በመናዘዝ ከተናገረ በኋላ ቅዱስ ጊዮርጊስ መሬት ተከፍታ እንድትውጠው አደረገው፡፡

ይህንንም ተዓምር ያዩ ሁሉ ብዙዎች ‹‹በጊዮርጊስ አምላክ አምነናል›› እያሉ በጌታችን አመኑ፡፡ የንጉሡም ሚስት እለእስክንድርያ በቅዱስ ጊዮርጊስ አምላክ ካመነች በኋላ ባሏን ከክፋቱ ተመልሶ እንዲያምን ብትለምነውና ብትመክረውም አልሰማት አለ፡፡ ይልቁንም ንጉሡ በአደባባይ በሕዝቡ ሁሉ ፊት የገዛ ሚስቱን አሠቃይቶ ሰውነቷን ቆራርጦ ሰቅሎ አንገቷን በመሰየፍ ሰማዕትነት እንድትቀበል አደረጋት፡፡ ቅድስት እለእስክንድርያም ቅዱስ ጊዮርጊስን ‹‹ሳልጠመቅ አልሙት›› ስትለው እርሱም ‹‹ደምሽ ጥምቀት ሆኖልሻልና እነሆ የክብር አክሊል እየጠበቀሽ ስለሆነ አይዞሽ›› ብሎ አጽንቷታል፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ጊዮርጊስ ከጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ታላቅ ቃልኪዳን ከተቀበለ በኋላ በ27 ዓመቱ በሚያዝያ 23 ቀን ሰማዕትነቱን በድል ፈጽሞ የክብር አክሊልን ተቀዳጀ፡፡ አንገቱም ሲቆረጥ ውሃ፣ ደምና ወተት ወጥቷል፡፡ ከሥጋውም እጅግ ብዙ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታይተዋል፡፡ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!!
(ምንጭ፡- ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ፣ ስንክሳር ዘወርሃ ሚያዝያ)
https://t.me/saint_mikael
880 viewsDave, edited  19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 22:07:10 መልእክተኛውን ሰው ጌታው ወደንጉሡ አስተዳደር በላከው ጊዜ ሦስት ቀን የሚያስኬደውን ሩቅ መንገድ በአንዲት ሰዓት ውስጥ አድርሰህ የመለስከው ኃያሉ ሰማዕት ፀሐይ ዘልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! እኛንም በአማላጅነትህ የምታመን ልጆችህን ከእርኩሰት የበደል ጎዳና በረድኤትህ መልሰን!
ሚያዝያ 23 ቀን የልዳው ፀሐይ የቅዱስ ጊዮርጊስ የሰማዕትነቱ ፍጻሜው ነውና እጅግ የበዛውን ገድሉን በጥቂቱ ብንመለከተው ለበረከት ይሆነናል፡፡ ይኸውም ታላቅ ሰማዕት ለጣኦት ካልሰገድክ ብለው 70 ነገሥታት በጋራ ሆነው ለ7 ዓመታት እጅግ አሠቃቂ መከራዎችን ያደረሱበት አጥንቱንም ፈጭተው ደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የበተኑት ነው፡፡ ሦስት ጊዜ ሲገድሉትም ጌታችን ሦስት ጊዜ ከሞት እያስነሣው ከሃድያንን ያሳፈረ ሲሆን ሰማዕትነቱን ፈጽሞ አንገቱ ሲቆረጥም ደም ውኃና ወተት ከአንገቱ ፈሰሰና ብዙዎችን አሳመ፡፡
ዳግመኛም በዚኽ ዕለት ጌታችን ተገልጦለት ከንዳድ በሽታ የሚጠብቅ ታላቅ ቃልኪዳን የገባለት ጻድቁ አባ ርቆ ዕረፍቱ ነው፡፡ ረድኤት በረከቱ ይደርብን በጸሎቱ ይማረን!!
ሊቀ ሰማዕታት ፀሐይ ዘልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ፡- ጊዮርጊስ ማለት ‹‹ኮከብ ብሩህ፣ ፀሐይ›› ማለት ነው፡፡ ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ሀገሩ ፍልስጤም ልዩ ስሟ ልዳ ሲሆን የተወለደው በ277 ዓ.ም ጥር 20 ቀን ነው፡፡ ጊዮርጊስ ማለት ኮከብ፣ ብሩህ፣ ሐረገ ወይን፣ ፀሐይ ማለት ነው፡፡ አባቱ ዞሮንቶስ ወይም አንስጣስዮስ የልዳ መኳንንት ሆኖ ተሹሞ ይኖር ነበር፤ እናቱ ቴዎብስታ ወይም አቅሌስያ ከቅዱስ ጊዮርጊስ ሌላ ማርታና እስያ የሚባሉ ሁለት ሴት ልጆችን ወልዳለች፡፡
ቅዱስ ጊዮርጊስ ዐሥር ዓመት በሆመው ጊዜ አባቱ ስለሞተ ሌላ ደግ ክርስቲያናዊ መስፍን ወስዶ አሳደገው፡፡ መድፍኑም በጦር ኃይል አሰለጠነው፡፡ ሃያ ዓመትም በሞላው ጊዜ መስፍኑ የ15 ዓመት ቆንጆ ልጅ ነበረችውና እርሷን አግብቶ ሀብቴን ወርሶ ይኑር ብሎ ድግስ ሲያስደግስ ጌታችን ቅዱስ ጊዮርጊስን ለዚህ አላጨውምና የመስፍኑን ነፍስ ወሰደ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ኀዘኑን ጨርሶ ወደ ቤሩት ሀገር ሄደ፡፡ በቤሩት ደራጎንን ያመልኩና ሴት ልጆቻቸውን ይገብሩለት ስለነበር ሰማዕቱ ደራጎኑን በኃይለ መስቀል ድል ነስቶት ሕዝቡን ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር አስገብቷቸዋል፡፡

ወደፋርስ ቢመለስ ዱድያኖስ ሰባ ነገሥታት ሰብስቦ ሰባ ጣዖታት አቁሞ ሲሰግድ ሲያሰግድ ቢያገኛቸው ለሃይማኖቱ ቀናዒ ነውና ከቤተመንግስቱ ገብቶ በከሃዲያኑ ሰባው ነገሥታት ፊት ክርስቲያን መሆኑን በመመስከር የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መሰከረ፡፡ ዱድያኖስም ማንነቱን ከተረዳ በኋላ ‹‹አንተማ የኛ ነህ በዐሥር አህጉር ላይ እሾምሃለሁ የኔን አምላክ አጵሎንን አምልክ›› አለው፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ‹‹ሹመት ሽልማትህ ለአንተ ይሁን እኔ አምላኬ ኢየሱስ ክርስቶስን አልክደውም›› አለው፡፡ በዚህ ጊዜ ዱድያኖስ እጅግ ተናዶ ብዙ አሠቃቂ መከራዎችን አደረሰበት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ጌታችንን ‹‹ይህን ከሃዲ እስካሳፍረው ድረስ ነፍሴን አትውሰዳት›› በማለት መከራውን ይታገስ ዘንድ ለመነው፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ፈቃዱን ይፈጽምለት ብዙ በመከራው ሁሉ ጽናትን ሰጥቶታል፡፡ ሦስት ጊዜም ከሞት አስነሥቶታል፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም የደረሱበት እጅግ አሠቃቂ መከራዎች የሰው ኅሊና ሊያስባቸው እንኳን የማይችላቸው ናቸው፡፡

በመጀመሪያም ዱድያኖስ በእንጨት ላይ ካሰቀለው በኋላ ሥጋውን በመቃን አስፈተተው፣ ረጃጅም ችንካሮች ያሉበት የብረት ጫማ አጫምቶት ሂድ አለው፡፡ ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልን ልኮለት ፈውሶታል፡፡ ዳግመኛም በሰባ ችንካሮች አስቸንክሮ በእሳት አስተኩሶ አናቱን በመዶሻ አስቀጥቅጦ በሆዱ ላይ የደንጊያ ምሰሶ አሳስሮ እንዲያንከባልሉት አደረገ፡፡ ሥጋውንም በመጋዝ አስተልትሎ ጨው ነሰነሰበት፡፡ ሥጋውም ተቆራርጦ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈቀ ሌሊት በእጁ ዳስሶ ከፈወሰውና ‹‹ገና ስድስት ዓመት ለስሜ ትጋደላለህ፣ 3 ጊዜ ትሞታለህ፣ በ4ኛውም ታርፋለህ›› ካለው በኋላ በመከራውም ሁሉ እርሱ እንደማይለየው ነገረው፡፡

ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ከዚያ ካደረሰበት አሠቃቂ መከራዎች ሁሉ ድኑ ፍጹም ጤነኛ መሆኑን በተመለከተ ጊዜ እጅግ ደንግጦ ‹‹የሚያሸንፍልኝ ቢኖር ብዙ ወርቅ እሰጠዋለሁ›› ብሎ ተናገረ፡፡ አትናስዮስ የተባለ መሰርይ አንዲትን ላም በጆሮዋ ሲያንሾካሹክባት ለሁለት ተሰንጥቃ ስትሞት ለንጉሡ አሳየውና ቅዱስ ጊዮርጊስን እንዲሚያሸንፍ ምልክት አሳየ፡፡ ንጉሡም ያሸንፍልኛል ብሎ ደስ አለው፡፡ መሰርይውም ሆድ በጥብጦ አንጀት ቆራርጦ የሚገድል መርዝ ቀምሞ አስማተ ሰይጣን ደግሞበት እንዲጠጣው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰጠው። ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን ስመ እግዚአብሔርን ጠርቶ ቢጠጣው እንደ ጨረቃ ደምቆ እንደ አበባ አሸብርቆ ተገኝቷል፡፡ በዚህም ጊዜ ጠንቋዩ ማረኝ ብሎ ከእግሩ ሥር ወደቀ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም መመለሱን አይቶ የቆመባትን መሬት በእግሩ ረግጦ ውሃን አፍልቆ ወደ ጌታችን በጸሎት ቢያመለክት ሐዋርያው ቶማስ በመንፈስ መጥቶ አጠመቀው፡፡ እርሱም ስለጌታችን አምላክነት መስክሮ ጥር 23 ቀን አንገቱን ለሰይፍ ሰጥቶ በሰማዕትነት ዐርፏል፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ ግን በመንኰራኩር አስፈጭቶ ከትልቅ ጉድጓድ ጥሎት ደንጊያ ዘግቶበት አትሞበት ሄደ፡፡ ጌታችንም የተፈጨውን የቅዱስ ጊዮርጊስ ሥጋ በእጁ ዳስሶ ፈውሶታል፡፡ ወደ ከሃዲውም ንጉሥ ተመልሶ ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› በማለት መሰከረ፡፡ ንጉሡም ዳግመኛ በብረት አልጋ አስቸንክሮ ከበታቹ እሳት አነደደበት ነገር ግን እሳቱ ደሙ ሲንጠባጠብበት ጠፍቷል፡፡ ጌታችንም ፈወሰው፡፡ ከዚህም በኋላ ዱድያኖስ ቅዱስ ጊዮርጊስን ‹‹ኢየሱስ አምላክ መሆኑን አሳየኝ›› ቢለው የለመለሙትን ዕፅ አድርቆ፣ የደረቁትን ደግሞ አለምልሞ፣ ከሞቱ 430 ዓመት የሆናቸውን ሙታንን አስነሥሰቶ አሳይቶታል፡፡ ነገር ግን ንጉሡ ልቡ ክፉ ነውና በርኃብና በጽም ይሙት ብሎ ምንም ከሌላት መበለት ቤት አሳስሮታል። እርሷም የሚቀመስ ስትፈልግ ቤቷን በእህል አትረፍርፎ የታሰረበትን ግንድ ማለትም የቤቱን ምሰሶ አለምልሞታል፡፡ ልጇም ጆሮው የማይሰማ ነበርና ፈወሰላት፡፡ መበለቲቷንም ከነልጆቿ አጥምቆአቸው መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከእስራቱ ፈትቶት ተመልሷል፡፡

ዳግመኛም ንጉሡ ዱድያኖስ ጭፍሮቹን ‹‹በመንኰራኩር ፈጭታችሁ አጥንቱን ደብረ ይድራስ ተራራ ላይ ወስዳችሁ ዝሩት›› ብሎ አዘዛቸው፡፡ ጭፍሮቹም የቅዱስ ጊዮርጊስን ሥጋ በመንኰራኩር ፈጭተው ወስደው በተራራው ላይ ቢረጩት ሥጋው ያረፈበት ሳር፣ ቅጠሉ፣ ደንጊያው፣ እንጨቱ ሁሉ ‹‹ጊዮርጊስ ቅዱሱ ለእግዚአብሔር፣ ጊዮርጊስ ሰማዕቱ ለእግዚአብሔር›› እያሉ አመስግነዋል፡፡ አሁንም ጌታችን ለሦስተኛ ጊዜ ከሞት አስነሣውና ሥጋውን ፈጭተው በተራራም ላይ ሥጋውን በትነውት ወደ ንጉሡ የሚመለሱትን ወታደሮች በመንገድ ከኋላቸው ሄዶ ደረሰባቸውና ‹‹ቆዩኝ ጠብቁኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እጅግ ደንግጠው ይህ እንዴት እንደሆነ ሲጠይቁት ‹‹አምላኬ ከሞት አዳነኝ›› አላቸው፡፡ ጭፍሮቹም እጅግ ደንግጠው ከእግሩ ስር ወድቀው ይቅር በለን ብለው በአምላኩ እንደሚያምኑ መሰከሩለት፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ከመሬት ላይ ውሃ አመንጭቶ በጸሎት ጌታችንን ቢጠይቅ ቅዱስ ዮሐንስ መጥቶ አጥምቋቸዋል፡፡ እነርሱም በንጉሣቸው ፊት ሄደው ስለጌታችን በመመስከር በሰማዕትነት ዐርፈዋል፡፡
636 viewsDave, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 22:07:10 ሚያዝያ 23 - እንኳን ለሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ

( በገብረ ሥላሴ)
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
ሚያዝያ 23 ‹‹ጸሎቱና በረከቱ ለሁላችን ይደረግልንና ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገው ተአምር ይኽ ነው፡

ብባ ከምትባል አገር ሰዎች ወገን የሆነ አንድ አረማዊ ሰው ነበረ፡፡ መካ የሚገኘውን መስጊድ ለመጎብኘት ወደ ምድረ ኅልዛዝ ሄደ፡፡ በዚኽም ቦታ ዲያብሎስ ከነሠራዊቱ ከሰማይ ወደ ምድር የወደቀበት ነው፡፡ ዳግመኛም የአትሪብን አገር ነቢይ መቃብር ይጎበኝ ዘንድ ሄደ፡፡ ጉብኝቱንም ከፈጸመ በኋላ ከጓደኞቹ ጋር ወደ ሀገሩ ተመልሶ እየሄደ ሣለ ወደኋላ ዘግይቶ ቆየና በዱር ብቻውን ቀረ፡፡ መሪር ልቅሶንም አለቀሰ፡፡ መድሪቱም በጣም በረሃ ናትና ምንም የለባትም፣ ይልቁንም የዘላን ወይም የሽፍታ መኖሪያ ነበረች፡፡ አረማዊውም ወደ ነቢያቸውና ወደ ጓደኞቹ ቢጮኽ ማንም ለእርዳታ የሚደርስለት አላገኘም፡፡ በዚኽም ጊዜ በጭንቅና በፍርሃት ሆኖ በመከራ ጊዜ ስሙ ሲጠራ ይሰማው የነበረውን የቅዱስ ጊዮርጊስን ስም እየጠራ እንዲረዳው እየጮኸ ለመነ፡፡ ወዲያውም ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ መጥቶ በፈረሱ ላይ አፈናጠጠውና እንደ ዓይን ጥቅሻ ፈጥኖ ብባ ከምትባለው ሀገሩ አደረሰውና ከእርሱ ተሰወረ፡፡ የመጣበትም ሀገር ጎዳና ሦስት ወር ያህል የሚያስኬድ ነበር፡፡ ሰውየውም ይኽን ታላቅ ተአምር ከተመለከተ በኋላ ልቡ ተሰወረ፣ እንደሕማም ሆነበት፡፡ አእምሮውንም ካወቀ በኋላ ግን ተነሥቶ ወደ ቤቱ ገባ፡፡
‹የሀገሩ ሰዎችም ሌሎቹ ሰዎች ወይም ጓደኞችህ ከመምጣታቸው በፊት ከዚያ ከሩቅ አገር አንተ ብቻህን እንዴት መጣህ?› ብለው ጠየቁት፡፡ እርሱም ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በፈረሱ ላይ አፈናጦ በቅጽበት ወደ ሀገሩ እንዳመጣው ነገራቸውና ምልክትም ትሆነው ዘንድ ከመካ ያመጣትን ከሸክላ የተሠራችና የሰጎን እንቁላል የምትመስል ነገር አሳያቸው፡፡ እነርሱም በሰሙት ነገር እጅግ ተደነቁ፡፡ ሰውየውም ወደ ቅዱስ ጊዮርጊስ ይዞ ሄዶ ያችን ምልክት ለኤጲስ ቆጶሱ ሰጠውና ኃያሉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገለትን እርዳታ ከሩቅ አገር እንዴት አድርጎ እንደዐይን ጥቅሻ በቅጽበት እንዳመጣው ነገረው፡፡ እስከመጨረሻውም ድረስ ለዚኽ ተአምር መታሰቢያ ሆኖ ይኖር ዘንድ ከቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ይሰቅለው ዘንድ ለመነው፡፡ ኤጲስቆጶሱም በቅዱስ ጊዮርጊስ ሥዕል አንጻር መጻሕፍት እንደሚነበቡባቸው ያለ ከፍተኛ ቦታ ላይ አስቀመጣት፡፡ በወቅቱም የቅዱስ ጊዮርጊስን ገድል የጻፈው ሰውም ወደዚያች ቤተ ክርስቲያን ሄዶ ያችን ምልክት እንዳያት በጻፈው የሰማዕቱ ገድል ላይ ጠቅሶታል፡፡ ያች እንቁላል መሰል ሸክላ በመካ ሀገር ከሚገኝ መስጊድ በስተቀር ሌላ የትም ቦታ ላይ አትሰቀልም ነበር፡፡ የገድሉ ጸሐፊም ይህን ጠቅሶ ኤጲስቆጶሱን እንዴት ይህችን ሸክላ ከቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንደሰቀሏት ጠየቀው፡፡ ኤጲስቆጶሱም ኃያሉ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ለአረማዊው ያደረገለትን ተአምር ከምድረ አልኅዛዝ በፈረሱ ላይ አፈናጦ እንደዐይን ጥቅሻ ወደ ሀገሩ በማምጣት ከሞት እንዳዳነው ነገረው፡፡ ያችንም እንቁላል መሰል ሸክላ በመታሰቢያ በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ እንዲሰቅልለት አረማዊው እንደለመነው ነገረው፡፡
የገድሉ ጸሐፊም በቅዱሳን አድሮ ድንቅ ድንቅ ነገርን የሚሠራ ልዑል እግዚአብሔርን እያመሰገነ ታሪኩን ከገድሉ ጋር ጻፈው፡፡ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ጸሎቱ በረከቱ ለሁላችን በዕውነት ይደረግልን አሜን!››
ዳግመኛም ቅዱስ ጊዮርጊስ ለዚያ አረማዊ ሰው ታላቅ ተአምር ባደረገባት በዚያች ብባ በምትባል አገር የሚኖር አንድ አረማዊ ነበር፡፡ እርሱም ቅዱስ ጊዮርጊስን የሚወድ በየዓመቱም በዕረፍቱ ዕለት ሚያዝያ 23 ቀን ብዙ በግና ፍየል እያረደ ዝክሩን የሚዘክር ነው፡፡ ለበዓሉም የሚያስፈልጉትን ሁሉ እያዘጋጀ ያቀርባል፡፡ በሥራውም ሁሉ በቅዱስ ጊዮርጊስ ይታመናልና ስለዚህም ነገር አረማውያን ጓደኞቹ ቀኑበት፡፡ ክርስቲያኖችን ወደሚጠላው አገረ ገዥ ዘንድ ሄደው የቅዱስ ጊዮርጊስን በዓልም እንዳያደርግ ከሦስት ቀን በፊት ከሰሱት፡፡ ገዥውም ፈጽሞ በመቆጣት ደብዳቤ ጻፈና አትሞ አሽጎ ለዚያ የቅዱስ ጊዮርጊስ በዓል ለሚያክር አረማዊ ሰው ሰጠውና እልቅሐራ ወደምትባል ሩቅ አገር ደብዳቤውን በፍጥነት ወስዶ በዚያ ላለው ገዥ ይሰጥ ዘንድ አዘዘው፡፡ እንዲከታተሉትም ወታደሮችን አብረው እንዲሄዱ አዘዘ፡፡ ይኽንንም ያደረገው በዓሉን እንዳያደርግ ሊያስታጉለው ፈልጎ ነው፡፡
ያ አረማዊና ጭፍሮቹም መጓዝ ጀምረው ከከተማው ውጭ እየሄዱ ሣሉ አረማዊው ‹‹ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ! የበዓልህን መታጎል ተመልከት…›› እያለ ጸለየ፡፡ ወዲያውም ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ በነጭ ፈረስ ላይ ተቀምጦ ተገለጠለትና ‹‹አይዞህ አትፍራ ና›› ብሎ እጁን ይዞ ከፈረሱ ላይ አስቀመጠውና እንደዐይን ጥቅሻ በቅጽበት ወስዶ ገዥው ካዘዘበት እልቅሐራ አገር ከገዥው ደጃፍ አደረሰው፡፡ ዳግመኛም ‹‹ሂድ ግባ የተላከውን ደብዳቤ አድርስ፣ መልሱንም ጽፎ ይሰጥሃል፣ እኔም እስክትመለስ ድረስ ከዚህ ቆሜ እጠብቅሃለሁ›› ብሎ ላከው፡፡
ገዥውም የተጻፈለትን ደብዳቤ ካነበበ በኋላ መልሱን ጽፎ ሰጠው፡፡ እርሱም ፈጥኖ ወደውጭ ቢወጣ ቅዱስ ጊዮርጊስን በፈረሱ ላይ እንደተቀመጠ እየጠበቀው አገኘውና እጅግ ደስ አለው፡፡ ሰማዕቱም ዳግመኛ ከፈረሱ ላይ አፈናጠጠውና በቅጽበት አረማዊውን ወደመጣበት አገር አደረሰውና ‹‹ወደቤትህ ግባና እንደልማድህ የበዓሌን መታሰቢያ አድርግ›› አለው፡፡ ያም አረማዊ ሰው በፍጹም ደስታ ደስ ተሰኝቶ ወደቤቱ ሄዶ ለበዓሉ የሚያስፈልገውን ሁሉ ከቀድሞ አስበልጦ አዘጋጀና ወስዶ ለኤጲስቆጶሱ ሰጠው፡፡
እነዚያ መጀመሪያ ላይ የቅዱስ ጊዮርጊስን በዓል እንዳያደርግ ለማስታጎል ብለው የከሰሱት አረማውያን ሰዎችም ዳግመኛ ወደገዥው ዘንድ ሄደው ‹‹እነሆ ያ ወደሩቅ ሀገር ደብዳቤ ይዞ እንዲሄድ ያዘዝከው ሰው በአንተ ላይ ተዘባበተብህ፣ ሳይሄድ ቀርቶ እርሱ ግን የጊዮርጊስን በዓል ለማክበር ይዘጋጃል›› ብለው ዳግመኛ ከሰሱት፡፡ ገዥውም እጅግ ተናዶ አስመጥቶ ጠየቀው፡፡ ሰውየውም ‹‹ጌታዬ ወደላከኝ አገር መልእክትህን አድርሻለሁ፣ የመልእክትህም መልስ እነሆ›› ብሎ የመልሱን ደብዳቤ ሰጠው፡፡ ገዥውም የመልሱን ደብዳቤ ባነበበው ጊዜ እርሱ ጽፎ በላከበት ዕለት የተጻፈ ደብዳቤ መሆኑን አረጋገጠ፡፡ በዚህም እጅግ ተገርሞ ‹‹ይህ መንገድ ለ3 ቀን ያህል የሚያስኬድ በጣም ሩቅ አገር ሆኖ ሳለ አንተ እንዴት በቅጽበት ደረስህ/›› ብሎ ጠየቀው፡፡ ሰውየውም ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ያደረገለትን ድንቅ ነገር በዝርዝር ነገረው፡፡ እነዚያ አብረውት ይሄዱ ዘንድ የተላኩት ጭፍችሮችም ከ6 ቀን በኋላ ተመልሰው መጥተው አረማዊው ከእነርሱ በዕለቱ ተለይቶ እንደነበር እነርሱ ግን ወደታዘዙብ አገር ደርሰው እንደመጡ ተናገሩ፡፡ አገረ ገዥውም ስለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ታላቅ ተአምርና ገናናት ፍርሃት አደረበት የሚቀስፈው መስሎታልና፡፡ የአገሩ ሰዎችም ሁሉ በተደረገው ታላቅ ተአምር ተደንቀው ፍርሃት አደረባቸው፡፡ ገዥውም ኤጲስቆጶሱን ጠርቶ ሁልጊዜም በየዓመቱ የቅዱስ ጊዮርጊስን በዓል ማክበሪያ የሚሆን ብዙ ገንዘብና ለበዓሉ ዝግጅት አስፈላጊ የሆነውን ሁሉ አሟልቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ሰጠ፡፡
645 viewsDave, 19:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-30 22:06:19
596 viewsDave, 19:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ