Get Mystery Box with random crypto!

SadatKemal Abu Meryem

የቴሌግራም ቻናል አርማ sadatkemalabumeryem — SadatKemal Abu Meryem S
የቴሌግራም ቻናል አርማ sadatkemalabumeryem — SadatKemal Abu Meryem
የሰርጥ አድራሻ: @sadatkemalabumeryem
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 119.45K

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-09-19 18:24:49

23.3K views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-19 17:41:45

22.0K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-19 11:32:19
ሚንሐጁ አል-ፊርቀቲ ናጂያ
ክፍል 20
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/5794
የኪታቡን ፒዲኤፍ ከማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጫኑ
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/5014
12.9K views08:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-18 17:47:26
ነብዩን አትወዳቸውም?
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/3591
15.2K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-18 17:47:26 ነብዩን አትወዳቸውም?
15.0K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-18 17:45:09 “መውሊድ”፣ “ክሪስማስ”፣ አሹራ….?
***********
ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃ
ባዎቻቸው በላይ አውቀው ነው ወይ?
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ነብይ ተደርገው በተላኩ ጊዜ ነሷራዎችም (ክርስትያኖች) ይሁዳዎችም ነበሩ፡፡ ነሷራዎች የኢሳንም ልደት ሲያከብሩ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የወንድማቸውን ኢሳ ልደት አንድም ቀን አክብረው አያውቁም፡፡ ምክንያቱም በአላህ አልታዘዙምና፡፡ የነብይም ይሁን የሌላ ግለሰብ የልደት በዓል ማክበር የነብያቶች እምነት እስልምና በፍፁም የሚያውቀው አይደለም፡፡ ልደት ማክበር የእስልምና አካልም አይደለም፡፡በሌላ በኩል ሌላኛው ወንድማቸው ነብየላህ ሙሳን (አለይሂ ሰላም) አስመልክቶ የሁዳዎች አሹራን ሲፆሙ አዩ፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የሁዳዎችን ለምን እንደሚፆሙ ጠየቁ “አላህ ሙሳን እና የእስራኢል ልጆችን ከፊርዐውን ነፃ ያወጣበት ቀን ነው” ሲሉ መለሱላቸው፡፡ ነብዩም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “እኛ በሙሳ ጉዳይ ከናንተ የበለጠ የተገባን ነን” ብለው አሹራን ፆሙ እንዲፆምም አዘዙ፡፡ እንዲያውም ረመዳን ከመደንገጉ በፊት አሹራ በሙስሊሞች ላይ ግዴታ ነበር፡፡ ከረመዳን በኋላ ይሀው እኛም የሳቸውን ፈለግ በመከተል እንፆመዋለን፡፡ ልክ እንደዚሁ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሰኞ ለምን እንደሚፆሙ” ሲጠየቁ “የተወለድኩበት ቀን ስለሆነ እና ቁርዐን እኔ ላይ የወረደበት ቀን ስለሆነ ነው” ብለዋል፡፡ ታድያ ግዴታ ያልሆነ የሱና ፆም አሹራን በአመት አንዴ እንድንፆመው፣ እሳቸው የተወለዱበትን ቀን እና ቁርዓን የወረደበትን ቀን ሰኞ እንዲሁ በሳምንትን አንዴ ሱና ፆም እንድንፆም ነግረውናል፡፡ የሚያሳዝነው አብዛኛው “መውሊድን” አከብራለሁ የሚል ሰው የታዘዘውን በየሳምንቱ የሚፆመውን ሱና ሲፆም አይታይም፡፡ ይልቁንስ ለምሳሌ “የኢስነይን ሰዎች ነን” እያሉ ሰኞ ሰኞ ጉንጫቸውን በአንደንዛዡ ቅጠል ጫት ወጥረው ሲቅሙ እና ሲጨፍሩ የሚውሉ ሸይጧን የተጫወተባቸው አሉ፡፡ በአመት አንዴ ግን ያልታዘዙትን “መውሊድ” ብለው በማክበር “የኢሳ ልደት” ብለው ከሚያከብሩት ሰዎች ጋር ተመሳስለዋል፡፡ የታዘዙትን ትተው ያልታዘዙትን በመስራት ወደ አላህ እዝነት ሳይሆን ቁጣውን ወደሚያከናንባቸው የሰይጣን መንገድ የሚንደረደሩ ሰዎች ምን አለ ቆም ብለው ቢያስቡ?
አላህ እኮ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) በመከተል እንጂ ውዴታውን እና ምህረቱን ቃል የገባልን ያላዘዙትን በመስራት አይደለም፡፡ ሸይጧን ደግሞ እንዲህ አሳቢ መስሎ ነው ከጥንት እስከዛሬ ሰዎችን ሲያጠም የነበረው፡፡ አላህ ከተንኮሉ ይጠብቀን፡፡
ሌላው ሰሃባዎች አላህ አማኝ፣ እውነተኞች፣ ወድጃቸዋለሁ እያለ ያወደሳቸው….. ከነሱ መንገድ ውጭ ያለን የሚከተል መንገድ የሳተ፣ ጀሀነምም እንደሚገባ አላህ እና መልክተኛው ነግረውን ሲያበቁ፡፡ ለምን ይሆን መውሊድንም ይሁን ሌሎች ተግባራትን በተመለከተ ሰሃባዎች የቆሙበት ቦታ የማንቆመው?
ሰሃባዎች ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በህይወት በነበሩ ግዜም ይሁን ሞተው አንድም ቀን የማንንም ነብይ ይሁን የረሱልን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ልደት አክብረው አያውቁም፡፡
ታድያ እኛ ማን ሆነን ነው ሰሃባዎች ያልሰሩትን የምንሰራው? የአላህን ዲን፣ ንፁሁን የነብዩ ሱና በቢድዐ ለማቆሸሽ፣ የሰይጣንን ተልኮ “ነብዩን መውደድ” በሚል ስም ለማሳካት ደፋ ቀና የሚባለው?
እውነት ሰሃባዎች ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሳይወዱ ቀርተው ነው የነብዩን መውሊድ ያላከበሩት?
ወይንስ እነሱ ለነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላቸው ውዴታ ሸሪዐ በደነገገው መልኩ በገንዘብ፣ በህይወት መስዋትነት እና በሌላም ስለገለፁ ነው?
እውነታው እነሱ ስለስርዐት አላቸው፡፡ ይህንን ከሰማይ የወረደ ዲን “እኔ እንደሚመስለኝ” እያሉ ሳይዳፈሩ ያንን ንፁህ ምንም ጭማሪ የማይፈልግ ዲን ለእኛ በሰላም አድርሰዋል፡፡ አላህም ወዷቸዋል፡፡ ዛሬ አላህ ዘንድ ገና ፍርድ ያልተሰጠባቸው ሰዎች ይህን ዲን መጥተው በፈለጉ ጊዜ በቀያየሩት ቁጥር እኛ አብረን የምንቀያየረው አላህን ነው የምናመልከው ወይንስ እነዚህ አላህ ያልደነገገውን የሚደነግጉ ዲን አፍራሾች?
መውሊድ የሸሮች ሁሉ መጠራቀሚያ፣ የሙስሊሞችን አንድነት ማፍረሻ፣ የድሆችብ ንብረት መብያ….. እርኩስ ተግባር ነው፡፡ ሙስሊሞች ሆይ! ራቁት፡፡
አይ ሸይጧን በየዘመኑ መጥፎውን ነገር ጥሩ አስመስሎ ስም እየቀያየረ የአደም ልጆችን ያጠማቸዋል፡፡ ወደ እሳትም ይመራቸዋል፡፡ ተመልከቱ አደም እና ሀዋን ያቺን ዛፍ ስሟን አሳምሮ እንዳትበሉ የተባሉትን አስበላቸው ከዛም ስህተት ውስጥ ጣላቸው፡፡ የኑሕን (አለይሂ ሰላም) ህዝቦች በሞቱት 5 ደጋግ ሰዎች ያዘነ መስሎ መቀማመጫቸው ላይ ሀውልት አሰርቶ ገደል ከተታቸው፡፡ የጠፉበትን እርኩስ ተግባር ሽርክ ውስጥ ዘፈቃቸው፡፡ አሁንም ይህን ኡመት “ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላችሁን ውዴት ልደቱን አክብሩለት” የሚመስል የሰይጣን ሹክታ እዚህ ኡማ ላይ ተሰራጭቶ የሽርክ መነሃርያ የሆነውን መውሊድ እያከበሩ ወደ እሳት ሲነዱ ይታያሉ፡፡ መውሊድ ላይ ከባባድ የሽርክ ቃላትን ከእስልምና አስፈንጥረው የሚያስወጡ የሽርክ ተግባራት ይታያሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ አላህን ትቶ ፍጡራንን መለመን፣ እነሱን ድረሱልን ብሎ መጣራት፣ አላህን ትቶ ለፍጡራን ስለት መግባት እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
አሳዛኙ ደግሞ ጥመቱን እንደሃቅ፣ ሃቁን እንደ ጥመት ቆጥረው “ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሀባዎቻቸው፣ ታቢኢኖች፣ አትባኡታቢኢን፣ 4 አኢማዎች፣ ሙሐዲሶች፣ 3 ምርጥ ክፍለ ዘመን እና ትውልድ አላከበረውም” ሲባሉ ሃቁን ከመቀበል ይልቅ ያልታዘዝነውን አንሰራም ያሉትን “ነብዩን የማይወዱ፣ የነብዩ ጠላቶች፣ ወሃብዬች እና ሌላም” ሲሉ ይደመጣሉ፡፡
ከድጡ ወደ ማጡ ይሉሃል ይህ ነው፡፡ ሸይጧን ግን ዛሬ ጥፋታቸውን እያሸበረቀላቸው ዲንን በዲን ስም እንዲንዱ እየገፋፋቸው ነው፡፡
ነሷራችን በነብየላህ ኢሳ (አለይሂ ወሰለም) ላይ ድንበር አልፈው “የአላህ ልጅ ነው” እንዲሉ ያደረጋቸው የሰው እና የጂን ሰይጣናት ናቸው፡፡ ነሷራች ኢሳን ድንበር ያለፉበት ጠልተውት ሳይሆን ወደውት ነው፡፡ ግን ድንበር አለፉ፡፡ ከልክ በላይ ከፍ ከፍ አደረጉት፣ ያላታዘዙትን ልደቱን አከበሩለት፡፡ ከዚህም ኡማ ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመውደድ ስም ሸይጧን መንገድ አስቷቸው ልክ እንደነሷራች ያልታዘዙትን ልደት ማክበር፣ ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “መጣ ያለፈው ወንጀላችንን ማረ”፣ “የሁሉ ቀላቢ”፣ “ልቤ ባንቱ በእርሶ ተመካ” እና የመሳሰሉትን የብቸኛ ፈጣሪና ተመላኪ አላህ መብት አሳልፈው ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመስጠት ታላቁን ማጋራት እና ቢድዐ ሲሰሩ ይታያል፡፡
ሸይጧን መቼም ለሰው ልጎች ከባድ ጠላታቸው ነው፡፡ አላህ ድንበር ከማለፍ፣ ከሽርክ፣ ከቢድዐ እና አላህ ከጠላው ሁሉ ይጠብቀን፡፡ አላህ ወደ ተውሒድ፣ ሱና፣ የሰለፉነ ሷሊሂን አረዳድ፣ እሱ መልካም ወዳለው ሁሉ ይምራን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሃቅ በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
16.9K views14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-18 12:32:23
የነብዩ (ﷺ) ሲራ ክፍል 4
https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/5788
16.5K views09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-16 05:32:48

24.2K views02:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-15 10:44:47

መውሊድን በተመለከተ አጭር መልአእክት

https://t.me/Muhammedsirage
14.4K views07:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-09-13 06:02:01 የትኛውን መውሊድ?
እንደሚታወቀው በኢስላም የታዘዙት ሁለት አመታዊ በኣላት፣ ኢድ አል-ፊጥር እና ኢድ አል-አድሃ ናቸው፡፡ ኢድ አል-ፊጥር አንድ ቀን ብቻ ሲሆን፣ ኢድ አል አድሃ ደግሞ 4 የበኣል ቀናቶች ናቸው፡፡ ታድያ በሀገራችን ተጨባጭ አላህ 4 ቀን እንዲከበር ያዘዘውን አንድ ቀን ብቻ እያከበርን ያልታዘዝነውን መውሊድ ግን ከአንድ ቀን በላይ በተለያዩ ሰዎች ስም ሲከበር ይታያል፡፡
ለምሳሌ ሀገራችን ላይ በተለያየ ቀናት ከሚከበሩ የመውሊድ አይነቶች ውስጥ
1) የነብዩ መውሊድ፣
2) የአሊ ጎንደር መውሊድ፣
3) የአባድር መውሊድ፣
4) የዳንግላው መውሊድ፣
5) የአብሬት መውሊድ፣
6) የቃጥባሬ መውሊድ፣
7) የአልከሶ መውሊድ፣
8) እና ስፍር ቁጥር የሌላቸው መውሊዶች……
ለምን ይሆን በኢስላም የታዘዝነውን ትተን ያልታዘዝነውን የምንሰራው?
እውነት ይህ ነው የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውዴታ?
በፍፁም፡፡
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “አደራችሁን አዳዲስ ነገሮችን (በዲን ላይ ከመጨመር) ተጠንቀቁ፡፡ ሁሉም አዲስ ነገር ጥመት ነው፡፡” ብለው ሲያበቁ
አሁንም ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “የእኛ ትእዛዝ የሌለበትን ስራ የሰራ ሰው ስራው ተመላሽ ነው (ተቀባይነት አያገኝም፣ ውድቅ ነው)” ብለው ሳለ

ዛሬ እሳቸው ያዘዙትን ትተው ያላዘዙትን የሳቸውንም ይሁን ሌሎች ጥሩ ሰዎች ናቸው ብለው የሚገምቷቸውን የአሊ ጎንደር መውሊድ፣ የአባድር መውሊድ፣ የዳንግላው መውሊድ፣ የአብሬት መውሊድ፣ የቃጥባሬ መውሊድ፣ የአልከሶ መውሊድ እና የመሳሰሉትን እያሉ በውዱ ሃይማኖታችን ላይ ቅጥፈትን ይቀጥፋሉ፣ የክህደት ንግግሮችን መውሊዶች ላይ ይናገራሉ፣ ይጨፍራሉ፣ ይህን አደንዛዥ ቅጠል ያላምጣሉ፡፡

ሱብሃነላህ ይህ በፍፁም ነብዩን መውደድ አይሆንም፡፡ ነብዩን ከማንም በላይ የሚወዱት ሰሃባዎች የነብዩን ፈለግ ህይወታቸው ላይ ተላበሱ እንጂ እንዲህ ልደት እናክብር አላሉም፡፡

ለሙስሊሙ ከታሰብ መውሊድ ብሎ በሺርክ፣ በቢድኣ፣ በጭፈራ እና አደንዛዥ ቅጠል ጫትን መቃም እና ማስቃም ሳይሆን፣ መስጂዶችን ማስፋፋት፣ መድረሳዎች መገንባት፣ እውነተኛውን የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) አስተምህሮት ማሰራጨት፣ ከሱስ የፀዳ ሃይማኖቱን እና ሀገሩን የሚጠቅም ትውልድ ማነፅ ይጠበቅብናል፡፡

ይሄ እውነተኛ የነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ውዴታ የሚገለፀበት ተግባር ነው፡፡
አላህ ሱናቸውን ከሚከተሉት ከቢድኣ ከሚርቁት ትውልዶች ያድርገን፡፡
https://t.me/SadatTextPosts
24.5K views03:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ