Get Mystery Box with random crypto!

MHSS STUDENT LEARNING SYSTEM

የቴሌግራም ቻናል አርማ mhss_learning — MHSS STUDENT LEARNING SYSTEM M
የቴሌግራም ቻናል አርማ mhss_learning — MHSS STUDENT LEARNING SYSTEM
የሰርጥ አድራሻ: @mhss_learning
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 468
የሰርጥ መግለጫ

Mohammed Hanfer High School

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-01 08:36:32
For Grade 12 Student form Schedule
65 views05:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 23:10:35
120 views20:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 07:41:17
For Grade 12 Student Only
136 views04:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 14:39:31 የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከ መጋቢት 20 - ሚያዚያ 15 ይከናወናል።
------------------------
የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከ መጋቢት 20 - ሚያዚያ 15,2015ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገለፀ።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባን በተመለከተ መግለጫ ሰጥቷል።
መግለጫውን የሰጡት የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) የ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ምዝገባ በበይነ መረብ እንደሚከናወን ገልፀዋል።

መረጃዎችን በትክክል ባለመሙላት ምክንያት የፈተና ሂደት ላይ ችግር እንደሚፈጥር የገለፁት ዋና ዳይሬክተሩ ይህንን ለማስቀረት ተማሪዎች መረጃዎቻቸውን በወቅቱ ማስመዝገብ እንዳለባቸውም ተናግረዋል።
ያልተመዘገበ ተማሪ የ 2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን እንደማይፈተንም ዶ/ር እሸቱ ገልፀዋል።

በ 2014ዓ.ም በነበረው የምዝገባ ሂደት የተፈታኞች ምዝገባ መረጃ ጉድለት የነበረበት እንደነበር እና በዚህም ምክንያት የፈተና አሰጣጥ ሂደቱ የተራዘመ እንዲሆን እንዳደረገው በመግለጫው ተነስቷል ።

በመግለጫው ምዝገባው ከ መጋቢት 20 እስከ ሚያዚያ 15/2015ዓ.ም ድረስ ለመደበኛና የማታ ተማሪዎች በመንግስት የመደበኛ ትምህርት ቤቶች ለ ድጋሜ ተፈታኞች እና የርቀት ትምህርት ተማሪዎች በተመረጡ የወረዳ ትምህርት ጽ/ቤቶች አማካኝነት በበይነ መረብ ብቻ እንደሚያካሂዱ ተገልጿል።

መደበኛ ተመዝጋቢዎች ከ 9-12ኛ ክፍል በተከታታይ ሲማሩ የነበሩ እና በ2015 ዓ.ም በመማር ላይ ያሉ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

ተማሪዎች ለምዝገባ ሲመጡም ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ በመያዝ በአካል ተገኝተው በበይነ መረብ መመዝገብ እንደሚጠበቅባቸው ተገልጿል።
በመግለጫውም ተማሪዎ፣ ወላጆች ፣ መዝጋቢዎች እና ከመምህራን የሚጠበቅባቸውን ሃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።

ፈተናው የሚሰጥበት ቀንን በተመለከተም ፈተናው በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥና ቀኑ ወደ ፊት የሚገለፅ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል።
190 views11:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 00:22:47
406 views21:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 17:25:02 #21_ምርጥ_አባባሎች

1. "አንድ የደስታ በር ሲዘጋ፣ ሌላ የደስታ በር ይከፈታል። እኛ ግን አብዛኛውን ጊዜ ወደ ተዘጋው በር እንጂ ወደተከፈተልን አናይም፡፡"
#ሔለን_ኬለር

2. ‘’አሸናፊ ለመሆን አንድም ሰዉ እንኳ በማይተማመንብህ ወቅት በራስህ ማመን አለብህ።’’
#ሹገር_ሬይ_ሮቢንሰን

3. "የራስህን የህይወት እቅድ ዲዛይን ካላደረግክ ዕጣ ፈንታህ የሚሆነው በሌሎች እቅድ ውስጥ መኖር/መውደቅ ይሆናል።
#ጂም_ሮን

4. "የምታልፈው ደቂቃ የእያንዳንዱ ሰው እኩል ሀብት ናት፤ አንዴ ካለፈች ግን የማንም ሀብት አይደለችም።"
#ማርክስ_አውሬሊየስ

5. "የደስታ ምንጭ የምትሞላውና ሳታቋርጥ የምትፈሰው ከውስጣችን በሚፈልቁ ብሩህ አስተሳሰቦችና ስሜቶች ነው።
#ዊሊያም_ላዩምፊሊፕስ

6. "በውስጥህ ብዙ ዓይነት ባህሪያት፣ ስብዕናዎች እንዳሉ አትዘንጋ ለራስህ እንግዳ አትሁን፡፡ የአዕምሮ ግዛቶችን ዘልቆ ገብቶ ማንነትንና ችሎታን እንደማወቅ ታላቅ ጀብዱ ከቶ የለም።"
#ሩሶ

7. "እንቅፋቶች እንደ ቢላዋ ናቸው፡፡ በስለቱ ከያዝናቸው ይቆርጡናል፡፡ በእጀታቸው ከያዝናቸው ደግሞ ይጠቅሙናል።"
#ጂምስ_ራስል_ሐዌል

8. “ተሳስተህ አታውቅም ማለት አዋቂ ነህ ማለት አይደለም፤ ምንም የማይሞክር ሰውም ከስህተት ነፃ ነውና።"
#እንግሊዛውያን

9. “የሰዎችን መልካም ገፅታ ብቻ ነው የምመለከተው። እኔ ራሴ እንከን የለሽ ሰላልሆንኩ የሌሎችን እንከን የምቆፍርበት ምክንያት የለኝም ።"
#መሀተመ_ጋንዲ

10. "የማይገለን የህይወት ፈተና፣ ጠንካራ ያደርገናል።”
#ፍሬደሪክ_ኒቼ

11. "በዓለም ላይ ራስህን ከማንም ጋር አታወዳድር፤ ያን ካደረግክ ራስህን እየሰደብክ ነው።”
#አለን_ስትራክ

12. "ሌሎች ሰዎች ምን ያህል በጣም ጥቂት ጊዜ (ከስንት አንዴ) ስለአንተ እንደሚያስቡ ብታውቅ ኖሮ፣ ሌሎች ስለ እኔ ምን ያስባሉ ብለህ አትጨነቅም ነበር።”
#ኤልኖር_ሮዝቬልት

13. "እራስን ሁን፣ የሚሰማህንም ተናገር፣ ምክንያቱም እራስህን በመሆንህ ቅር ለሚላቸው ሰዎች ቦታ/ደንታ መስጠት የለብህም፤ የሚበጁህ ሰዎች ደግሞ እራስህን በመሆንህ ቅር አይሰኙምና።”
#ዶ/ር_ሱስ

14. "ቅን አሳቢ ሰው ጽጌረዳ አበባው ላይ ሲያተኩር ጨለምተኛ ሰው ግን ጽጌረዳውን በመዘንጋት እሾሁ ላይ ያተኩራል።”
#ካህሊል_ጂብራን

15. "ሌላን ሰው ለመሆን መፈለግ የራስን ማንነትን ማባከን ነው።”
#ኩርት_ኮቤይን

16. "የዚህች አለም ታሪክ ማለት በራሳቸው የሚያምኑ የጥቂት ግለሰቦች ታሪክ ማለት ነው።”
#ስዋሚ_ቪቬካናንዳ

17. "የወደፊቱን ለመተንበይ የተሻለው ዘዴ፤ ወደፊትን መፍጠር ነው።”
#አለን_ኬይ

18. “እምነት ማለት ምንም እንኳን ሙሉው የሕይወት መሰላል ባይታይህም የመሠላሉን የመጀመሪያውን እርካብ መርገጥ ነው፡፡ ››
#ማርቲን_ሉተር

19. "ማለም የፈጠራ መነሻ ነው፤ የምትፈልገውን ታልማለህ፣ ያለምከውን ትመኛለህ፤ በመጨረሻም የተመኘኸውን ትፈጥራለህ።"
#ጆርጅ_በርናንድ_ሾው

20. ‘’ለመጀመር ስኬታማ መሆን አይጠበቅብህም ነገር ግን ስኬታማ ለመሆን መጀመር አለብህ ፡፡
#ዚግ_ዚግላር

21. "ደሀ ሆነህ ብትወለድ ጥፋቱ ያንተ አይደለም፤ ደሀ ሆነህ ብትሞት ግን ጥፋቱ ያንተ ነው።"
#ቢል_ጌትስ
401 views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 17:21:36 ለፈተና ለመዘጋጀት የሚጠቅሙ 12 ነጥቦች
በመላው ኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ ፈተናዎች እየተቃረቡ ነው። ታዲያ በዚህ ወቅት ተማሪዎችን እጅግ የሚያስጨንቁ ጉዳዮች እንዴት አድርገን ለፈተናው እናጥና? ያጠናነውንስ ላለመርሳት ምን ማድረግ አለብን የሚሉት ጥያቄዎች ናቸው።
በእነዚህ ምክሮች መሠረት የማስታወስ ችሎታችሁንና የትኩረት አቅማችሁን ታዳብራላችሁ።
1. ቁርስና ጠቃሚ ምግቦች
ሰውነታችን በአግባቡ ሥራውን እንዲሰራ ኃይል ያስፈልገዋል፤ አንጎላችን ደግሞ ትኩረት እንዲኖረውና የማስተዋል አቅማችን እንዲጨምር በቂ የሆነና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት ይፈልጋል።
ጥናቶች እንደሚያሳዩት ቁርሳቸውን ተመግበው ወደፈተና የሚገቡ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ። የተመጣጠነ ምግብ ተመግበው ለፈተና የሚቀርቡት ደግሞ የበለጠ የማስታወስና የማስተዋል አቅም ይኖራቸዋል።

2. በጠዋት ወደ ጥናት መግባት
ሁሌም ቢሆን ነገሮችን አስቀድሞ መጀመርን የመሰለ ነገር የለም። ለፈተናም ቢሆን ጥናት በጠዋት ተነስቶ መጀመር በፈተና ወቅት የተረጋጋ መንፈስ እንዲኖረን ይረዳል።
ጠዋት ላይ ጭንቅላታችን እረፍት አድርጎ በአዲስ መንፈስ ሁሉንም ነገር ስለሚጀምር፤ በዚህ ሰዓት ማጥናት ውጤታማ ያደርጋል። በተለይ ደግሞ የክለሳ ጥናቶችን ለከሰዓት ማሸጋገር ተገቢ አይደለም።
ጠዋት ጥናት የምንጀምርበትና የምናበቃበት ሰዓት ከፈተናው በፊት ባሉት ሁለት ወይም ሦስት ሳምንታት ውስጥ ተመሳሳይ ለማድረግ መሞከርም ውጤታማ ያደርጋል።





3. ምን ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባችሁ ወስኑ
በመጀመሪያ ፈተናው የጽሁፍ ነው ወይስ የተግባር? ወይስ ቃለመጠይቅ ነው የሚለውን መለየት ወሳኝ ነው።
ሁሉም ዓይነት ፈተናዎች የራሳቸው የሆነ የተለያየ አይነት አቀራረብ አላቸው። በምሳሌ አስደግፎ ማብራሪያ መስጠት የሚጠይቅ ዓይነት ፈተና ከሆነ ከዚህ በፊት የተሠሩ ፈተናዎችን እያመሳከሩ ጥቂት ቦታዎች ላይ በትኩረት መዘጋጀት።
ምናልባት ፈተናው ምርጫ አልያም አጭር መልስ የሚፈልግ ዓይነት ከሆነ ቀለል ያለና አጠቃላይ መረጃዎችን ለመያዝ መሞከር።
4. እቅድ ማዘጋጀት
ምናልባት ነገሮችን ቦታ ቦታ ለማስያዝና እቅድ ለማውጣት የምናጠፋው ጊዜ የባከነ መስሎ ሊሰማን ይችላል። ነገር ግን እውነታው በተቃራኒው ነው። ምክንያቱም ምን ማጥናት እንዳለባችሁና መቼ ማጥናት እንዳለባችሁ እቅዳችሁ ይነግራችኋል።
ከዚህ በተጨማሪም ምን ያክል እንደተጓዛችሁ ለመመዝገብና ለመከታተል ይረዳል።
የትኞቹን ማስታወሻ ደብተሮች መቼ መመልከት እንዳለባችሁ፣ የትኞቹን መጻህፍት ለተጨማሪ ማብራሪያ እንደምትጠቀሙ እንዲሁም የፈተና ጥያቄዎችን መቼ መለማመድ እንዳለባችሁ በእቅድ ውስጥ ማስገባት ውጤታማ ያደርጋል።
እዚህ ጋር መርሳት የሌለብን ለእረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴም ቦታ መስጠት እንዳለብን ነው።
5. ከፋፍሎ ማጥናት
የክለሳ ጥናትን ከፋፍሎ ማካሄድን የመሰለ ነገር የለም። አንድ የትምህርት ዓይነት ላይ 10 ሰዓት ሙሉ ከማሳለፍ በየቀኑ አንድ ሰዓት በማጥናት በ10 ቀን መጨረስ ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋል።
ያጠናነውን ነገር ለማስታወስና በቀላሉ ለመሸምደድ ጭንቅላታችን ጊዜ ይፈልጋል። ከፋፍሎ ማጥናት ደግሞ ለዚህ ፍቱን መድሃኒት ነው። ከፋፍሎ ማጥናት እጅግ ውጤታማው መንገድ እንደሆነም በመላው ዓለም የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች ያለመክታሉ።



6. ራሳችሁን ቶሎ ቶሎ ፈትኑ
የሥነ አዕምሮ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚሉት የማስታወስ ችሎታን ለማዳበርና በራስ መተማመናችንን ለመጨመር ራስን መፈተን ውጤታማ ያደርጋል።
ከዚህ በተጨማሪ እየተዘጋጀንበት ያለነውን ጉዳይ በደንብ እንድናውቀው ከማድረጉ በተጨማሪ የረሳናቸው አልያም የዘለልናቸው ርዕሶችን ለመለየት ይረዳናል።
7. መምህር መሆን
ከባዱን የክለሳና ራሳችሁን የመፈተን ሥራውን ካከናወናችሁ በኋላ ጓደኞቻችሁን ሰብሰብ አድርጋችሁ በጭንቅላታችሁ የሚመጣውን ነገር በሙሉ ንገሯቸው። ራሳችሁን በመምህር ቦታ አድርጋችሁ እውቀታችሁን ለማካፈል ሞክሩ።
ምን ያህል እንደምታስታውሱ ለማወቅ ከመርዳቱ በተጨማሪ ጓደኞቻችሁንም ትጠቅሟቸዋላችሁ።
8. ከተንቀሳቃሽ ስልካችሁ ራቅ በሉ

ስልኮች በጣም ብዙ ጥቅም አላቸው። ነገር ግን በጥናት ወቅት ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ነው የሚያመዝነው። በተለይ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምትጠቀሙ ከሆነ።
ብዙ ጥናቶች እንዳረጋገጡት ብዙ ጊዜያቸውን ስልካቸው ላይ የሚያሳልፉ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው ሁሌም ቢሆን ዝቅ ያለ ነው።
ብትችሉ ስልካችሁን አጠገባችሁ እንኳን አታድርጉት።
9. ሙዚቃ መቀነስና በጸጥታ ማንበብ
በጸጥታ ውስጥ ሆነው ጥናታቸውን የሚያከናወኑ ተማሪዎች ሙዚቃ እየሰሙ ከሚያጠኑት ጋር ሲወዳደሩ በእጅጉ የተሻለ የማስታወስና የትኩረት አቅም እንዳለቸው ማረጋገጥ ተችሏል።
10. ቋሚ እረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴ
ውጤታማ የክለሳ ጥናት ማለት እረፍት አልባ ጥናት ማለት አይደለም። በጥናታችን መሀል መሀል ላይ ጥሩ አየር ለማግኘትና ሰውነታችንን ለማፍታታት ወጣ ብሎ እንቅስቃሴ ማድረግ የማስታወስ ችሎታችንን በደንብ ከፍ ያደርገዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሰውነታችን እና ጭንቅላታችን በእጅጉ የተሳሰሩ በመሆናቸው እንቅስቃሴ ስናደርግ የደም ዝውውራችን ይስተካከላል፤ ይህ ደግሞ በቂ ኦክስጅን ወደ ጭንቅላታችን እንዲሄድ ይረዳል።
አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ጭንቀትን መከላከልና በራስ መተማመንን መጨመር ከነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ።
11. እንቅልፍ

ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው።
በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዲሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታድርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ።
12. መረጋጋትና በጎ በጎውን ማሰብ
እስካሁን የተዘረዘሩትን ነገሮች ሁሉ ተግባራዊ ካደረጋችሁ ምንም የሚያሳስባችሁ ነገር ሊኖር አይገባም። ዘና ብላችሁ ወደ ፈተና መግባት ብቻ ነው የሚቀራችሁ። ምናልባት ጥሩ ያልሆነ አጋጣሚ ቢገጥማችሁ እንኳን እሱን ረስታችሁ ለቀጣዩ በጥሩ መንፈስ ለመዘጋጀት ሞክሩ።
በመጨረሻም በእያንዳንዱ ጥሩ የፈተና ጊዜ ለራሳችሁ ሽልማት መስጠት አትርሱ።
314 views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 22:27:35 The average weight of A, B and C is 45 kg. If the average weight of A and B be 40 kg and that of B and C be 43 kg, then the weight of B is:
A. 17 kg
B. 20 kg
C. 26 kg
D. 31 kg
Answer: D

Let A, B, C represent their respective weights. Then,
A + B + C = 45
3
A + B + C = (45*3)=135 (¡)

A + B = (40 x 2) = 80 .... (ii)
B + C = (43 x 2) = 86 ....(iii)

Adding (ii) and (iii), we get: A + 2B + C = 166 .... (iv)

Subtracting (i) from (iv), we get : B = 31.
B's weight = 31 kg.
335 views19:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 09:13:19 ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በአካል በመገኘት መጋቢት 8 እና 9 /2015ዓ.ም. እንድትመዝገቡ እንገልፃለን።

፨ምዝገባ የምታካሂዱባቸው ግቢዎች

1ኛ. በማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የትምህርት መስክ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሚዛን አማን ከተማ በሚገኘው ዋናው ግቢ ፣

2ኛ. በተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) ትምህርት መስክ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ደግሞ ቴፒ ከተማ በሚገኘው ቴፒ ግቢ

፨ለምዝገባ የሚያስፈልጉ የትምህርት ማስረጃዎች እና የግል መገልገያ ቁሳቁሶች

1ኛ. የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት እንዲሁም ከ9ኛ --12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ ፣

2ኛ. አምስት የቅርብ ጊዜ ሦስት በአራት (3*4) ጉርድ ፎቶ ፣

3ኛ. ብርድልብስ፣አንሶላና የትራስ ጨርቅ መያዝ እንደሚጠበቅባችሁ እናሳውቃለን።

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት
342 views06:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 09:12:02 #አምቦዩኒቨርሲቲ

አምቦ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የተመደቡ የሪሜዲያል (የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም) ተማሪዎችን የሚቀበልበት የመግቢያ ቀን መጋቢት 07 እና 08 2015 ዓ.ም በመሆኑ በተጠቀሰው ቀናት ብቻ በማህበራዊ ሳይንስ መስክ የተመደባችሁ በዋና ካምፓስ ፤ በተፈጥሮ ሳይንስ የተመደባችሁ አምቦ ከተማ ሃጫሉ ሁንደሳ ካምፓስ በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ጥሪ እያደረገ ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞ ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ ዩኒቨረሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
ሁሉም ተማሪዎች ለምዝገባ ስትመጡ ልትይዟቸው የሚገቡ፡-
- ከ8 –12ኛ ክፍል ያሉ የትምህርት ማስረጃ ዋናውና ኮፒ፡
- የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሳርትፍኬት ዋናውና ኮፒ፡
- 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ ብዛት 8:
- አንሶላ፡ ብርድልብስ፡ ትራስልብስ እና የስፖርት ትጥቅ::

ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት
324 views06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ