Get Mystery Box with random crypto!

Maranatha Digital Network

የቴሌግራም ቻናል አርማ maranatha_fellowship — Maranatha Digital Network M
የቴሌግራም ቻናል አርማ maranatha_fellowship — Maranatha Digital Network
የሰርጥ አድራሻ: @maranatha_fellowship
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.19K
የሰርጥ መግለጫ

#Maranatha_digital_Network #youth center #spreading the gospel of the lord Jesus Christ #christian living #Christian fellowship
Follow us on:-
instagram : maranatha_fellowship
facebook: maranathafellowshipEthiopia
Telegram group @Maranatha_Fellowship2

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-07-27 07:39:06 አማኝ በምን ይሸለማል?
ክፍል-10

2-የኋለኛው ትንሣኤ
✧ ከሺው ዓመት መንግሥት በኃላ የሚፈጸም ሲሆን #ያልዳኑ_ሰዎች_ለፍርድ (ለኩነኔ) የሚነሱበት ሁለተኛው ትንሣኤ ነው።
✧ የዚህ ትንሣኤ ተካፋይ የሚሆኑ ሙታን ሁሉ በታላቁና ነጩ ዙፋን ፍርድ ፊት ይቆማሉ። ከዚህ ቀደም እንደተመለከትነው ከዚህ ፍርድ ፊት የሚቆም ማንኛውም ሰው ስሙ በሕይወት መጽሐፍ ላይ ተጽፎ ስላልተገኘ ሁለተኛው ሞት ይሰለጥንበታል (በእሳት ባህር ውስጥ ይጣላል)።
✧ ዳንኤል እንደተመለከተው ለእፍረት(ለውርደት) እና ለዘላለም ጕስቍልና የሚነሱበት የኅጥኣን ትንሣኤ ነው [ት/ዳን. 12÷2]።
✧ በፊተኛውና በኋለኛው ትንሣኤ መካከል ቢያንስ የሺህ ዓመት ልዩነት አለ። “#የቀሩቱ_ሙታን ግን ይህ #ሺህ_ዓመት_እስኪፈጸም ድረስ በሕይወት አልኖሩም። ይህ የፊተኛው ትንሣኤ ነው።”
— ራእይ 20፥5
✧ ከፊተኛው ትንሣኤ በኋላ የሺው ዓመት (የመሲሁ) መንግሥት በምድር ላይ የሚሆን ሲሆን ከኋለኛው ትንሣኤ በኋላ ግን ምድርና ሰማይ ከፊቱ ይሸሻሉ፤ የሰማይም ፍጥረት በታላቅ ትኩሳት ይቀልጣል። [2ጴጥ. 3÷12፤ ራዕይ 20÷11]

Дየፍርድ ወንበር ፍርድ አሰጣጥ
//––••–––••–––••–––••––//
✧ያልዳኑ ሰዎች ሁሉ (የኋለኛው ትንሣኤ ተካፋይ የሆኑቱ) የዚህ ፍርድ ተካፋይ አይሆኑም።
✧ፍርዱ የአማኞችን ንጥቀት ተከትሎ (ጌታ "#በጻድቃን_ትንሣኤ" ብሎ እንደተናገረው»» ሉቃስ 14÷14) በአየር ላይ ከበጉ ሠርግ ፊት ይፈጸማል።
✧“ክርስቲያኖች በእምነት አማካኝነት በክርስቶስ ያገኙትን ዘላለማዊ ጽድቅ የሚመለከት ሳይሆን፤ በዚህ ምድር ሲኖሩ ለሠሩት ሥራ የሚቀበሉት ፍርድ ነው።” (የአድሱ መደበኛ ትርጉም ማጥኛ)
የፍርድ አፈፃፀሙን በአግባቡ ለመገንዘብ 1ቆሮ. 3÷11–15 እጅጉን ይረዳናል። ከዚህ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል አራት ነጥቦችን እንደሚከተለው እንመልከት....

፩ ብቸኛው መሠረት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው [ቁ.11]
☞የቤተክርስትያን የማዕዘኑ ራስ ድንጋይ ክርስቶስ እንደሆነ ቅዱሳት መጻሕፍት ያስተምሩናል። እርሱ #የተፈተነ_የመሠረት_ድንጋይ ስለሆነ (ት/ኢሳ. 28÷16) ያለጥርጥር ጽኑና አስተማማኝ ነው። መጽሐፍ “በእርሱ የሚያምን ሁሉ አያፍርም” እንደሚል በእርሱ ላይ ያለ ከመሠረቱ (ከክርስቶስ) የተነሳ ሕይወት አለው።

፪ ያ ቀን [ቁ.13]
☞ይህ «ያ ቀን» የተባለው ቀን ፍርዱ የሚፈጸምበት፤ ይሄውም አማኞች በክርስቶስ ፍርድ ወንበር (Bema seat) ፊት የሚቀርቡበት ነው። በዚህን ቀን የፍርድ ተቀባዩ መዳን አለመዳን ሳይሆን ሥራው ይፈተናል። አማኙ በምድር በኖረበት ዘመን የኖረው ኑሮ ሁሉ ይገለጣል (ያ ቀን ወደ ብርሃን ያመጣዋል)። #እሳቱ_የእያንዳንዱን_ሥራ_ጥራት_የሚፈትን_እንጂ_ፍርድ_ተቀባዩን_የሚፈጅ_አይደለም

¶ከዚህ ቀጥለን የምንመለከታቸው ቀሪዎቹ ሁለት ነጥቦች ከፍርዱ ውጤት ጋር የተያያዙ ናቸው። ቁ.12 ላይ “ማንም ግን በዚህ መሠረት (በክርስቶስ) ላይ...” በማለት የፍርዱ ምክንያት አማኞች በተመሠረተው መሠረት »»በክርስቶስ ላይ ያነጹት (የገነቡት) ኑሮ እንደሆነ በግልፅ ያስቀምጣል።

፫ ሥራው ተፈትኖ ያለፈለት ይሸለማል [ቁ.12&14]
☞ወርቅ፣ ብርና የከበረ ድንጋይ➜ በእሳት ተፈትኖ የሚያልፈውን (የሚጸናውን) ሥራ የሚያመላክቱ ሲሆኑ በእግዚአብሔር ቃል የሚመራ የጤናማ ክርስትና ህይወት ምሳሌዎች ናቸው።
የእግዚአብሔር ጸጋ ረድቶአቸው.... ክቡር በሆነው እግዚአብሔርን በመምሰል ህይወት የኖሩ፣ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ፈቃድ በማስገዛት በክርስቶስ ደም የተዋጁበትን የሚመጥን ኑሮ ለመኖር የጣሩ፣ እንደ እግዚአብሔር ቃል ለመኖር የተጉ አማኞች ከጌታ ዘንድ ምስጋና ይቀበላሉ [1ጴጥ. 1÷6–7፤ 1ቆሮ. 4÷5]።

፬ ሥራው የተቃጠለበት ይጎዳበታል (ሽልማት ይቀርበታል) [ቁ.12&15]
☞እንጨት፣ ሳር እና አገዳ➜ በእሳት ተፈትኖ ማለፍ የማይችለውን (የሚቃጠለውን) እንደ ሰው ጥበብና መንደራዊ ከንቱ ኑሮ የመኖር የደካማ ህይወት መግለጫዎች ናቸው።
1ኛ ቆሮንቶስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁵ የማንም ሥራ የተቃጠለበት ቢሆን ይጎዳበታል፥ እርሱ ራሱ ግን ይድናል ነገር ግን በእሳት እንደሚድን ይሆናል።
▼▼(አዲሱ መ.ት)
¹⁵ ሥራው የተቃጠለበት ግን #ሽልማት_ይቀርበታል፤ እርሱ ራሱ ግን ይድናል፤ ይሁን እንጂ #የሚድነው_በእሳት_ውስጥ_በጭንቅ_እንደሚያልፍ_ሆኖ_ነው።
☞መጽሐፍ ቅዱሳችን አማኝ በምድር በኖረበት ደካማ ኑሮ ምክንያት ድነቱን ያጣል ብሎ አያስተምረንም #ምክንያቱም_ድነት_ወይም_የዘላለም_ሕይወት_በክርስቶስ_በኩል_የሆነ_ገና_ደካሞች_ሳለን_የተሰጠን_የእግዚአብሔር_ነፃ_ስጦታ_እንጂ_በሥራችን_ላይ_የተመሠረተ_አይደለም!!
ይቀጥላል........
ጸጋና ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችን ጋር ይሁን!
|.MARANATHA DIGITAL NETWORK.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
3.4K viewsYOKABID 4ME, edited  04:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 22:21:30
MDN-BIBLE VERSE

“እናንተ ግን ወዳጆች ሆይ፤ እጅግ ቅዱስ በሆነው #እምነታችሁ ራሳችሁን ለማነጽ ትጉ፤ #በመንፈስ ቅዱስም ጸልዩ።”
— ይሁዳ 1፥20 (አዲሱ መ.ት)

መልካም ምሽት
|.MARANATHA DIGITAL NETWORK.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
2.6K viewsCUP 10 »»»»»»»»»»»», edited  19:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 12:40:58 አማኝ በምን ይሸለማል?
ክፍል -9
¶ከዚህ ቀደም በነበሩ ክፍሎች በአዲስ ኪዳን ከሚገኙ ፍርዶች መካከል አንዱንና የመጨረሻ የሆነውን (ከምድር እና ሰማይ መጨረሻ በኃላ የሚፈፀመውን) ስንመለከት ቆይተናል። በእነዚያ ክፍሎች የታላቁና ነጩ ዙፋን ፍርድ የእግዚአብሔር ቍጣ በሀይል የሚገለጥበት መሆኑን እና አማኞችን እንደማይመለከት ለመመልከት ሞክረናል። በዛሬው እና በቀጣዮቹ ክፍሎች ደግሞ አማኞችን ከሚመለከታቸው ፍርዶች አንዱ የሆነውን ቀጥለን እንመለከታለን.. መልካም ንባብ ተመኘው...

የክርስቶስ የፍርድ ወንበር [2ቆሮ.5÷9-10፤ ሮሜ 14÷10]

¶በግሪኩ “βῆμα”»» “Bema” በመባል የሚታወቅ ሲሆን አማኞች በዚህ ምድር ሲኖሩ “ምን?፤ ለምን?” እንደሰሩ ሥራቸው የሚፈተንበት ከዚያም እንደየስራቸው መጠን ብድራትን የሚቀበሉበት ነው።
¶ከዚህ ቀደም አጽንዖት እንደሰጠነው በአማኝ የሚገለጠው መልካም ሥራ ከአማኙ ጉብዝና፣ ልዩ አቅም እና ችሎታ የመነጨ ሳይሆን #እግዚአብሔር_ራሱ መልካም የመስራትን ፍላጎት ሆነ የማድረግን ብቃት በአማኙ ውስጥ እንደሚሰራ [ፊል. 2÷13] እንዲሁም እስከ ጌታ መምጫ ድረስ እንደሚያስቀጥለን [ፊል. 1÷6] ጸጋው እንደሚረዳን መዘንጋት አይገባም።
¶ይህ ፍርድ ያልዳኑትን (የኋለኛው ትንሣኤ ተካፋይ የሆኑትን) እንደማይመለከትና እና የፍርዱ ተቀባዮች መዳን አለመዳናቸውን የሚያረጋግጡበት አለመሆኑን ልብ ልንል ይገባል። [ክፍል 3 እና 4ን መለስ ብለው ይመልከቱ]።
¶የፍርዱ ውጤትም መሸለም አልያም አለመሸለም ነው። #ከሽልማት_ጋር_እንጂ_ነፃ_ስጦታ_ከሆነው_ከዘላለም_ሕይወት_ጋር_የሚገናኝ_አይደለም!! (በቀጣዩ ክፍል በሰፊው እንመለከታለን)
¶የፍርዱ መፈጸሚያ ጊዜ ከንጥቀት በኋላ ከበጉ ሰርግ በፊት በአየር ላይ ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም #የጻድቃንን_ትንሣኤ ተከትሎ እንደሆነ ተናግሯል [ሉቃ. 14÷14]

ስለትንሣኤ ያውቃሉ
ስለትንሣኤ ወደፊት በደንብ የተብራራ ትምህርት ይዘን እንደምንቀርብ እያሳወኩ ቁንጽል የሆነውን እንደሚከተለው አሰናድቼላችኋለሁ።
✓ከአዳም አንስቶ እስከመጨረሻው ትውልድ ድረስ የሰው ልጅ በሙሉ እንደሚነሳ የእግዚአብሔር ቃል ያስተምራል። #ፈርሶ_የሚቀር_ሥጋ_ጠፍቶ_የሚቀር_ሰው_የለም። ዳሩ ግን የሁሉም ትንሣኤ በደፈናው በአንድ ላይ /አንድ ጊዜ/ የሚፈጸም ሳይሆን በራሱ ተራ እንደሆነ ቅዱሳት መጽሕፍት ያረጋግጡልናል [1ቆሮ. 15÷23]።
¶የትንሣኤ ትምህርት የክርስትና መሰረታዊ ትምህርት እንደሆነና እውንተኝነቱ ማረጋገጫ የክርስቶስ ትንሣኤ መሆኑን የእውነት ቃል በግልጥ ያስተምራል ።

ዳንኤል በዘመኑ ድንቅ ነገር በራዕይ ተመልክቶ ነበር [ት/ዳን 12÷2]። የሙታን ትንሣኤ እንዳለና “...እኵሌቶቹ ወደ #ዘላለም_ሕይወት እኵሌቶቹም ወደ #እፍረትና ወደ #ዘላለም_ጕስቍልና።” እንደሚነሱ አይቷል። ጌታም #ለሕይወት_ትንሣኤ እና #ለፍርድ_ትንሣኤ ከመቃብር የሚወጡ እንዳሉ ተናግሯል [ዮሐ.5÷28]። ከላይ የቀረቡትን ጥቅሶች በጥንቃቄ ካስተዋልን ሁለት አይነት ትንሣኤዎች እንዳሉ መረዳት አዳጋች አይሆንብንም።

1-የፊተኛው ትንሣኤ
ራእይ 20
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ √በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው #ብፁዕና_ቅዱስ ነው፤
√ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ #ሥልጣን_የለውም፥
√ዳሩ ግን የእግዚአብሔርና የክርስቶስ ካህናት ይሆናሉ ከእርሱም ጋር ይህን #ሺህ_ዓመት_ይነግሣሉ።
¶ለክርስቶስ የሆኑት በክብር የሚነሱበት ነው።
¶የቅዱሳን ወይም የጻድቃን ትንሣኤ በመባል ይታወቃል።
¶የዳኑ ሰዎች ለሕይወት የሚነሱበት ነው (ለሕይወት ትንሣኤ)።

በውስጡ ሦስት ተራቸውን የጠበቁ ትንሣኤዎች ያካትታል።
. ከፊል ትንሣኤ
¶ጌታ ከተነሳ በኋላ ከብሉይ ኪዳን ብዙዎች ቅዱሳን ተነስተው (ከመቃብሮቻቸው ወጥተው) ነበር። [ማቴ. 27÷52-53]

. የቤተክርስቲያን ንጥቀት
¶በክርስቶስ ሆነው ያንቀላፉት መቃብሮቻቸው ተከፍቶ በመውጣት፤ በሕይወት የምንቀር ደግሞ በቅፅበተ-አይን በመለወጥ የማይበሰብሰውን ሰማያዊውን አካል እንካፈላለን። [ፊል. 3÷20፤ 1ተሰ 4÷13-18]

ሐ.በሰባቱ ዓመት መከራ የሚገደሉ
¶ከቤተክርስቲያን ንጥቀት በኃላ ለ7 ዓመት በምድር ላይ መከራ (በአየር ላይ የበጉ ሠርግ) እንደምሆን የታወቀ ነው። በዚህን ጊዜ የሚሰበከውን የመንግሥቱን ወንጌል በመቀበላቸውና ለአውሬው ምስል ባለመስገዳቸው የሚገደሉት ከሺው አመት መንግሥት በፊት ይነሳሉ። [ራዕ. 20÷4፤ 6÷9....]
ይቀጥላል.....
ጸጋና ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችን ጋር ይሁን!
|.MARANATHA DIGITAL NETWORK.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
3.2K viewsYOKABID 4ME, 09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 15:05:30
“ከዚህ የተነሣ በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቍጣ ይመጣልና.. ” ኤፌ.5፥6
በዚህ ጥቅስ መሠረት «በማይታዘዙት ልጆች» የሚለው እነማንን ይወክላል?
Anonymous Quiz
10%
ለመታዘዝ የደከሙትን (ክፍተት የተገኘባቸውን) የእግዚአብሔርን ልጆች
39%
እንደ እግዚአብሔር ቃል ባለመኖር ኃጢአት የተያዙትን አማኞች
38%
ያላመኑትን ወይም ያልዳኑትን ሰዎች
13%
አማኝ የነበሩ ከሀዲዎች
233 voters3.1K viewsYOKABID 4ME, 12:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-14 13:18:59 አማኝ በምን ይሸለማል?
ክፍል-8
¶በ7ኛው ክፍል የእግዚአብሔርን ቍጣ ምንነትና እነማን ላይ እንደሚመጣ ለመመልከት ሞክረን ነበር... አሁን ደግሞ ቀጥለን አማኞችን እንደማይመለከት እንማማራለን።

የእግዚአብሔር ቍጣ አማኞችን ይመለከት ይሆን? መጽሐፍ ምን ይላል
¶እግዚአብሔር በኃጢአት ላይ መቆጣቱ የቅድስና ባህሪው መገለጫ እንደሆነ የባለፈው ክፍል ትምህርታችን ነው። የእግዚአብሔር ቃል በግልጠት እንደሚያስተምረውም #የሰው_ልጆች_ሁሉ_ኃጢአትን_ሰርተዋል። ስለዚህ ሁሉም የእግዚአብሔር ቍጣ ተካፋይ መሆናቸው የግድ ነበር። ነገር ግን 1ኛ ተሰ. 5÷9 ላይ “#እግዚአብሔር_ለቍጣ_አልመረጠንምናበጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።” በማለት አማኞች በክርስቶስ በኩል በሆነው የእግዚአብሔር ምርጫ ከእግዚአብሔር ቍጣ መዳንን እንዳገኙ በግልፅ ያስቀምጣል። በሌላ አባባል አማኝ የተመረጠው በክርስቶስ ኢየሱስ ከእግዚአብሔር ቍጣ ለመዳን ነው [ሮሜ.5÷9]። #ካልሆነማ_ከምን_ድነን_ነው_ድኛለው_የሚንለው?

¶የሰው ልጆች ሁሉ ያለልዩነት ኃጢአትን ሰርተው ሳሉ የእግዚአብሔር ቍጣ አማኞችን የማይመለከተው ያለምክንያት ነውን በፍፁም
1ኛ ዮሐንስ 2
“² እርሱም (ኢየሱስ ክርስቶስ) የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው....”

¶የኃጢአት ስርየት ሁሌም ከደም መፍሰስ ጋር የተያያዘ ነው። ደምም ሳይፈስ ስርየት የለም [ዕብ.9÷22]። ፋሲካችን የሆነው ክርስቶስ የኃጢአታችን ማስተሰሪያ ሆኖ ሊያድነን መስዋዕት እንደሆነልን (እንደታረደልን) ቅዱሳት መጽሐፍት ያስተምሩናል። ሐዋርያው ዮሐንስ በጻፈው መልዕክት (ከላይ ባለው ጥቅስ) “ማስተስሪያ” ለሚለው ቃል የዋለው የግሪኩ ቃል «#የእግዚአብሔርን_ቍጣ_ለማብረድ_ብቃት_ያለው_መስዋዕት» እንደሆነ ያመለክታል። ስለዚህ የኃጢአት ስርየት ዋና አላማ ሰዎችን ከእግዚአብሔር ቍጣ ማዳን ነው። በብሉይ የነበሩ መስዋዕቶች ስርየትን ማምጣት (ኃጢአትን ማስወገድ) የማይችሉ በመሆናቸው በተደጋጋሚ በየጊዜው መቅረብ ነበረባቸው። ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ የቀረበው የአዲሱ ኪዳን መስዋዕት ግን አብ ረክቶበታልና ስርየትን አስገኝቷል።

ድነት ማለት እንግዲህ የኃጢአት ስርየትን ባገኘንበት በክርስቶስ ኢየሱስ ደም ከእግዚአብሔር ቍጣ ያመለጥንበት እውነት እንደሆነ ከላይ በዝርዝር ከቀረቡ ሀሳቦች መረዳት ይቻላል። ይህም ከእኛ ከራሳችን የሆነ ሳይሆን ከእግዚአብሔር ጸጋ የሆነ ነው። የቅድስና ባህሪው አስገድዶት በኃጢአታችን ላይ የተቆጣው #ራሱ እግዚአብሔር #ከራሱ ቍጣ ሊያድነን #የራሱን በግ ወደዚህ ዓለም ልኮታል። ከማናችንም ይልቅ እግዚአብሔር የልጁ መስዋዕትነት ከቍጣው እንደሚያድነን እርግጠኛ ነው። በዚህ መስዋዕትነትም በአማኞች ኃጢአት ላይ የነበረው የእግዚአብሔር ቊጣ ተወግዶ በክርስቶስ ላይ ስላረፈ አማኞች ከቍጣው ነፃ ወጥተዋል። ጌታ ኢየሱስ በመስቀል ላይ የተሰቀለው ኃጢአታችንን ተሸክሞ ስለነበር ኃጢአታችንን እግዚአብሔር በመስቀል ላይ ቀጥቶታል። ያለኃጢአቱ በእንጨት የተሰቀለልን ጌታ ዕዳችንን ሁሉ ከፍሎ ተፈፀመ ብሏል።

¶ምድርን ሁሉ ለማጥፋት መጥቶ ከነበረው የጥፋት ውሃ ኖህና ቤተሰቦቹ ግን #መርከብ ውስጥ ተሸሽገው እንደተረፉ ሁሉ ለአማኞች ከቍጣ የዳኑበት መርከባቸው #ክርስቶስ ነው። በግብፅ ምድር ሁሉ ላይ መጥቶ የነበረው የሞት መልዓክ #ቤቱ_ውስጥ_ከነበሩት_እስራኤላውያን_ብቃት_ሳይሆን_በመቃኖቻቸው_ላይ_ከታየላቸው_ከፋሲካው_በግ_ደም የተነሳ እንዳለፋቸው፤ እንዲሁ የክርስቶስ ክቡር ደም ከእግዚአብሔር ቍጣ ያመለጥንበት ብቃታችን ነው።

በአጠቃላይ በዮሐ.3÷36 መሠረት የእግዚአብሔር ቍጣ በማያምኑት ላይ የሚሆን ሕይወትን ካለማየት [ከዘላለም ጥፋት] ጋር የሚስተካከል እንደሆነ መረዳት እንችላለን። #የቁጣ_ልጆች_ነበርን_አሁን_አይደለንም
ኤፌሶን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥
⁵ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ #በበደላችን_ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር #ሕይወት_ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥

ይቀጥላል........
ጸጋና ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችን ጋር ይሁን!
|.MARANATHA DIGITAL NETWORK.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
6.8K viewsYOKABID 4ME, 10:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-12 14:00:41
ከሚከተሉት አማራጮች መካከል በቅዱሱ መጽሐፋችን መሠረት እውነት ያልሆነው የቱ ነው?
Anonymous Quiz
32%
ከዚህ ቀደም ከፊል የቅዱሳን ትንሣኤ ተፈጸሞ ነበር
24%
ሁሉም ሰው በተመሳሳይ ጊዜ አይደለም የሚነሳው
20%
ቅዱሳን የኋለኛው ትንሣኤ ተካፋዮች ናቸው
24%
ያልዳኑ ሰዎች ከሺው ዓመት መንግሥት በኋላ ነው የሚነሱት
206 voters2.3K viewsYOKABID 4ME, 11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 13:24:42 አማኝ በምን ይሸለማል?
ክፍል-7

¶በ6ኛው ክፍል ስለፍርዶች መመልከት መጀመራችን የሚረሳ አይደለም። ዛሬም ቀጥለን #ስለእግዚአብሔር_ቁጣ እንማማራለን መልካም ንባብ ተመኘው....

¶መጽሐፍ ቅዱሳችን ስለእግዚአብሔር ቁጣ ግልፅና የተብራራ ትምህርት አለው። በብሉይም ሆነ በአዲሱ ኪዳን ቅዱሳት መጽሐፍት ውስጥ በብዙ ስፍራዎች ተጽፎ ስለሚናገኝ ለማናችንም አዲስ ቋንቋ እንደማይሆን እሙን ነው። ሁላችሁም ምንነቱን ቢትጠየቁ ጥሩ ምላሽ እንደሚትሰጡ አልጠራጠርም። እንደእኔ ምልከታ ግን የእግዚአብሔር ቁጣ እንደሚከተለው ይብራራል....
የእግዚአብሔር_ቍጣ:– በረባ ባልረባ ፊትን እንደማኮፈስ ያለ መሠረት የለሽ እንደሰው ቁጣ ሳይሆን ከቅድስና ባህሪው ጋር የሚጻረረውን #ኃጢአትን የሚበቀልበት ትክክለኛ የሆነ ለኃጢአት ያለው ጥልቅ ጥላቻ ነው።
፨ይሄ ፍቅር ከሆነው ማንነቱ ጋር የሚጣረስ ባህሪው ሳይሆን ከአመፅ ጋር ምንም አይነት ትብብር እንደሌለው የሚያሳይ የቅድስና ባህሪው ነው። #ቅዱስ_የሆነው_እግዚአብሔር_በቅዱስ_አደራረጉ_በኃጢአት_ላይ_ይቆጣል።

የእግዚአብሔር ቊጣ እነማንን ይሆን የሚመለከተው? መጽሐፍ ምን ይላል
¶መጽሐፍ ቅዱሳችንን ረጋ ብለን ስናጠና #የእግዚአብሔር_ቊጣ ወደፊት ሊገለጥ ያለና አለም ከዚህ ቀደም ፈጽማ አይታው የማታውቀው ከምናስበው በላይ እጅግ አስጨናቂ እና አስፈሪ እንደሆነ እንረዳለን። ይህ በፍርድ የሚገለጠው የእግዚአብሔር ቊጣ:- #ታላቁንና_ነጩን_ዙፋን_ፍርድ በሚያመለክት መልኩ»»» “ታላቁ የቊጣ ቀን” በመባል ተሰይሟል። በእርግጥ የሰባቱ ዓመት መከራም ቊጣው የሚገለጥበት መሆኑን መረዳት ተገቢ ነው።

ቆላስይስ 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ በእነዚህም ጠንቅ #የእግዚአብሔር_ቍጣ_በማይታዘዙ_ልጆች_ላይ_ይመጣል፤
⁷ እናንተም ደግሞ ትኖሩባቸው በነበራችሁ ጊዜ፥ በፊት በእነዚህ ተመላለሳችሁ።

የማይታዘዙ ልጆች” እነማን ይሆኑ
¶በእምነት የእግዚአብሔር ልጆች የሆኑ ነገር ግን ለመታዘዝ የደከሙ (ክፍተት የታየባቸው) አማኞች ይሆኑን? #አይደለም
¶ከላይ በጥቅሱ ግልፅ ሆኖ እንደምናነበው:- የእግዚአብሔር ቍጣ የሚመጣው #በማይታዘዙት_ልጆች ላይ እንደሆነ ከገለጸ በኃላ በ7ኛው ቁጥር “#እናንተም_ደግሞ” በማለት አማኞችን»» የማይታዘዙ ብሎ ከመደባቸው ጎራ ለይቶ ያስቀምጣል።

¶በኤፌ.2፥1–3:– በክርስቶስ ሆነው ሕያዋን ከመሆናቸው በፊት አማኞች ስለነበራቸው የቀድሞ ማንነት በግልፅ ያብራራል። በዚሁ ክፍል መሠረት “#የማይታዘዙ_ልጆች” የአየር አለቃ መንፈስ ለሆነው /ለሰይጣን/ ፈቃድ ተገዝተው የሚኖሩ #የቁጣ_ልጆች እንጂ #የእግዚአብሔር_ልጆች_አይደሉም
•|ከዚህ በተጨማሪ በ2ተሰ.2÷8–10 እነዚህ የማይታዘዙ የተባሉቱ የማይታዘዙት ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል እንደሆነና የእግዚአብሔር በቀል የዘላለም ጥፋት እንደሚያስከትልባቸው በዝርዝር ተቀምጦ እናገኛለን።
እኛም ሁላችን እንደዚያው (የቍጣ ልጆች ማለትም ለቍጣ የተጠበቅን) ነበርን። ስለት በስቶ ያቆሰለው፣ የፀሐይ ትኩሳት ያደከመው፣ የግርፋት ብዛት መልከ-ጥፉ ያደረገው፣ ከሰዎች ንቀትን የጠገበ... ያ.. የጽድቅ ልብሳችን ሊሆን ያለልብስ ዕርቃኑን የተሰቀለልን»» በጠላቶቹ ፍቅር ተነድፎ በእንጨት ላይ የተሰፋልን.. በመስቀል የዋለልን ፍቅር #ከጉድ_አወጣን። ክብር ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ለእርሱ ይሁን

¶በአጠቃላይ የዘላለም ጥፋትን የሚያስከትለው የእግዚአብሔር ቍጣ በማይታዘዙ ልጆች ላይ ማለትም ለወንጌል እውነት በእምነት በማይታዘዙት ላይ ሊገለጥ ያለ ነው። #የማይታዘዙ የሚለው ቃል በግሪኩ ἀπείθεια [apeítheia] ሲሆን፤ ትርጓሜውም »» የማያምኑ/ አማኞች ያልሆኑ ማለት ነው።

ኤፌሶን 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁶ ከዚህ የተነሣ #በማይታዘዙት ልጆች ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ይመጣልና ማንም በከንቱ ንግግር አያታልላችሁ።
⁷ እንግዲህ ከእነርሱ ጋር ተካፋዮች አትሁኑ፤
⁸ ቀድሞ ጨለማ ነበራችሁና፥ #አሁን_ግን_በጌታ_ብርሃን_ናችሁ፤


ከዚህ ቀጥለን በቀጣዩ ክፍል አማኞችን የእግዚአብሔር ቍጣ አይመለከትም ማለት ምን ማለት እንደሆነ፣ ምክንያቱስ ምን እንደሆነና ዋስትናው/ ማረጋገጫው ምን እንደሆነ እንመለከታለን።
ጸጋ ይብዛልን አሜን
ይቀጥላል.....
|.MARANATHA DIGITAL NETWORK.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
3.7K viewsYOKABID 4ME, 10:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 08:39:01
DAILY VERSE

“ዳዊትም ስለ እርሱ እንዲህ ይላል፤ “ ‘#ጌታን ሁል ጊዜ በፊቴ #አየዋለሁ፤ እርሱ በቀኜ ነውና፣ ከቶ #አልታወክም።”
— ሐዋርያት 2፥25 (አዲሱ መ.ት)

|.Maranatha Digital Network.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
2.6K viewsCUP 10 »»»»»»»»»»»», edited  05:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 19:58:09 አማኝ በምን ይሸለማል?
ክፍል-6

¶ቅዱሱ መጽሐፋችን ከአዳም አንስቶ የሰዉ ልጆች ሁሉ ፍርድን እንደሚቀበሉ ቢያስተምረንም ሁሉም ግን በተመሳሳይ ጊዜ አንድ አይነት ፍርድ እንደሚቀበሉ አይነግረንም፡፡ እግዚአብሔር አብ በሙታንና በሕያዋን ላይ እንዲፈርድ ለወልድ ሰጥቶታል፤ ቀን ቀጥሮም ወስኗል (ዮሐ. 5፡22)፡፡ የጌታችንም የኢየሱስ ክርስቶስ ትንሳኤ ከሚያረጋግጥልን ብዙ ነገሮች አንዱ:- ማንም ያለ ፍርድ/ ፍርድ ሳይቀበል/ እንደማይቀር ነው (ሐዋ. 17፡30-31)፡፡ ሐዋርያዉ ጴጥሮስ፡- ኢየሱስ አደራ ብሎ ካዘዛቸዉ ጉዳዮች መካከል የፍርድ ነገር መካተቱን መናገሩ… (ሐዋ. 10፡32) እኛም ረጋ ብለን ልናጤነዉ የሚገባ ለመሆኑ ጥርጥር የለዉም፡፡

¶በብዙ አማኞች ዘንድ ስለ ጌታ መምጣት ያለዉ ምልከታ በእግዚአብሔር ቃል መሠረት ሊፈትሽ እና ሊታረም የተገባ መሆኑን ከራሴዉ እርምት ላረጋግጥላችሁ እችላለሁ፡፡ የጌታ መምጣት የምንደሰትበት ሳይሆን የምንሰጋበት እንደዉም ያለንበትን የመንፈሳዊ ህይወት ድካም ተመልክተን #አሁን_ባይመጣ የምንልበት ደረጃ የደረስን ጥቂቶች አይደለንም፡፡ #ልብ_ሊባል_የተገባ_እዉነታ_ግን_የጌታን_መምጣት_እየሰጉ_መኖር_የተስተካከለ_ህይወት_እንዲኖረን_የሚያበረክተዉ_አንዳች_ነገር_አለመኖሩ_ነዉ፡፡ ይልቅ የጌታን መገለጥ /መምጣት/ በጉጉት መጠባበቅ እጅግ መልካም እንደሆነና የጠራን ታማኙ እግዚአብሔር እስከ መጨረሻ ድረስ ራሱ እያጸናን መልካም ኑሮ እንድንኖር እንደሚያስችለን የቃለ-እግዚአብሔር ትምህርት ነው።

¶ከመጽሐፍ ቅዱሳችን አስተምሮ እጅግ በተጻራኒ መጽናኛ ቃል እና ትልቁ ተስፋችን የሆነው የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ መምጣት ጉዳይ አሁን ላይ አማኙ እንድሰጋ ከዳረጉት ነገሮች አንዱ #የፍርድ_ፍርሃት እንደሆነ ግልፅ ነው። “#በፍርድ_ፊት_ቆሜ_ስራዬ_ለመዳን_የማያበቃ_ሆኖ_ከዘላለም_ህይወት_እጎድል_ይሆን?” እንዲህ አይነት ጥያቄዎች ስለጌታ መምጣት ባለን ምልከታ ብዥታ የሚፈጥሩ መሆናቸው አጠያያቂ አይደለም። ስለሆነም በቅዱሱ መጽሐፍ ሰፍረው ከሚናገኛቸው የፍርድ አይነቶች ሁለቱን ቀንጨብ አድርገን ለተወሰኑ ክፍሎች እንደሚከተለው እንመልከት....

የታላቁና ነጩ ዙፋን ፍርድ[ራዕይ. 20፥11-15]

¶በግሪኩ "Thronos" በመባል የሚታወቅ ሲሆን በታላቅና ነጭ ዙፋን ላይ በተቀመጠው እግዚአብሔር ወልድ ፊት ሙታን/ ያለክርስቶስ የሆኑ ሰዎች/ ብቻ የሚቆሙበት ነው።
¶ዓለም በኃጢአት ምክንያት የሚትኰነንበት በመሆኑ ያልዳኑ ሰዎች ብቻ በፍርዱ ፊት ይቆማሉ።
¶ፍርዱ የሚከናወነው #የኋለኛው_ትንሣኤ ተካፋይ በሆኑ ሰዎች ሁሉ ላይ ሲሆን መፈጸሚያ ጊዜውም ከሺው አመት መንግሥት በኃላ ነው።
¶በዚህ ፍርድ ፊት የቆመ ማንኛውም ሰው ስሙ በሕይወት መጽሐፍ ላይ ተጽፎ ያልተገኘ በመሆኑ ወደ ዘላለም ጥፋት /የእሳት ባህር/ ሁለተኛው ሞት ይጣላል እንጂ የመዳን ተስፋ የለውም።

ቅዱሳን ወደዚይኛው ፍርድ እንደማይመጡ የትኛውም ሰው ከተናገረው በላይ ፍርድን ሁሉ ሊፈርድ ከአብ የተቀበለውና ሁሉ የሚመለከተው ወልድ «እውነቱን ልንገራችሁ! ቃሌን የሚሰማ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ህይወት ተሻግሯልና በኃጢአቱ ምክንያት ለፍርድ አይቀርብም።» [ዮሐ.5÷24 ሕያውቃል ትርጉም] ብሎ ተናግሯል።
¶የአድስ ኪዳን ማዕከላዊ ጥቂስ በሆነው ዮሐ.3÷16 የሰፈረውን እውነታ በ18ኛው ቁጥር ሲያብራራ “#በእርሱ_በሚያምን_አይፈረድበትም” ይላል።
ይቀጥላል..........
የጌታ ጸጋ ይብዛልን!!
|.Maranatha Digital Network.|
@Maranatha_Fellowship
@Maranatha_Fellowship2
3.2K viewsYOKABID 4ME, 16:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 10:34:15
‹‹...ሁላችን በክርስቶስ በፍርድ ወንበር ፊት ልንገለጥ ይገባናልና፡፡›› (2ቆሮ.5;10)
በዚህ ጥቅስ መሠረት ፍርድ ተቀባዮችን ለመወከል የገባዉ ''ሁላችን'' የሚለው ቃል እነማንን ያመላክታል?
Anonymous Quiz
56%
ከአዳም ጀምሮ የሰውን ፍጥረት ሁሉ
16%
በክርስቶስ ባለማመናቸው ጠንቅ ፍርድ የሚጠብቃቸውን
19%
በክርስቶስ በማመን ከጥፋት ፍርድ የዳኑትን
9%
መዳንን አግኝተው (የክርስቶስ አካል ብልቶች ሆነዉ) መልካም የማይሰሩትን ብቻ
243 voters3.3K viewsYOKABID 4ME, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ