Get Mystery Box with random crypto!

Lighthouse Training & Consulting PLC

የቴሌግራም ቻናል አርማ lighthouselearningcenter — Lighthouse Training & Consulting PLC L
የቴሌግራም ቻናል አርማ lighthouselearningcenter — Lighthouse Training & Consulting PLC
የሰርጥ አድራሻ: @lighthouselearningcenter
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.97K
የሰርጥ መግለጫ

በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የግል እና ሙያዊ አቅምን የሚያጎለብቱ የተለያዩ አጫጭር ስልጠናዎችን እንሰጣለን።
ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ!
አስተያየትዎን ለመስጠት:-https://t.me/addlist/bKMEnwP0DG83ZGM0

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-22 19:48:11
https://youtube.com/@Anki_Books

በቅርብ ቀን ውስጥ ከተለያዩ #አንቂ #መጻሕፍት የምናገኛቸውን ጠቃሚና አስተማሪ ሃሳቦች #ብቻ ማጋራት የምንጀምርበትን ይህን youtube ቻናላችንን Subscribe በማድረግ ተከተሉን።

#የ"ፍለጠው፣ ቁረጠው" መልእክት የሚተላለፍባቸው Youtube ቻናሎችንን ከምንከታተል እንዲህ ያሉ ቻናሎችን subscribe በማድረግ መከታተል ፋይዳ አለው!

ይህ አዲስ ዩቲዩብ ቻናላችን 1,000 subscriber ላይ ሲደርስ #ብቻ ገራሚና #ህይወት #ቀያሪ #መጻሕፍት የሚዳሰሱባቸውን ቪዲዮዎች መልቀቅ እንጀምራለን።

#አሁኑኑ #subscribe #በማድረግ #ፍላጎታችሁን #አሳዩን!

https://youtube.com/@Anki_Books
1.2K viewsLighthouse- Academy of Success, 16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 15:30:51 የሰው ልጅ ሕይወቱን በእንዴት ያለ መላ እንደሚመራ ሁሉንም የሚያግባባ ወጥ የሆነ የተቀመጠ የኑሮ-ዘዴ የለም፡፡ ሰው ፍላጎቱ፣ ማንነቱ፣ አስተሳሰቡ፣ ዝንባሌው፣ ፍልስፍናው ለየቅል በመሆኑ የአኗኗር ዘይቤውም አልተገናኝቶም እንዲሆን አድርጎታል፡፡ ሰውን በዚህ መንገድ ሕይወትህን ብትመራው ወይም ኑሮህን ብትገፋው ደስተኛና ስኬታማ ትሆናለህ ተብሎ መላ አይታዘዝለትም ወይም prescription አይጻፍለትም፡፡ እሱ የወደደውን፣ ያመነበትን፣ የተቀበለውን፣ የተመቸውንና የቀናውን መንገድ ይይዛል ወይም Subscribe ያደርጋል እንጂ፡፡

ብዙ ሰው የራሱን የሕይወት ፍልስፍና ሌላው ላይ ለመጫን ሲጣደፍ ይታያል፡፡ ሌላው በራሱ የሕይወት መንገድ ተመላልሶ የደረሰበት የአኗኗር ልምድ ሌላ ሰው ላይ ላይገጥም ይችላል፡፡ ሃሳብ ጫሪ ወይም እንደማንቂያ ደውል፤ እንደማበረታቻ ወይም እንደመቀስቀሻ መነሻ ሃሳብ ሆኖ ሊያገለግል ይችል ይሆን እንጂ የመጨረሻው ለሰው ልጅ ሁሉ የሚያዋጣ ምርጡ የሕይወት መንገድ ነው ተብሎ ግን አይወሰድም፡፡ “ምርጥ!” በራሱ አንጻራዊ ነውና!

ይሄንን ሃሳብ በሚመለከት የተለያዩ ምሁራንና ፈላስፋዎች የራሳቸውን ሃሳብ አጋርተዋል፡፡ ከነዚህ መካከል ፈላስፋ፣ የስነልቦና ሊቅ፣ ፀሐፊና የጥበብ ሰው የነበረው ካርል ጁንግ ይገኝበታል፡፡ ይህ ሰው እንዴት መኖር እንዳለብን ለተከታዮቹ በፃፋቸው የግል ደብዳቤዎች የራሱን ምክረ-ሃሳብ አስቀምጧል፡፡ ይህ ታላቅ ሰው ‹‹How to live and the origin of “Do the next right thing”›› በሚባለው አስተሳሰቡ ይታወቃል፡፡ ካርል ጁንግ አድናቂዎቹና ተከታዮቹ ከሆኑ የተለያዩ ሰዎች ስለህይወትና ‹‹እንዴት ስለመኖር›› ለሚነሱለት ጥያቄዎች በደብዳቤ አማካኝነት ምክረ ሃሳቡን ለጠያቂዎቹ ይሰድላቸው ነበር፡፡ እነዚህም ደብዳቤዎቹ ተመርጠውና ተሰብስበው (Selected Letters of C.G. Jung, 1909-1961) በሚል ርእስ በመፅሐፍ ታትመውለታል፡፡

በዚህ መጽሐፍ ውስጥ አንዲት የካርል ጁንግ ተከታይ የሆነች ሴት አንድ የሕይወት ጥያቄ አንስታለት ነበር፡፡ ጥያቄዋም ‹‹እንዴት ልኑር?›› የሚል ነበር፡፡

ካርል ጁንግ ሲመልስ፡-

‹‹ጥያቄሽ ሊመለስ የማይችል ነው፡፡ ምክንያቱም አንቺ ማወቅ የፈለግሽው አንድ ሰው እንዴት መኖር አለበት የሚለውን ነው፡፡ ይሄን ደግሞ የሚያውቀው ራሱ ጠያቂው ነው፡፡ ማንም የሚኖረው እንደሚችለው ነውና (One lives as one can)፡፡ አንድ ሰው እንዴት መኖር እንዳለበት ምንም ዓይነት የተቀመጠ ወይም የተጻፈ መንገድ የለም (There is no single, definite way for the individual which is prescribed for him or would be the proper one)፡፡ አማኝ ከሆንሽ ወደ ቤተ-እምነትሽ መሄድ ትችያለሽ፡፡ ምናልባት እነሱ እንዴት መኖር እንዳለብሽ ሊሰብኩሽ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የራስሽን የአኗኗር ዘይቤ መፍጠር ከፈልግሽ ቀድመሽ ያላወቅሽው ወይም ከማንም ያልተሰጠሸ የራስሽን የሕይወት መንገድ መስራት ይጠበቅብሻል፡፡ ይሄ በእያንዳንዱ የሕይወት እርምጃሽ የሚጀመር ነው፡፡

ሁሌም የሚቀጥለው የሕይወት ተግባርሽ ትክክለኛ ነገርን መከወን ከሆነ የራስሽን የህይወት መንገድ ወይም እንዴት የመኖር ጥበብን በውስጠ-ሕሊናሽ የመፃፍ ብቃትን ታዳብሪያለሽ፡፡ በሌሎች ተደጋፊ ሳይሆን ራሷን በራሷ ሃሳብ ችላ የምትንቀሳቀስ የራሷ አዋቂ ትሆኛለሽ፡፡ ወደፊት እንዴት መኖር እንዳለብሽ ባታውቂም በአሁኑና በሚቀጥለው ሕይወትሽ አስፈላጊውን በማስቀደምና ትክክለኛውን በመከወን ኑሮሽን በደስታና በስኬት ልትሞይው ትችያለሽ፡፡›› ... ሲል መክሯታል፡፡

ጉዳዩን ወደባለቤቱ የሚመልስ ታላቅ ምክር ነው! የሕይወት ቁልፉም፣ የጥያቄው መልሱም ያለው እያንዳንዳችን ጋር ነው፡፡ የሌሎች ሰዎች የሕይወት ቁልፍ የአንተን ወይም የአንቺን የሕይወት በር አይከፍትምና፡፡ በሌላ ሰው መንገድ የሚመላለስ ከግቡ አይደርስም፡፡ ራሱን መምራት የሚችል ሕሊና መፍጠር ያልቻለ በመጣው ወጀብ ይወሰዳል፡፡ ማንም ሲገፋው ይወድቃል፡፡ ስኬት እውን የሚሆነው በራስ መንገድ ነው፡፡ ደስታ የሚገኘው ከራስ ነው፡፡ ያለፈውን ውድቀት መድገም ሳይሆን የሚቀጥለውን አዲስ ሕይወት በማሳመር ነው ሕይወትን በደስታ ማዝለቅ የሚቻለው፡፡ በድግግሞሽ ከመደንዘዝ አካሄድን መለወጥ ዓይነተኛ ዘዴ ነው፡፡ ከድንግዝግዙ አስተሳሰብ በመውጣት ራስን ማብራት የሚቻለው የሚቀጥለውን ተግባራችንን በማስተካከል ነው፡፡

ወዳጄ ሆይ.... ከቆረጥክ የማትወጣው ፈተና የለም፡፡ ፀፀትህንና ጭንቀትህን የምታራግፈው፣ ያለፈው ውድቀትህን ድል የምትነሳው ቀጣይ ስራህን አስፈላጊና ልክ ስታደርገው ነው፡፡ ልክነትህን በራስህ መንገድ ስራው፡፡ በሌሎች መንገድ አትወዛገብ! የራስህን የጠራ መንገድ ፍጠር! በራስህ እጅ የሕይወት ቁልፍህን ቅረፅ! ለምን ወደቅኩ አትበል፤ ለምን ተሳሳትኩ ብለህ ወደኋላ አትመለስ፡፡ ባትወደውም፣ ባላሰብከው አጋጣሚ ወይም ጥሩ መስሎህ የማይፈለግ ቦታ ብትገኝም እውነቱን ተቀበለው! ‹‹ሰው ራሱን በራሱ ካላፀደቀ ምቾት አይኖረውም! (A man cannot be comfortable without his own approval)›› እንዲል ማርክ ትዌይን አንተነትህን እስከነምናምንህ ካልተቀበልክ መረጋጋትና የአዕምሮ ሰላም አይኖርህም፡፡ ጥፋትህን ተማርበት! ውድቀትህን ተለወጥበት! የስኬትህ መወጣጫ አድርገው! የሆነው አንዴ ሆኗልና ሕይወትህን በአዲስ መንገድ ቀጥል፡፡ ዋናው የህይወት ጉዳይ ያለው የሚቀጥለው ላይ ነው፡፡ የሆነውን ነገር መመለስ አይቻልም፤ ቀጣይ የሚሆነውን ነገር ግን መቀየር ትችላለህ፡፡ ወደፊት ምን እንደሚገጥምህ ባታውቅም ስራህ ግን ሁሌ ልክና አስፈላጊ ይሁን፡፡ ልክነትህ ያድንሃልና!

ቀጣይ ተግባርህን በመልካም ጀምር! ሕይወት ይቀጥላልና!

በልክነት ወደፊት!

ፀሃፊው:- እሸቱ ብሩ ይትባረክ
1.7K viewsLighthouse- Academy of Success, 12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 15:30:47
1.5K viewsLighthouse- Academy of Success, 12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 18:11:09 Lighthouse- Academy of Success /የስኬት አካዳሚ/ pinned a photo
15:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 18:10:54
ሁላችንም ነፍስ ካወቅን ጀምሮ ጧትና ማታ የምንደክመው፤ ምን ልስራ? ምን ልማር? የት ልኑር? ማንን ላግባ? በጣም ብዙ ነገሮችን የምንመርጠው፤ ዝንባሌዎቻችንንና ልማዶቻችንን ሁሉ የምናደርገው፤ አብዛህኛውን የጸሎታችንን ክፍል የሚወስደው ስኬት ነው።

ሁሉም ሰው ማስኖ ማስኖ ለውድቀት የሚደክም የለም። ግን ደግሞ ስለ ብርሀን ስናወራ ጨለማን መርሳት አይቻልም። እናም በህይወት ውስጥም እንደ ብርሀንና ጨለማ ስኬትና ውድቀት አብረው ይኖራሉ።

....በየትኛውም የአለም ክፍል ስኬት ትልቅ issue ነው። ስለ ስኬት ሳያወሩ ማለፍ አይቻልም። ...ስኬት ከምናስበው በላይ ደማችን ውስጥ ያለ ነገር ነው። ....ስኬት የህይወት እውነታ ከመሆኑ በፊት ወይም ውድቀት የህይወት ግዴታ ሆኖ ከመምጣቱ በፊት የሚፈጠር ነገር አለ። ይህም አስተሳሰብ ነው (ስለ ስኬት የምናስበው ነገር)።

አንድ ሰው ስለ ስኬትም ሆነ ስለ ውድቀት ምንም አላስብም ቢል እንኳ እሱም አስተሳሰብ ነው። አለማሰብም የአስተሳሰብ አይነት ነው። ስለ ስኬት ምንም አላሰብኩም ከሚለው ጀምሮ ስኬትን ለማምጣት ቀንና ሌሊት ለሚለፋው ወይም ደግሞ ውድቀት ውስጥ ገብቶ በህይወቱ ከሚንገታገተው ሰው ድረስ የስኬት አስተሳሰብ ገዥ ነው። ....

ስለዚህ ስኬት ምንድን ነው? የተሳካለት ሰው ማን ነው? ስኬት ከአስተሳሰባችን ጋር እንዴት ነው የሚጣመረው? የሚለው ዋነኛ ነገር ነው።

(ዶ/ር ምህረት ደበበ በሸገር ካፌ ከጋዜጠኛ መአዛ ብሩ ጋር ከነበረው ቆይታ የተወሰደ)
1.7K viewsLighthouse- Academy of Success, 15:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-20 23:38:20
1.6K viewsLighthouse- Academy of Success, 20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-18 18:35:32
#የተማሪዎች_ውጤት_ለሚያሳስባችሁ_ሁሉ!

በአዲስ አበባ እና በተለያዩ የሃገራችን አካባቢዎች ለምትገኙ #ትምህርት #ቤቶች፣ #የትምህርት #ቢሮዎች እንዲሁም #በትምህርት ላይ #የምትሰሩ #መንግስታዊ #ያልሆናችሁ #ተቋማት በሙሉ!

ህጋዊ እውቅና እና ፍቃድ ያለው ድርጅታችን Lighthouse Training and Consulting PLC/ላይትሃውስ ስልጠና እና ማማከር ኃ.የተ.የግ. ማህበር/ ከ7ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚገኙ ተማሪዎችን የትምህርት ውጤት በከፍተኛ ደረጃ ማሻሻል የሚያስችልና በትምህርታቸው ስኬታማ እንዲሆኑ የሚረዳ፤ በሳይንስ እና ተጨባጭ የምርምር ውጤቶች ላይ የተመሰረተ፤ በአይነቱና በአቀራረቡ የተለየ የስልጠና መርሃ ግብር አዘጋጅቷል።

ተማሪዎቻችሁ የዚህ ስልጠና እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪያችንን እያቀረብን አጠቃላይ የፕሮጀክቱን ሀሳብ በሚመለከት ወይም ለበለጠ መረጃ በተጠቀሰው አድራሻችን ልታገኙንና ልታናግሩን እንደምትችሉ እንገልፃለን።

#አድራሻችን:- አዲስ አበባ፣ የካ ክፍለ ከተማ፣ ወረዳ 12 ልዩ ስሙ ወሰን ግሮሰሪ፣ የአብስራ ህንፃ፣ ቢሮ ቁጥር 05

#ስልክ:-
+251-911- 37-91-79 ወይም +251703-37-91-79
#ኢሜይል:-
lighthouseacademyofsuccess@gmail.com

#አላማችን#የዘንድሮው#የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ውጤት #እንዳይደገም #ድርሻችንን #መወጣት #ነው!

#መምህራን የተማሪዎቻችሁን፤ #ወላጆች የልጆቻችሁን ውጤት #በአጭር #ጊዜ፣ በከፍተኛ ደረጃ ማሻሻል የሚያስችልና #በትምህርታቸው #ስኬታማ #እንዲሆኑ የሚረዳ #ስልጠና ስለሆነ ለትምህርት ቤቶቻችሁ #አመራሮች ይህን #መልእክት #አጋሯቸው።

#ለተማሪዎች #አመች #በሆነ #ቀንና #ሰዓት በትምህርት ቤታቸው ቅፅር ግቢ #በአካል ተገኝተን ስልጠናውን እንሰጣለን።
1.3K viewsLighthouse- Academy of Success, 15:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 20:02:19 ከራስህ አትሽሽ! ከእውነትህ ተፋጠጥ፤ የሰቀልከውን እውነት አውርድ!
(Face the reality!)
(እ.ብ.ይ.)

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ዘንድ በየዓመቱ የሚፆመው የአብይ ፆም ተገባደደ፡፡ ፆሙ የጌታችንንና የመድሐኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የአርባ ቀንና የአርባ ሌሊት ፆም መታሰቢያ የሚያደርግ ዓመታዊ ፆም ነው፡፡ በተለይ የፆሙ ማገባደጃ ሳምንት የክርስቶስን ህማማቱን፣ ግርፋቱን፣ አንግልቱን፣ ስቃዩን የምናስብበት ሳምንት ነው፡፡ አዎ ጌታችን የሰቀሉትን ‹‹የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው›› ብሎ ነፍሱን ቢሰጥም በሶሰትኛው ቀን በመለኮታዊ ሃይሉ ሞትን ድል አድርጎ ተነስቷል፡፡ ሞትን አሸንፏል፡፡ ፍቅሩ ምድርን ሁሉ ገዝቷል፡፡

የሚያሳዝነው ጉዳይ ግን ዓለማችን አሁንም እውነትን እንደሰቀለች መሆኗ ነው፡፡ በዚህ በኛ ዘመንና ትውልድ አሁንም ሐቅ እንደተሰቀለ ነው፡፡ በእውነት የሚነግድ ነጋዴ ጠፍቷል፡፡ በታማኝነት ሐገሩን የሚያገለግል ባለስልጣን ህልም እየሆነ ነው፡፡ ዛሬም እውነት በምድራችን ላይ የለችም የሚያስብል ደረጃ ላይ ደርሳለች፡፡ እውነት ያለው ፍቅር፣ እውነት ያለው እምነት፣ ሐቅ ያለው ንግድ፣ እውነት ያለው ወዳጅነት፣ እውነት ያለው ዝምድና፣ እውነት የሞላው ትዳር፤ እውነት ያለው ዕውቀት፤ ለእውነት የሚወግን ህግ፣ ለእውነት የቆመ መንግስት፣ በሀቅ የሚመራ የሰው ልጅ እየጠፋ ነው፡፡ በድብብቆሽ የጦፈ የሴሰኝነት ፍቅር፤ በወረት የሞቀ ወዳጅነት፣ በመከዳዳት የሚገባደድ ስምምነት፤ በመሰለቻቸት፣ በመጠላላትና በመጠፋፋት የሚያልቅ ወዳጅነት፤ በውክቢያና በችኮላ ተጀምሮ ግለቱን ቶሎ በሚጨርስ የወረት ፍቅረኝነት ዓለም እየታመሰች ነው፡፡ ሰው በገዛ የምኞት ገመዱ ተጠፍንጓል፡፡ ልቅ ፍላጎቱ መረን ለቅቆታል፡፡ ስሜቱ አዋክቦ ከሕሊናው አርቆታል፡፡ ደመነፍሱ ከራሱ ጋር አጣልቶታል፡፡ ስጋውና ነፍሱ፤ ስሜቱና መንፈሱ አልተዋሃደም፡፡ ለመብላት ብቻ የሚኖር ሆዳም ትውልድ ሆኗል፡፡ ለገዛ ጥቅሙ ብቻ ሲል የሌሎችን መብትና ጥቅም የሚጋፋ ስግብግብ ፍጥረት በዝቷል፡፡ ብልጠት እንጂ ብልህነት የሌለው ትውልድ በገፍ እያመረትን ነው፡፡

በዚህ ዘመን እውነቱንና እምነቱን በአፉ ብቻ የሚናገር ነው ምድሪቱን የሞላው፡፡ ለመናገር የፈጠነ፣ ለመስማትና ረጋ ብሎ ለማስተዋል የዘገየ ነው ዓለሙን ያጥለቀለቀው፡፡ በኑሮውና በሕይወቱ እውነቱንና እምነቱን በተግባር አጥብቆ የያዘ እምብዛም ነው፡፡ ሰውነቱን አሽቀንጥሮ የጣለ፣ ስብዕናው የተቃወሰ እልፍ ነው፡፡ ይሄ ሰልጥኛለሁ የሚለው ዘመነኛው ትውልድ ከህሊናው የተጣላ፤ ፍቃደ-ልቦናውን የዘነጋ፣ እፍረት የሌለው ፈጣጣ ትውልድ ስለመሆኑ ብዙ ማሳያዎቹን መዘርዘር ይቻላል፡፡ አዎ የዛሬው ሰው በገዛ ፍቃዱ በላዩ ላይ የባርነት ቀንበሩን አክብዷል፤ የሎሌነት ሸክሙን አብዝቷል፡፡ የሰለጠነ መስሎት ሠይጥኗል፡፡ ገንዘብ ገንዘብ ሲል ግንዛቤውን ጥሏል፣ ማስተዋሉን አጥቷል፡፡ ሰውነቱን ላይደርስበት አርቆ ሰቅሏል፡፡

ሰው እውነትን ሰቅሎ ኑሮውን አስወድዷል፡፡ የዋጋ ንረቱን ጭንቅላቱን አዙሮታል፡፡ ዘንድሮ ያልተሰቀለ ምን አለ? እውነት ተሰቅሏል፤ እምነት ተሰቅሏል፤ ኑሮ ተሰቅሏል፣ የእህልና የቁስ ዋጋ ተሰቅሏል፣ ሰውነት ላይደረስበት ተሰቅሏል፤ ደግነት ተወድዷል፤ ታማኝነት እንደብርቅዬ እንስሳ የሚታይ ሆኗል፡፡ አጃኢብ ነው መቼስ!

ወዳጄ ሆይ..... ያንተስ የአንተነትህ ፋሲካ መቼ ነው?? ያንተስ የሰውነት ትንሳኤህ ወዴት አለ?? ከቶ መቼ ይሆን ከሃሳብ ህመምህ፣ አስተሳሰብ ስቃይህ የምትገላገለው?? የሰው ልጆችስ ከወደቅንበት ስብዕናችን የምንነሳው መቼ ይሆን??

አዎ ወዳጄ! ከመንጋው ጋር አትጋፋ! በስሜት ከሚነጉደው ጋር አትንጎድ፡፡ የበዓሉን ምሳሌነት ተረዳ፡፡ የምታየውን፣ የምትሰማውን ሁሉ ከሕይወትህ ጋር እያገናኘህ አስበው፣ ተንትነው፣ አብሰልስለው፡፡ ከዛም የሚጠቅምህን ውሰድ፡፡ በጎ ነገርን ተለማመድ፡፡ በሚጠቅም አዲስ ሃሳብ ትለወጥ ዘንድ በርታ፡፡ በስቅለቱ በዓል የተሰቀለውን ክርስቶስ ህማሙን እያስታወስክ ዛሬም አንተን እያሰቃየህ ያለው የምኞት ዓለም እየመረመርክ፤ ራስህ አርቀህ የሰቀልከውን እውነት አውርድና ለእውነትና በእውነት ኑሮህን ጀምር፡፡ የትንሳኤውን በዓል ስታከብር አንተን የጣለህንና የአሸነፈህን ቀሽም አስተሳሰብ ድል ነስተህ በአዲስና በቀና አስተሳሰብ ተነስተህ ሕይወትህን አቅናው፡፡

ከራስህ አትሽሽ! ከእውነትህ ተፋጠጥ፤ የሰቀልከውን እውነት አውርድ - Face the reality!

‹‹ጥንት የተሠቀለችው እውነት
ለልብ አብነት ነች፣
ለሰው ምሣሌ ነች፤
በደምና በአጥንት፤ ታስራ የተገመደች፡፡
ውስጠኛዋን እውነት መላልሶ ለመስራት፣
የተሠቀለችውንም እውነት፤ ያሻል አለመርሳት፡፡››

....የትንሳኤውን በዓል ስታከብር አንተን የጣለህንና የአሸነፈህን ቀሽም አስተሳሰብ ድል ነስተህ በአዲስና በቀና አስተሳሰብ ተነስተህ ሕይወትህን አቅናው፡፡...

መልካም የትንሳኤ በዓል!

________________
እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
1.7K viewsLighthouse- Academy of Success, edited  17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 20:02:14
1.6K viewsLighthouse- Academy of Success, 17:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 18:58:45
ሪች ዋልተርስ ይባላል። ኮሎምቢያዊ፣ ቤት አልባ እና ጎዳና ተዳዳሪ ሲሆን ውሎው እና አዳሩ በኮሎምቢያ ጎዳናዎች ላይ ነው። ቀኑ ተገባዶ የኮሎምቢያ አበባ ገበያ ሲበተን ሪች ዋልተር ወደ አበባ መደብሮች በመሄድ ከገበያተኞች የተረፉ እና ከመጠረዝ የተረፉ አበቦችን ይሰበስባል

ይህንን የሚያደርገው ለራሱ አይደለም ይልቅስ በኮሎምቢያ መንገዶች ላይ ለሚያገኛቸው ሰዎች "ደስተኛ ሁኑ! መልካም ቀን ይሁንላችሁ" እያለ ለመስጠት ነው::

ከፊቱ ላይ ፈገግታ የማይጠፋው ዋልተርስ "እኔ ምንም የለኝም ለሰዎች ልሰጥ የምችለው ብቸኛው ነገር ደስታ ነው" ይላል:: ከሪች ዋልተርስ እጅ አበባ የተቀበሉ ሰዎች "ከአበቦቹ ጋር አብሮ የሚለግሰው ፈገግታ እና ደስታ ልብን ያሞቃል" ይላሉ

አንዳንድ ነገሮች ዋጋቸው እልፍ ቢሆንም ነጻ ናቸው !!

(በዘመላዕክ እንድሪያስ)
1.3K viewsLighthouse- Academy of Success, 15:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ