Get Mystery Box with random crypto!

Lighthouse Training & Consulting PLC

የቴሌግራም ቻናል አርማ lighthouselearningcenter — Lighthouse Training & Consulting PLC L
የቴሌግራም ቻናል አርማ lighthouselearningcenter — Lighthouse Training & Consulting PLC
የሰርጥ አድራሻ: @lighthouselearningcenter
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.97K
የሰርጥ መግለጫ

በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የግል እና ሙያዊ አቅምን የሚያጎለብቱ የተለያዩ አጫጭር ስልጠናዎችን እንሰጣለን።
ሊንኩን በመጫን ይቀላቀሉ!
አስተያየትዎን ለመስጠት:-https://t.me/addlist/bKMEnwP0DG83ZGM0

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-04-13 15:06:45
በአንድ ወቅት አንድ ወጣት ሶቅራጥስን የስኬት ምስጢር ምን እንደሆነ ይጠይቀዋል። ሶቅራጥስ ከወጣቱ ጋር በነጋታው ጠዋት ከወንዝ ዳርቻ ለመገናኘት ቀጠሮ ያዘ።

በነጋታው ሁለቱም እየተራመዱ ወደ ወንዙ ገቡ። ውሀው አንገታቸው ላይ ሲደርስ በድንገት ሶቅራጠስ ልጁን ጎትቶ ውሀው ውስጥ ደፈቀው። ልጁ ለመውጣት ቢታገልም ጉልበቱ ከሶቅራጥስ ጋር ሊመጣጠን ስላልቻለ ጥረቱ አልተሳካለትም።

በመጨረሻ ወጣቱ ፊቱ ወደ ሰማያዊነት መቀየር ሲጀምር ለቀቀው። ልጁ አየር ስቦ ከተረጋጋ በኋላ ሶቅራጥስ ጥያቄውን አቀረበለት "ለመሆኑ ውሀ ውስጥ እያለህ ከምንም ነገር በላይ አስፈልጎህ የነበረው ነገር ምንድነው?" ልጁ ምንም ሳያመነታ "አየር" ብሎ መለሰ።

"የስኬትም ሚስጢር ይሄ ነው፤ ልክ አየር የፈለከውን ያህል ስኬትንም ፈልገውና ታገኘዋለህ፤ ሌላ ሚስጥር የለውም" ብሎ መለሰለት።

"ያለህበት አለም የቱንም ያህል አስቸጋሪ ቢሆን የሌሎችን የስኬት ጉዞ ካነበብክ ለስኬት የሚያበቃህን እምነት መፍጠር ትችላለህ!"

--- አንቶኒ ሮቢንስ
1.9K viewsLighthouse- Academy of Success, 12:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-12 18:37:25
አንድ ጀርመናዊ ግለሰብ ነበር አሉ፡፡ ይህ ግለሰብ ዓለምን ለመለወጥ ፅኑ እምነት ነበረው። ምድርን ተለውጣ፣ የተሻለች ሆና ማየት ይመኝ ነበር፡፡ ቀበቶውን ጠበቅ አድርጎ ዓለምን ለመለወጥ በፅኑ ተነሳ። ለዓመታት ደፋ ቀና አለ። ረፍት የለሽ ስራ ውስጥ ገባ። በአታካች እንቅስቃሴ ተወጠረ። ነገር ግን ጠብ ያለ ነገር የለም።

“ምናልባትም ከዓለም በፊት አውሮፓን ለመለወጥ መነሳት ነበረብኝ!” አለና አውሮፓን ለመለወጥ ተነሳ። ዓመታት ቢማስንም ድካሙ የውሃ ሽታ ሆነ።

ተስፋ ሳይቆርጥ ቅድሚያ ሀገሩን ጀርመንን ለመለወጥ ወሰነ። በጣምም ደከመ። በሀገሪቱ ላይ ያመጣው ግን ምንም ለውጥ የለም። ግራ ተጋባ።

ከአካባቢዩ መጀመር አለብኝ ብሎ ወሰነ። እንዳሰበው አልሆነለትም። አይደለም የአካባቢው ማህበረሰብ በደሞዙ የሚያስተዳድራቸው ቤተሰቦቹ እንኳን ለውጥ ማሳየት አልቻሉም።

አንድ ችግር እንዳለ ተረዳ። ከራስ በፊት ሌሉችን ለመለወጥ መሞከር ከንቱ ድካም መሆኑን ተገነዘበ። በመስታወት ከሚያየው የግል ምስሉ ለመጀመር ወሰነ።...ራሱን ለመለወጥ ራሱ ላይ መድከሙን (ኢንቨስት ማድረጉን) ተያያዘው።

ከራስ በፊት ሌሎችን ለመለወጥ መሞከር ከንቱ ድካም...!


ምንጭ፦ ‘የሕይወት ግብህን ቅረጽ’ መጽሐፍ
ዝግጅት በኡስታዝ ያሲን ኑሩ
1.4K viewsLighthouse- Academy of Success, 15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 19:32:13 Lighthouse- Academy of Success /የስኬት አካዳሚ/ pinned a photo
16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 16:26:16 አንድ ሰው ስንት ነው?

(እ.ብ.ይ.)

አንድ ሰው ብዙ ሰው ነው፡፡ ብዙ ሰው ግን አንድ ሰው ሊሆን አይችልም፡፡ የአንድ ሰው ብዙነት ከዕድሜው የሚያገኛቸው ብዝሃ ማንነቱ ነው፡፡ አንድ ሰው በልጅነቱ የልጅነት አስተሳሰብና ማንነት አለው፤ በወጣትነቱም የወጣትነቱን ሰውነትና የትኩስነት ማንነቱን ይይዛል፡፡ ያው አንዱ ሰው ሲጎለምስም የጉልምስና ሰውነትን ያንፀባርቃል፡፡ በአዛውንትነት ዕድሜውም በተረጋጋው ማንነቱ ሰውነቱን ያበጃጃል፡፡ በስተመጨረሻም በዘመነ እርጅናው ትናንቱን እየወቀሰና እያሞገሰ፣ ዛሬ ላይ መካሪና ዘካሪ እየሆነና ወዳለፈው ጊዜ በሃሳብ ፈረስ እየጋለበ፣ ትዝታውንም እያቀነቀነ ወዳማይቀረው ይሄዳል፡፡ እነዚህ ሁሉ የተለያዩ ማንነቶች በአንድ ግለሰብ ህይወት ላይ ወጥተው የሚገቡ፤ ገብተው የሚወጡ ማንነቶች ናቸው፡፡

አምላክ የሰው ልጅ ተፈጥሮን አንድ ጊዜ ቢሰራውም ሰው ግን ማንነቱን ብዙ ጊዜ ያበጃጃዋል፡፡ እንደእውቀቱ መጠን፤ እንደአስተሳሰቡ ደረጃ፣ እንደሕይወት ገጠመኙ፣ እንደአኗኗር ሁኔታው፣ እንደአስተዳደግ ዘዬው ራሱን ይለዋውጣል፤ አዕምሮውን ያድሳል፤ ሃሳቡን ያገላብጣል፡፡ ከተፈጥሯዊው የእድሜ ጉዞው በተለየም ሰው ዕውቀትን ሲጨምር፣ አስተሳሰቡን ሲያድስ፣ ኑሮውን ሲቀይር አዲስ የአኗኗር ዘይቤን ሲከተል አዲስ ሰውነትን ይጎናፀፋል፡፡ ያው አንዱ ሰው ብዙ የተለያዩ ማንነቶችን ለራሱ ይጋብዛል፡፡ ታዲያ አንድ ሰው ስንት ነው? ብዙ ነዋ!

አንድ ጥንታዊ ፈላስፋ ያነሳው ግሩም ጥያቄ ነበር፡፡ ጥያቄውም፡-

‹‹እኔ ራሴ አንድ ሰው ሆኜ አላውቅም፡፡ ምክንያቱም አስቀድሞ እንደህፃን፣ ቀጥሎም እንደወጣት፣ ከዚያም እንደጎልማሳ፣ በመጨረሻም እንደሽማግሌ ኖሬአለሁ፡፡ ከሞት በኋላ ሕይወት ቢኖር እንኳን ዘላለማዊውን ሕይወት እንደማን ሆኜ ነው የምኖረው? የእኔ የሕይወት ተሞክሮ ውጤት ነኝ፡፡ ስለሆነም ሁለትና ሶስት ወይም ከዚያ በላይ የሰው ባሕሪያትን በውስጤ ይዤ በምድር ላይ ከኖርኩ በኋላ ብሞት በምኖረው ሕይወት የመገለጫዬ ባህርይ ማን ሊሆን ነው?›› ሲል ይጠይቃል፡፡

ጥያቄው ወሳኝ ጥያቄ ነው፡፡ ሰው ከሞት በኋላ የማንነት መገለጫው ማን እንደሆነና በየትኛውስ ማንነቱ ሊፈረጅ እንደሚገባ ማወቅ አጓጊ ነው፡፡ እንደእኔ ግን ሰው ከሞት በፊት በመጨረሻ ሕይወቱ የያዘው ማንነቱ በዕድሜው ሙሉ ያያቸውና የተለዋወጠባቸው ማንነቶች ድምር ውጤት በመሆኑ የሚፈረጀውም፣ የሚከሰሰውም፣ የሚደነቀውም ሆነ የሚከበረው በኋለኛው የህይወት ማንነቱ ነው፡፡ ምክንያቱም የመጨረሻው ሕይወቱ የዕድሜው ሁሉ መጠቅለያ ማንነት ነው፡፡ ሰው በዕድሜው ካያቸው የራሱ የተለያዩ ማንነቶች የሚወሰደውን ወስዶ፣ የሚጣለውን ጥሎ መልካሙን ማንነት መያዝ የእሱ ድርሻ ነውና፡፡ ከራስ መማርን የመሰለ ምን ወሳኝ ትምህርት አለ?! ምንም!

እድሜ ካልተማርንበት ቁጥር ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ቁጥር ብቻ ደግሞ ዋጋ የለውም፡፡ ዋጋ ያለው ሕይወት እውን የሚሆነው የሰው ልጅ ዕድሜ በበጎ ስራ ሲቆጠርና ሲተመን ብቻ ነው፡፡ በዚች አስገራሚ ዓለም ሽማግሌ ሆነው እንደ ልጅ የሚኖሩ፤ ልጅ ሆነው እንደአዋቂ የሆኑ መኖራቸው ሃቅ ነውና፡፡

ከሞት መለስ በሕይወት እያለ የሰው ልጅ መጠየቅም፣ መኮነንም፣ መደነቅም ሆነ መከበር ካለበት በአሁናዊው ማንነቱ ነው፡፡ ዛሬ ማንነቱን በበጎ አስተሳሰብ የዋጀ ሰው ትናንት ባጠፋው መወቀስ የለበትም፡፡ የትናንቱ ጥፋት በትናንት ማንነቱ ነው ሊፈረጅ የሚገባው፡፡ ዛሬ አዲስ ሰው ነውና!

የአመክንዮ ሕግም በትናንት ማንነቱ የዛሬውን አዲስ ማንነቱን የሚደመድሙ ሰዎች ልክ እንዳልሆኑ ይናገራል፡፡ ይሄንንም Miss-representation Fallacy ሲል ይገልፀዋል፡፡ ዛሬ አዲስ ሰው ነውና የትናንቱን ሽሯል፡፡ የትናንት አሮጌ አስተሳሰቡን በአዲስ አስተሳሰብ አድሷል፡፡ የትናንት አላዋቂነቱን በዛሬ ዕውቀቱ ቀይሯል፡፡ ትናንት ያልገባው ዛሬ ገብቶታልና፡፡

ታላቁ የነፃነት ታጋይ የነበሩት ኔልሰን ማንዴላ እንዲህ ይሉናል፡-

‹‹በስኬቴ አትዳኙኝ፡፡ ይልቁንስ ምን ያህል ጊዜ ወድቄ ምን ያህል ጊዜ መልሼ እንደተነሳሁ አይታቹህ ፍረዱኝ (Do not judge me by my success, judge me by how many times I fell down and got back up again)›› ይላሉ፡፡

አዎ! የአወዳደቅህ ሳይሆን የአነሳስህ ሁኔታ ያንተን ማንነት አጥርቶ ያሳያል፡፡ የወደቁ ሳይሆን ከውድቀታቸው የተነሱ አዕምሯቸው ሰፊ ስለመሆኑ ክርክር አያሻውም፡፡ በጠባቡ አስተሳሰባቸው ወድቀው በሰፊ አስተሳሰባቸው ሕይወታቸውን ያሰፉና ከውድቀታቸው የተነሱ ትንሳኤ ብሩሃን የሆኑ ሊደነቁ ይገባል፡፡ ምክንያቱም በመውደቅ መነሳታቸው መካከል ያገኙት ትምህርት እንዴት ከውድቀት መነሳት እንደሚቻል አዲስ ዕውቀት አስጨብጧቸዋል፡፡ ተስፋ ቆርጠው ወድቀው አለመቅረታቸው የሚያሳየው የአስተሳሰባቸው ጮራ ምን ያህል የበራ እንደነበረ የሚያሳይ ነውና፡፡

አዎ! ዛሬ ዛሬ ብዙዎቻችን በተለያዩ ውድቀቶችና አወዳደቆች ተፍገምግመናል፡፡ የሚያሳፍረውና የሚያስፈራው ነገር ከውድቀታችን ለመነሳት ፍላጎቱም ሆነ ቁርጠኝነቱ የሌለን መሆኑ ነው፡፡ አንዳንዶች በዘረኝነት ወድቀዋል፣ ጥቂቶች በትእቢት በአፍጢማቸው ተተክለዋል፡፡ ቀላል ቁጥር የሌላቸው አወቅን ብለው ደንቁረዋል፤ ሰፋን ብለው ጠብበዋል፡፡ ሰለጠንን ያሉት እቡያን ሰይጥነዋል፡፡ ከዕድሜአቸው ያልተማሩ፤ ከብዝሃ ማንነታቸው ቀለም ያልቆጠሩ፣ መልካሙን ያልኮረጁ ቆመ-ቀሮች ቤት ይቁጠራቸው፡፡ ከብዝሃ ማንነታቸው ያልተማሩ በአንዱ ማንነታቸው የሙጥኝ ያሉ አዲስ ሃሳብ ያስደነግጣቸዋል፤ ለውጥ ይቀፋቸዋል፤ አዲስ ማንነት ያስፈራቸዋል፡፡

አዎ! አንድ ሰው ብዙ ነው፡፡ ብዙነቱን ግን እውን የሚያደርገው በሰፊው አስተሳሰቡ ሲሰፋ ነው፡፡ ከተፈራረቁበት ማንነቶቹ ጠቃሚውን ማንነት ፈልቅቆ የሚያወጣ ብልህ ሰው ከብዙነቱ እልፍ ትምህርት ቀስሟል፡፡ ቅስሙን የሚሰብር ሳይሆን ቅስሙን በአዲስ አስተሳሰብ የሚጠግን ጀግና ካለፈው ሕይወቱ ብዙ የተማረ ነው፡፡ ከውድቀቱ የሚማር መላልሶ መነሳት አይቸግረውምና፡፡

ወዳጄ ሆይ… አንተ አንድ ሰው አይደለህምና እንደብዙ ሰው አስብ የዕለቱ መልዕክት ነው! መውደቅን አትፍራ! ነገር ግን እንዴት ከወደቅበት ቦታ መነሳት እንደምትችል አዕምሮህን አሰራ፡፡ መውደቅ በማንም ላይ የሚደርስ ነው፡፡ ከዛ ይልቅ ወድቆ መቅረት ነው አሳፋሪው ነገር፡፡

ቸር መነሳት! ቸር ትንሳኤ! ቸር ብዝሃነት!

እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
1.8K viewsLighthouse- Academy of Success, 13:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-08 16:26:11
1.6K viewsLighthouse- Academy of Success, 13:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 20:58:36 በአንድ ገበሬ ቤት የምትኖር አይጥ ነበረች። ታዲያ ከለታት አንድ ቀን ይህችው አይጥ ገበሬው እና ባለቤቱ እቃ ሸምተው ወደ ቤታቸው ሲገቡ ትመለከትና ለእኔ የሚሆን ምን ገዝተው ይሆን? ብላ በቀዳዳ አጮልቃ ስታይ ፍፁም ያልጠበቀችው ነገር፡፡ የተገዛው ነገር የሚበላ ሳይሆን የአይጥ ወጥመድ ነበር፡፡

በድንጋጤ ውስጥ እንዳለች ከጉድጓዷ ወጥታ እየሮጠች በግቢው ውስጥ ወዳሉት የቤት እንስሳት ሄደች፡፡ መጀመሪያ ያገኘችው ዶሮን ነበር… እየጫረች ጥራጥሬ ስትለቅም፡፡ “ማነሽ አንቺ ዶሮ፣ ኧረ ጉድ አልሰማሽ፣ ቤት ውስጥ ወጥመድ ተገዝቷል፡፡” ብትላት ጊዜ ዶሮዋ እየተቆናጠረች “እና ምን ይጠበስ! አንቺ ተጨነቂበት እንጂ እኔን የሚያሳስበኝ ነገር አይደለም” አለቻት፡፡

አይጧ እየተበሳጨች ወደ በግ ሄደችና “ስማኝማ አቶ በግ፣ ቤት ውስጥ የአይጥ ወጥመድ ተገዝቷል፤ እባክህ አንድ ነገር እናድርግ!!” ስትል በተማፅኖ ብጠይቀውም በጉ ካቀረቀረበት ሳር ላይ ቀና ሳይል “በጣም ያሳዝናል! ግን ልረዳሽ አልችልም፤ ራስሽ ተወጪው” አላት፡፡
አሁንም አይጥ ቁና ቁና እየተነፈሰች፣ ወደ በሬ ዘንድ ሄደችና ቤት ውስጥ ስለተገዛው ወጥመድ ነገረችው፡፡ በሬውም ምንም ሳይመስለው እንዲህ ሲል መለሰላት፣ “እንዴው ምን ይሻልሻል? ባይሆን በግና ዶሮ ይርዱሽና አንድ ነገር አድርጊ፤ እኔን እንኳን ተይኝ፡፡”
አይጧ ተበሳጭታ፣ “ኧረ ተው አንድ ነገር ብናደርግ ይሻላል፤ ለጊዜው ቢመስላችሁም ችግሩ የጋራችን ነው!!” ስትል ተናገረች፡፡

ሁሉም ተያይተው ተሳሳቁባት፡፡ “ቀልደኛ ነሽ!” እየተባባሉ፡፡ አይጥም ተስፋ ቆርጣ ወደ ጉድጓዷ ገብታ ለሊቱን ሙሉ እንቅልፍ ሳይወስዳት አደረች፡፡

ማታ ወጥመዱ ተጠምዶ እያለ ቀጭ የሚል ድምፅ ሲሰማ የገበሩው ሚስት ተስፈንጥራ ተነሳች. . . ወጥመዱ የያዛትን አይጥ ለማየት፡፡ ጭለማ ስለነበረ በዳበሳ ወደ ወጥመዱ ሄዳ ወጥመዱን ስትነካው በአይጥ ፋንታ የተያዘው መርዘኛ እባብ ስለነበረ ነደፋት፡፡ በነጋታው የገበሬው ሚስት ከሀኪም ቤት ስትመለስ ራስምታት እንዳያስቸግራት ተብሎ ዶሮዋ ታረደችና ሾርባ ተዘጋጀላት፡፡ የገበሬው ሚስት ህመሙ እየጠናባት ሲሄድ በቶሎ እንድታገግም ተብሎ በግ ታረደላት፡፡ ሆኖም ግን ሴትዮዋ ማገገሟ ቀርቶ ሞተች፡፡ ይህንን ተከትሎ ዘመድ አዝማድ ለለቅሶ ሲመጣ ለተስካር በሚል በሬውም ታረደ፡፡

አይጥም ቁጭ ብላ እያለቀሰች ሶስቱም ሲታረዱ አየች።

ችግር ሲመጣ ለጊዜው አንድ ሰውን ብቻ የሚጎዳ ይመስላል፡፡ ሁሉም አያገባኝም ይላል፤ ቆይቶ ግን ሁላችንንም ይበላል፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ አክቲቪስቶች፣ ሚዲያዎች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ በስልጣን ላይ የሚገኙ አካላትም ሆነ ተራው ዜጋ እዚህ አገር በሚከሰቱ ችግሮች ላይ በጋራ እስካልተንቀሳቀሱ ድረስ ለሁላችንም የመጣውን ችግር ከሥሩ ነቅለን መጣል አይቻለንም፡፡

ልዩነት ሊኖረን ቢችልም የጋራ የሚያደርገንም ነገር አለ፤ እሱም ‹የጋራ ቤታችን የሆነችው ኢትዮጵያ ናት›፡፡

የአገር ጉዳይ ነጥብ የማስቆጠርና ያለማስቆጠር አይደለም፤ የአገር ጉዳይ የሁሉም ጉዳይ ነው፡፡

በአገር ላይ የተደቀነ አደጋን ዝም ብለን ያለፍነው እንደሆን እንደሞኙ በግ፣ እንደ ቸልተኛው በሬ እና እንደ ሆድ አደሯ ዶሮ ከመበላት አናመልጥም፡፡

አይጧ እንዳለችው. . .

“ለጊዜው ቢመስልም፤
ለኔ የመጣ ጢስ ላንቺ አይመለስም፡፡”
2.5K viewsLighthouse- Academy of Success, 17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 20:58:32
2.2K viewsLighthouse- Academy of Success, 17:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 17:03:50 Lighthouse- Academy of Success /የስኬት አካዳሚ/ pinned a photo
14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 17:03:25 1. ተስፋ አድራጊ መሆን ረጅም ርቀት ይዞህ ይሄዳል፡፡

በጣም አስከፊ በሆኑ ጊዜያት እንኳ ተስፋ ባለመቁረጥ ችግሮችን መጋፈጥና ለመቀየር መቁረጥ የመፍትሄ መላ እንዲመጣልን ያደርጋል፡፡ ስለዚህ ተስፋ አትቁረጥ፣ ጨለምተኛ አትሁን፡፡

2. መርህ፣ አቋም፣ ያመንክበት ጉዳይ ይኑርህ ነገር ግን ለመስተካከል ቦታ ይኑርህ፡፡

በደረስክበት እውቀት መሰረት በነገሮች ላይ አቋም ሊኖርህ ይገባል፡፡ ነገር ግን የህይወት ዘመን ሁሉ ተማሪ ከሆንክ በአንድ ወቅት የያዝከው አቋም ትክክል እንዳልሆነ ስትረዳ ያመንክበትን ጉዳይ ማስተካከል ይኖርብሃል፡፡

3. አዋዋልህን እና ጓደኞችህን ምረጥ፡፡

አስተሳሰብህን እና ድርጊትህን በገንቢ ጎን ከሚተቹና ከሚገነቡ ሰዎች ጋር የምታደርግ ከሆነ በየጊዜው እየተሻሻልክ የምትሄድ ሰው ትሆናለህ፡፡ ባህሪህ እና ህይወትህ እያደር የሚመስለው የጓደኞችህን ነው፡፡

4. መሆን የምትፈልገውንና መስራት የምትፈልገውን በጊዜ አውቀህ ጀምር፡፡

በወጣትነት ጀምረህ መርጠህ የምትሄበት መንገድ እያደር አንተንም እየቀረፀህ ስለሚሄድ በዛው የመቀጠል እድል ይጨምርልሃል፣ አይቻልም ለሚሉህ በቀላሉ ላትሸነፍ ትችላለህ፣ በእድሜህ ብዙ ሳትገፋ ስኬታማ እና ብዙ ተፅእኖ አምጪ ትሆናለህ፡፡ የራስህን ራእይ የማትገነባ ከሆነ ሌሎች ቀጥረውህ ራእያቸውን እንድትገነባላቸው ያደርጉሃል፡፡

5. ከሌሎች ጎበዞች ጋር በጥምረት ስራ፡፡

ከጎበዞች ጋር በጥምረት ስትሰራ አንተ የማታውቃቸውን ነገሮች ያሳውቁሃል፣ አንተ ልታገኛቸው የማትችላቸውን ሰዎች እንድታገኝ እድል ይከፍቱልሃል፣ ይበልጥ ወደፊት ያራምዱሃል፡፡

6. በቅፅበት ከፍተኛ ደረጃ እደርሳለሁ አትበል፡፡

ከትምህርት ቤት አንደወጣህ ወዲያው ሃብታም፣ ባለስልጣን፣ ወይም ስኬታማ እሆናለሁ ብለህ አትጠብቅ፡፡ ከፍተኛ ትምህርት ቢኖርህ እንኳ ስኬታማ ለመሆን ብዙ ልምድ ያስፈልግሃል፡፡

7. ስለ ስህተቶችህ ሌሎችን ሳይሆን ራስህን ውቀስ ተማርባቸው፡፡

ስህተቶች እንድንቆጭባቸው ሳይሆን እንድንማርባቸው ካደረግን ደግመን አንሰራቸውም፡፡

8. በተቀጣጠለ መንፈስና መሰጠት ስራ፡፡

መርጠህ ወይም ፈልገህ የምትሰራውን ስራ በከፍተኛ ትጋት፣ መሰጠት፣ መቀጣጠል የምታደርግ ከሆነ ስራ አስደሳችና ቀላል ይሆንልሃል፡፡ የምትሰራው ስራ ውስጥ እነዚህ ነገሮች ከጠፉ ወይም የምትሰራው የሚሰለችህ ከሆነ የምትሰራው ነገር የውስጥ ፍላጎትህን ማንፀባረቁ አጠራጣሪ ነው፡፡

9. ምርጡ ትምህርት ቤት ኮሌጅ ሳይሆን ህይወት ነው፡፡

ምንም ያህል መፅሀፎች ብታነብ፣ ፈተናዎችን ብትወስድና ብታልፍ፣ በህይወት ሂደት የምትማረውን ያህል ብቁ አያደርጉህም፡፡ ስራዎች እና የስራ ሃላፊዎች ያስተምሩሃል፣ ያበቁሃል፡፡

10. እውነተኛ ኑሮና ህይወት በቴሌቪዥን እንደምታየው አይደለም፡፡

ኑሮ ቲቪ ላይ ስታይ እንዳለው ካፌዎች ሄዶ ዘና ማለት ከመሰለህ ተሳስተሃል፡፡ ስራ ሰርተህ ኑሮህን ህይወትህን ለመለወጥ ተንቀሳቀስ፡፡

11. ህይወት ሁሌም የቀና አይደለም፡፡

በህይወት ጉዞህ ትገጫለህ ትወድቃለህ፡፡ ኑሮ ፈተና ነው፣ ጌም መሳይ ነው፣ ተነስተህ እስኪሳካልህ ጉዞህን ቀጥል፡፡

12. የራስ ስራ መስራት ድፍረትና ብከስርም እሰራለሁ ማለትን ይጠይቃል፡፡

ቢዝነስ በአንድ ጎኑ አንደ ቁማር ነው፡፡ 100% ማሸነፍ መቻልህን ቀድመህ እርግጠኛ መሆን አትችልም፡፡ ከቁማር የሚለየው ግን ማጥናት፣ ማቀድና፣ ሁኔታዎችን እያየህና እየቀያያርክ በጥንቃቄ መተግበር መቻልህ ነው፡፡

13. ለስኬታማነት ትእግስት እና ጠንክሮ መስራት ያስፈልግሃል፡፡ በአቋራጭ የሚመጣ ዘላቂ ስኬት የለም፡፡

14. ለራስህ ክብር ይኑርህ፣ በማንነትህ ኩራ፡፡

እያንዳንዳችን የተለያየን ስለሆንን ራስህን ከሌላው ጋር እያወዳደርክ ዝቅተኝነት አይሰማህ፡፡ በሌላው ውስጥ የሌለ አንተ ውስጥ ያለ ችሎታ ስላለ ፈልገህ አግኘው፣ ተቀበለው፣ እዛ ላይ አተኩር፣ አዳብረው፣ በራስህ ተማመን፡፡ ስኬታማ የምትሆነው በዚህ መንገድ ነው፡፡

15. ራስህን አታሳብጥ፡፡

ስኬታማና ታላቅ የመሆን ራእይ መሰነቅ ተገቢ ነው፤ ነገር ግን ዛሬ ላይ ብትወጣ ነገ ደግሞ ታች መውረድ ሊገጥምህ ይችላል፡፡ ላይ መውጣትህ የብዙ ነገሮች ጥምር ውጤት ስለሆነ ራስህን አይነኬና ልዩ ፍጡር አድርገህ አታስብ፡፡

16. ነገሮችን በቀና በመውሰድ ተማር፡፡

በስራህ ያልተደሰቱብህ ደንበኞችና ትችቶቻቸው፣ ስህተቶችህ፣ ውድቀቶችህ ታላቅ የመማሪያ መሳሪዎች ናቸው፡፡ ከነዚህ የሚመጣውን አስተያየትና ትችት አጣመህ አትመልከት፣ ተማርባቸው፣ ራስህን ለውጥባቸው፡፡

17. በአለም ስላለው ከፍተኛ ድህነት፣ የሃብት ልዩነት፣ ችግር አስብ፡፡

ቴክኖሎጂና ሃብት እየተስፋፋ በሄደ መጠን አለም ከቀድሞ ይልቅ የተሻለች ቦታ እየሆነች ነው፡፡ ነገር ግን ብዙዎች የሚኖሩት አስከፊ ድህነት፣ በሽታ፣ ወዘተ ደግሞ ሊቀየር የሚገባው እና የሚችል መሆኑን አስብበት፡፡

18. ስኬትህን አካፍል፡፡

አንተ ከፊትህ ከነበሩት ስኬታማ ሰዎች ታሪክና ፍሬአቸው እንደ ተነቃቃህ፣ እንደተማርክ እና እንደተጠቀምክ ሁሉ አንተም የስኬትህን ምክንያቶች እና ውጤቶች ለሌሎች አካፍል፡፡ መሪነት ሌሎችን ለስኬት ማብቃት ነው፡፡

19. አርተፊሻል ኢንተለጀንስ፣ ኤነርጂ፣ እና ባዮ ሳይንስ ጥሩ የትምህርት ዘርፎች ስለሆኑ እነዚህን ተማሩ፡፡

እነዚህ የትምህርት ዘርፎች ወደፊት ከፍተኛ ተፅእኖ የሚፈጠርባቸው ናቸው፡፡

20. ደሃ ሆነህ ተወልደህ ከሆነ ጥፋቱ የአንተ አይደለም፤ ደሃ ሆነህ ልትሞት ከሆነ ግን ጥፋቱ የአንተ ነው፡፡
1.1K viewsLighthouse- Academy of Success, 14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 17:03:21
898 viewsLighthouse- Academy of Success, edited  14:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ