2023-06-03 22:03:32
በገጠመን ፈተና ላይ ሌላ ችግር የምትፈጥሩልን ሰዎች እባካችሁ ታቀቡልን!
-----------------
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ሆይ! እየደረሰብን ያለው መከራ የሸገር ሲቲ የመስጂድ ፈረሳን ተከትሎ ፅንፍ የረገጠው ርህራሄ ቢሱ የብልፅግና አመራር በንፁሀን ላይ የከፈተው የ"ተኩሰህ ግደል" ዘመቻ መሆኑን በአይናችን እያየን ነው።
ይሁንና ይህን ፈተና አስታከው ችግሩ ከመጅሊስ የመጣ አስመስለው የቀድሞውን ስርአት አስናፋቂ እንባ አላቃሾችን እያየን ነው።
እነሆ አእምሮ ላለው ሁሉ ቆም ብሎ ራሱን ጠይቆ እንዲመልስ አንድ ጥያቄ እጠይቀዋለሁ:-
አፈሙዝ ደቅኖ እየገደለ ያለውን ስርአት የተጋፈጡት ሙፍቲ ቢሆኑ ምን ያመጣሉ??
ይህን ጥያቄ ቆም ብላችሁ አስባችሁ መልሱት!!
ችግሩ ከአመራር ስርአቱ እንጂ ከመጅሊሱ እንዳልሆነ እያየነው ያለው እውነታ ነው። መጅሊሱ ደግሞ ያለ ርህራሄ እየገደለ ያለውን ስርአት ተጨባጭ እያየ ህዝበ ሙስሊሙን "ተዘጋጅ፣ መስጂድህን ጠብቅ፣ ራስህን አስከብር..." ወዘተ የመሰለ ቀጭን ትእዛዝ ቢያስተላልፍ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አስቡት!!
እንኳን እንዲህ ብሎ ቀርቶ እንዲሁም እያየነው ነው።
ስለሆነም ጉዳዩን እንደ መጅሊስ አመራሮች ስናየው የእውነትም ግራ ቀኝ አይቶ መነጋገር ካለበት አካላት ጋር ተመካክሮና ተወያይቶ አስቦና ወስኖ ነው እንጂ መልክት ወደ ሙስሊሙ ማስተላለፍ ያለበት እንዲሁ በለው እንዲል የምትጠብቁ የዋሆች ጉዳዩ ዘመናዊ መሳሪያ ከታጠቀው ከባለ ወታደሩ መንግስትና እስኪሪብቶና ወረቀት ከያዘ መጅሊስ መሀል ያለ ፍጥጫ መሆኑን ልብ ልትሉ ይገባል።
ከዚህ በመቀጠል ሌላው ወሳኙ ነጥብ ፈተና ሲመጣ ሙስሊም ከመቼውም የበለጠ ይተሳሰራል፣ አንድነቱን ይጠብቃል፣ ይናበባል። በዚህ አካሄዱ ነው ድል ማድረግ የሚችለው።
ስለሆነም አንድነቱን በሚያፍረከርክ ፅሁፎችና ጉዳዩን የእርስበርስ መጠላለፍ በሚያደርጉ የሚዲያ ስራዎች ላይ የተጠመዱ አካላትን ፈፅሞ ልንነቃባቸው ይገባል። የፈተና ሰአት ላይ እንገኛለንና እየመራ ካለው አመራር ጋር ጉዞን ወደፊት ማድረግ ብቻና ብቻ የሚያዋጣን ሰአት ላይ ነን!! በዚህ ሰአት "ሙፍቲዬ ናፈቁን" ጨዋታ በፈተናችን ላይ ሌላ አንድነትን የማጣት ፈተና ከመጨመር ውጪ ምን ይጠቅማል!!!
በፈተና ሰአት ተረጋግቶ ማሰብን ነው የኛ ነብይ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ያስተማሩት። ይህን ተግባራዊ ማድረግ ካልቻልን ድል እየራቀን ይመጣልና ቆም ብለን እናስብ!!!
ወሰላም!!!!!!!!!!
ኑርሁሴን ጋሹ
7.3K views19:03