Get Mystery Box with random crypto!

ጉራማይሌ Delivery 🇪🇹

የቴሌግራም ቻናል አርማ guramaylebooks — ጉራማይሌ Delivery 🇪🇹
የቴሌግራም ቻናል አርማ guramaylebooks — ጉራማይሌ Delivery 🇪🇹
የሰርጥ አድራሻ: @guramaylebooks
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 15.57K
የሰርጥ መግለጫ

ምንም አይነት መፅሀፍ ይዘዙን ያሉበት ቦታ ድረስ በነፃ እናመጣሎታለን፡
በሚያስገርም "ከ10-50%" በሆነ የዋጋ ቅናሽ ሞክረው ይዩን በአገልግሎታችን ይደሰታሉ
Free delivery
@Guramaylebooks
@Guramayelie 0912319263

Ratings & Reviews

1.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2022-07-02 20:14:11
የዕውቀት ብልጭታ. ከከበደ ሚካኤል
የገፅ ብዛት - 184 የተለጠፈበት ዋጋ - 250 ብር
መሸጫ ዋጋ - 170 ብር >= 3 Free delivery
Contact us @Guramayelie 0912319263

Telegram : t.me/guramaylebooks
Twitter : twitter.com/guramaylebooks
Facebook : facebook.com/guramaylebooks
IG : Instagram.com/guramayle_books
Email : guramaylebooks@gmail.com ።
3.2K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-01 01:03:21
3.6K views22:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 10:04:08
ሕይወት ከባድ ነች - በጭንቀቶች፣ በውጥረት፣ በአስፈሪ ክስተቶች የተሞላች። እና ይህንን ሁሉ ጠራርጎ ለማስወገድ ምን ማድረግ ይኖርብናል? እንዴትስ እነዚህን ሁሉ ችግሮች እንደ ተራ ነገር ንቀን ልናልፋቸው እንችላለን?
ፍልስፍና ቀላል ሆኖ ሊተገበር የሚችል መፍትሄ ያቀርብልናል - #ሜሜንቶ_ሞሪ
ሜሜንቶ ሞሪ የላቲን ሃረግ ሲሆን ትርጓሜውም “እንደምትሞት አስታውስ” ማለት ነው። አይቀሬ ስለሆነው ሞት ስታስብ ለዚህ ሁሉ ጉዳይ መጨነቄ አግባብ ነው ወይ? የሚል ጥያቄን ታነሳለህ።
የሮም ንጉስ እና ፈላስፋ የነበረው ማርክስ አውሬሊየስ ይህን ሃሳብ አጥብቆ ይወደዋል። ሞት ተፈጥሯዊ እና አይቀሬ ነው ንብረትን ለማፍራት መሮጥ፣ አለማዊ ሃብትን ማሳደድ… ይህ ሁሉ ልፋታችን ይዘነው ለማንሄደው ኮተት ነው ይለናል። አንድ ቀን አፈር እንሆናለን፤ ስለምንስ ምድራዊ ጊዜያችንን በጭንቀት ውስጥ እናሳልፋለን?
ሶቅራጠስም፣ ዘርዓ ያዕቆብም የዘመናቸው ወፈፌዎች ነበሩ። እንኳን ሊጠየቁ ሊታሰቡ እንኳ የከበዱ ጥያቄዎችን አንስተው መርምረዋል። ሶቅራጠስን ያስገደለው፤ ዘርዓ ያዕቆብንም ከአገር ያሰደደ ፍልስፍና ምንድን ነው?


ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ እስከ ሶቅራጥስ
ትርጉም በፍሉይ ዓለም
የገፅ ብዛት - 352 የተለጠፈበት ዋጋ - 350 ብር
መሸጫ ዋጋ - 210 ብር >= 3 Free delivery
Contact us @Guramayelie 0912319263
3.9K views07:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 07:50:38
ከዚህ በፊት ያሳተማቸው ሶስቱ መጽሐፍት ፀረ-666፣ ሣድስ፣ እና አልፈራም በሰፊው ተወዳጅነትን ያስገኙለት ጋዜጠኛ መምህር ዐቢይ ይልማ የመጀመሪያውን መጽሐፉን ቀጣይ ክፍል ፀረ-666 ቁጥር 2 ለገበያ አቅርቦልናል። መልካም ንባብ ይሁንላችሁ።

ፀረ-666 ቁ2. መ/ር ዐቢይ ይልማ
የገፅ ብዛት - 222 የተለጠፈበት ዋጋ - 280 ብር
መሸጫ ዋጋ - 200 ብር >= 3 Free delivery
Contact us @Guramayelie 0912319263
6.1K views04:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-14 22:29:38
የካህሳይ አብርሃም መጽሐፍ በአሲምባ የግል ታሪኩ ላይ ያተኮረ ነው። የታሪክ ኩርባዎቹም፦ ወላጆቹ፣ ከሱ ጋር ነፍስ የተቀባበለው ይመር ንጉሤ የተባለው ገበሬ ፤ እና አሲምባ የወለደለት ድላይ የተባለች ጓድ ፍቅረኛው፤ ናቸው። መጽሐፉ የአሲምባ ጓዶቹ ታሪክ ላይ ያተኮረ ነው። ባለታሪኩ፤ የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ሠራዊት (የኢሕአፓ የታጠቀ ክንፍ) ውስጥ እስከነበረበት ወቅት ድረስ፣ ያሳለፈውን ሁኔታ በመንተራሱ፤ አንድም በዚያው አካባቢ የተወለደ በመሆኑ፣ አንድም እዚያው የታገለ በመሆኑ፣ ስለትግራይ ልዩ ልዩ ስፍራዎችም በቅርበት ያስረዳናል። በኢሕአሠ ዐይን በመመልከት፤ በዚያ ክልል ይንቀሳቀሱ የነበሩትን ሌሎች ድርጅቶች ሁኔታም ያገናዝብልናል። ከቦታው፣ ከፖለቲካው እንቅስቃሴ እና ከህዝቡ አኳያ ያ ጊዜ ምን አይነት ስዕል ይታይበት እንደነበር ያስረዳናል። (ገጣሚ፣ ፀሐፊ፣ ተርጓሚ፣ ጋዜጠኛ... ነብይ መኮነን ስለመጽሐፉ ከሰጡት አስተያየት የተወሰደ)

የአሲምባ ፍቅር. በካሕሳይ አብርሃ ብስራት
የገፅ ብዛት - 439 የተለጠፈበት ዋጋ - 300 ብር
መሸጫ ዋጋ - 260 ብር >= 3 Free delivery
Contact us @Guramayelie 0912319263
5.2K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:11:40
ባህላችን አሁንም አለ አልተዘነጋም የኛ ድርሻ ማስቀጠል ብቻ ነው!!!
5.3K viewsedited  08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 11:10:41
ከዚህ መጽሐፍ ገጾች የምታገኛቸው ነገሮች በከፊል፡-
በዓለማችን ታዋቂ የሆኑ ባለፈጠራ ክህሎትና ስኬታማ ሰዎች ራዕያቸውን እውን ሊያደርጉ የቻሉበትን ድብቅ ልማድ፤
ፍርኃትን ወደ ብርታት፤ ችግርን ወደ ኃይል፤ የቀድሞ ችግርን ወደ ድል መቀየር የሚያስችል ተቀዳሚ ብልኃት፤
ራሳችሁን ብርቱ በማድረግ ቸልተኝነትን አሸንፋችሁ በሥራችሁ ላይ የምታንፀባርቁበትን ብልኃት መገንዘብ፤
ዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ልማዶች በመረዳት የልዕለ-ሰብ ብቃት የተላበሰ እና በሥነ-ምግባር የታነፀ ስብዕናን መላበስ፤
ነገገሮችን በቀላል መንገድ፤ በውበትና በሰላም የምትከውኑበትና ልዩ ጥበብ ማወቅ . . .
ሮቢን ሻርማ- የዓለማችን የአመራር ጥበብና የግል አቅም ማጐልበት አማካሪዎች ቁንጮ ነው፡፡ የእርሱ ደንበኞች ከሆኑት መካከል- ዓለም አቀፍ ዝነኞች፣ ቢሊየነሮች፣ የኤን. ቢ. ኤ ቅርጫት ኳስ ከዋክብት . . . . እንዲሁም ከኩባንያዎች ደግሞ ስታርባክስ፣ ፌዴክስ፣ ጀነራል ኤሌክትሪክ፣ ማይክሮሶፍት፣ ናይክ እና ቲ. ዲ. ባንክ ይጠቀሳሉ፡፡ ከ15 ሚሊዮን እትም የበለጠ የተሸጠለትና ሥራዎቹ በ 92 ቋንቋዎች ተተርጉመው የተነበቡለት ሻርማ በዓለም አቀፍ የተነባቢነት ደረጃ በሕይወት ካሉ ደራሲያን አንደኛ ነው፡፡


የጀግና ማኒፌስቶ
ሮቢን ሻርማ
የገፅ ብዛት - 370 የተለጠፈበት ዋጋ - 350 ብር
መሸጫ ዋጋ - 260 ብር >= 3 Free delivery
Contact us @Guramayelie 0912319263
4.9K views08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-29 08:02:10
ስሙ መጽሐፍትን በትረካ የሚያቀርብላችሁ የሞባይል መተግበሪያ ነው። ሲፈልጉ በቋሚ ደንበኝነት ተመዝግበው ሲፈልጉ ደግሞ በአንድ ጊዜ ክፍያ አባል መሆን ይችላሉ። የብዙ ደራስያንን ስራዎች በድምጽ በመቅዳት እያቀረቡ ነው ለምሳሌ በብዙ አንባብያን ዘንድ ተወዳጅ የሆኑት የአዳም ረታ መጽሐፍትም ይገኙበታል።
ከዚህ በተጨማሪም የታላላቆቹ ደራስያን አለማየሁ ገላጋይ፣ እንዳለጌታ ከበደ፣ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ አንዷለም አራጌ፣ ዮርዳኖስ አልማዝ እና ሌሎችም ስራዎች ተካተውባቸዋል። መተግበሪያቸውን አውርደው ነጻ የሚለቀቁ መጽሐፍቶቻቸውን አዳምጠው ቼክ ያድርጉ እና ከወደዱት ቀጣዩ የእርስዎ ምርጫ ነው።
ጉግል ማከማቻ ፡ https://bit.ly/SemuGooglePlay
አፕል ማከማቻ፡https://apple.co/3gzblVH
ድረ-ገፅ፡ https://www.semuaudiobooks.com/
6.2K views05:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:28:53 ዳግማዊ ምኒልክ ካህናትንና ሴቶች ሳይቀሩ ባንድነት አስተባብረው ኢትዮጵያውያንን ባንድ እግር አቁመው በአገር ወራሪ ፊት አሰልፈዋል ቀኑን ሙሉ በማዋጋት ይኸን ዓለም የተዶነቀበትን ድል ባኙበት ማታ ወደ ሰፈራቸው ሲመለሱ : አዲ ፈቂ ጐታ ላይ ወጥተው በእንዳ ሰንበት ቤተክርስቲያን ገብተው ይኸን ድል ለሰጣቸው እግዚአብሔር ምስጋና አቅርበዋል። አዲ ፈቂ በእንዳ ኪዳነ ምሕረት በመነኮሲይቶ ተራራ መካከል የሚገኝ ነው። የአዲ ፈቂም ተራራ ከባሕር ከፍታው 2062 ሜትር ነው። ከሌሎቹ አብያተ ክርስቲያናት ወደዚህ መሔድን የመረጡት ምናልባት ጦርነቱ የተደረገው የካቲት 23 ቀን እሑድ ስለሆነ የአዲፈቂ ቤተ ክርስቲያን እንዳ ሰንበት (የሰንበት ቤተ ክርስቲያን) ስለሆነ ዕለተ ሰንበት ‘የለቱ ለት ቀናኝ’ በሚሉ እምነት ይሆናል።

ከዚያ ወርደው ሠራዊቱ “እየገደለ ሰጠው ላሞራ!” እያለ በሆታ እያጀባቸው በደስታና በእልልታ ወደ ሰፈራቸው ደረሱ። ወደ ድንኳናቸው ገብተው በዙፋናቸው እንደ ተቀመጡ ፥ ጦርነቱን እንደ ወንድ በትጋት የተካፈሉት የሚወድዋቸው ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ በኢትዮጵያ ልማድ ለዠግና ፥ ለገዳይ እንደሚደረገው ሁሉ ንጉሠ ነገሥቱ ወደ ተቀመጡበት ዙፋን ቀርበው እጅ ነሥተው የድል አድራጊነት ምልክት የሆነውን የወርቅ ሎቲ በዦሮአቸው አንጠለጠሉላቸው።

በማግሥቱም ፥ በዓድዋና በአክሱም ዙሪያ ያሉ ካህናት ለድሉ በዓል ተሰብስበው ነበርና ምራቱ በቅድሚያ ለአክሱም ካህናት ስለተሰጠ ካህናቱ ከድጓ ውስጥ “ሞዖ ለሞት ሰዓሮ ለጣኦት ወገብረ ትንሣኤ በሰንበት” (የድጓው ትርጉም “ሞትን አሸነፈ ጣኦትንም ሻረ ፥ በሰንበትም ትንሣኤ አደረገ” ተብሎ ለጌታችን በጳውሎስ የተነረውን ለምኒልክ ለማውረስ ነው። ጢሞቴዎስ ምዕ.1 ቁ.10 ፥ ዕብ.2 ቁ.14) የሚለውን ጥቅስ ገሠው አዜሙ። ምስማክም “እንተ ቀጥቀጥኮ አርእስቲሁ ለከይሲ ወትሁቦሙ ሲሳዮሙ ለሕዝበ ኢትዮጵያ” የሚለው ከዳዊት መዝሙር ተዘመረ።

በአዲስ አበባ ገና የጦርነቱ ወሬ ሳይሰማ ውጊያውና ድሉ በተፈጸመበት ቀን የጊዮርጊስ ለት የቤተ ክርስቲያኑ አለቃ መምህር ጽጌ የሚባሉት ሊቅ የተቀኙት መወድስ ቅኔ እንዶ ትንቢት ሆኖ ተደንቆ ላቸዋል። ቅኔው ታሪካዊ ስለሆነ እንደሚከተለው አስፍረነዋል።

በሕፅነ ምኒልክ ይረፍቅ ሰማዕተ ልዕልና
ወበሕፅነ ሰማዕት ይትሐወስ አሰረ ምኒልክ ላዕክ
እስመ እም ሮምያ ፈትተ አድባረ ድንጋጼ ወሀውከ
ምኒልክ ንጉሠ አድኅኖ ዘኢዮር መልአክ
ወእግረ ምኒልክ ኢይትሐወክ
እስመ በቅድሜሁ የሐውር ጸያሔ ፍኖት ወልደ አምላክ
ቡርክትሂ ገነተ ጽጌ እስመ ውእቱ ቡሩክ
ዓለመ ምኒልክ ቀዳማዊ ዘይመጽእ ምኒልክ
ወሎቱ ሶርያ ትሰግድ ወታስተበርክ
በጽባህ እስመ ቀርበ ሙስና ሮምያ መሥዋዕተ ሠርክ

በሙሉ ሁሉን መተርጐም ምንም ያህል ስለማይጠቅም ከሙሉው አንዳንዱን ፍሬ ነገር ግዕዝ ለማያውቁ እናብራራለን። አምስተኛውና ስድስተኛው ሐረግ ፥ “ወእግረ ምኒልክ ኢይትሐወክ። እስመ በቅድሜሁ የሐውር ጸያሔፍ—ኖት ወልዶ አምላክ” “መንገድ ጠራጊው ወልደ አምላክ በፊቱ ስለሚሔድ ፥ የምኒልክ እርምጃ አይደናቀፍም” ማለት ነው ወልዶ አምላክ የራስ መኰንን የክርስትና ስም ስለሆነ መኰንን ግንባር ቀደም ጦር አዝማች እየሆኑ በአላጌና በመቀሌ እየተዋጉ ለንጉሠ ነገሥቱ የጦርነት ጉዟቸውን ያቀኑትን ለመጥቀስ ነው።

ከሁሉ የቅኔ ሐረጐች የመጨረሻው መስመር ፥ “በጽባህ እስመ ቀርበ ሙስና ርምያ መሥዋዕተ ሠርክ” “የሮማ ጥፋት እንደ ዕለት መሥዋዕት በጧት ቀርቧል” ያሉት ለባለቅኔው እንደ ደንበኛ ትንቢት ተቆጥሮላቸዋል። በእርግጥም ግንባር ቀደም ሆኖ በጧት ግሥጋሤ ደርሶ የተማረከው የዤኔራል አልቤርቶኒ ጦር የተመታውና የኢጣልያ ጦር ቅስሙ የተሰበረው ከጧቱ ላይ ስለሆነ “በጽባሕ እስመ ቀርበ ሙስና ሮምያ . . .” ብለው የጦርነቱ ዕለት የጦርነቱን ወሬ ሳይሰሙ የተቀኙትና በተግባር የተፈጸመው በትክክል ተገናኝቷል። አዲስ አበባም እንደገቡ ዐፄ ምኒልክ ይኸንኑ ሰምተው ሸልመዋቸዋል ይባላል።



ከ ተክለጻዲቅ መኩርያ
"ዐፄ ምኒልክ እና የኢትዮጵያ አንድነት" መጽሐፍ ላይ የተወሰደ
6.9K views16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-16 19:28:39
ዐፄ ምኒልክ እና የኢትዮጵያ አንድነት
ከተክለ ጻድቅ መኲሪያ
የገፅ ብዛት - 708 የተለጠፈበት ዋጋ - 557 ብር
መሸጫ ዋጋ - 450 ብር >= 3 Free delivery
Contact us @Guramayelie 0912319263
5.0K views16:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ