የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
162
የሰርጥ መግለጫ
We will inform you of new things as much as we can💯
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
2
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2
2023-02-23 17:03:50
በአለማችን ላይ እየተበራከተ የመጣው
የራስን ማጥፋት ሙከራ በጣም እየጨመረ ሲሆን
ምክኝያቶቹም
ድብርት
ከቴክኖሎጂ ጋር ያለመጠን ቅርርብ
ከሰው ጋር የመገናኝት ፍላጎታችንመቀነስ ከብዙወቹ ጥቂቶቹ ሲሆኑ
በአለማቺን ከፍተኛ የራስ ማጥፋት ሙከራ የሚደረግባት
ጃፓን ስትሆን
ምክንያቱም ጃፓኖች ሲበዛ ወግ አጥባቂ ናቸው
ይህ እንዳለ ሆኖ ግን
30 በመቶ የሚሆኑት ራሳቸውን የሚያጠፍት
ፈተና በመውደቅ እንደሆነስ ያውቃሉ
https://t.me/Goncha24
https://t.me/Goncha24
https://t.me/Goncha24
113 views14:03
2023-02-23 10:33:32
የዋቻሞ ዩኒቨርስቲ የመደበኛ የተማሪወች አቀባበል ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ትምህርት ዘመን አዲስ ገቢ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪዎችን መቀበል ጀምሯል።
በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው 50 ከመቶ እና ከዚያ በላይ ያመጡ ተማሪዎች በ15 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች መመደባቸው ይታወቃል።
ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ከ1 ሺህ በላይ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ተመድበውለታል።
https://t.me/ethio24new
https://t.me/ethio24new
https://t.me/ethio24new
113 viewsedited 07:33
2023-02-23 08:50:21
ውሾቹ ይጮሀሉ ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል> በነገራችን ላይ "ውሾቹም ይጮኻሉ ግመሎቹም ይሄዳሉ" የሚለው አባባል የአረብ ነጋዴዎች አባባል እንደሆነ "የኔ ጀግና" የሚለው የሙሃዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት መጽሐፍ ላይም ሰፍሮ እናገኛለን።
አረቦች በግመሎቻቸው የንግድ እቃዎቻቸውን ጭነው በሚሄዱበት ሰዓት የበረሃ ውሾት በጣም ቢጮሁባቸውም እነሱ ላይ ድንጋይ በመወርወር ጊዜን አያባክኑም፤ ምክንያቱም የውሾቹ መጮህ ግመሉን ከጉዞው አያቆመውምና።
በአንድ ወቅት የእንግሊዝ መሪ የነበረው ዊንስተን ቸርችልም ይህንን ብሎ ነበር...
"ባንተ ላይ ለሚጮህ ውሻ ሁሉ እየቆምክ ድንጋይ የምትወረውር ከሆነ ከአላማህ በቶሎ አትደርስም" ንግግሩ እውነታን ያዘለም ነው።
መልስ ለሚገባው እንጂ ለተናገረ ሁሉ መልስ መስጠት አግባብ አይደለም የጊዜ ብክነትም ነው። ምክንያቱም አንዳንዶች የሚጮሁት ትክክለኛ ጥያቄን እና መልእክትን ይዘው ሳይሆን እኛን ከመስመራችን አስወጥተው ከራሳቸው ጎራ ለመመደብ ነውና።
https://t.me/ethio24new
https://t.me/ethio24new
https://t.me/ethio24new
107 viewsedited 05:50
2023-02-22 21:56:08
ሴቶች አውሬ ወንድ ይወዳሉሴቶች ውስብስብ ናቸው፣ ለዚህም ሳይሆን አይቀርም ከተረጋጋ ህይወት ይልቅ ውጥንቅጡ የወጣ (chaotic) ህይወትን የሚመርጡት። ሰላማዊ እና የተረጋጋ ህይወትን በቶሎ ይሰለቻሉ።
ምሳሌ የሚሆነን ... ጸባየ ሸጋና አንገቱን ደፍቶ ከሚኖር ወንድ ይልቅ ልባቸው የሚርደው ለአውሬው ወንድ ነው።
በአንድ ወቅት የጉግል ኢንጂነሮች "ሴቶች ምን አይነት ወንድን ይፈልጋሉ?" የሚል ጥናት አካሂደው ነበር።
ጥናቱም እንደሚያመላክተው በአብዛኛው ሴቶች የሚነበቡ መጽሐፍቶች ተመሳሳይ የታሪክ ይዘት አላቸው - አንዲት ምንም የማታውቅ ውብ ሴት ከአንድ የአውሬነት ወይም የአፈንጋጭነት ጠባይ ካለው ወንድ ጋር በፍቅር ትወድቃለች። ሴቷም ይህን ቁጡ የሆነ ፍጥረት አማላ፣ በራሷ መንገድ ገርታ ታቀዘቅዘዋለች።
ሴቶች የሚወድቁላቸው አውሬ ወንዶች እነማን ናቸው?
ሴት፣ ልክ እንደ ኮኮናት ፍሬ ውጪው ጠንካራ እና የማይሰበር፣ ውስጡ ግን ጣፋጭና ለስላሳ ወንድን ትፈልጋለች - በሌሎች ፊት የገዘፈ፣ ከእሷ ውጪ ለማንም የማይንበረከክን ወንድ!
... ለእሷ ጣፍጦና ለስልሶ ለሌሎች የማይረታ፤ እሷ ብቻ በውስጡ ያለውን ልስላሴና ጣፋጭነት ታገኘዋለች።
የገጹ አንባቢዎች ተሳተፉበት... ሴቶችም፣ ወንዶችም እስቲ ሀሳብ ስጡበት...
https://t.me/ethio24new
https://t.me/ethio24new
127 viewsedited 18:56
2023-02-22 17:53:43
የ12 አመት ህፃን ልጅ ላይ የጋብቻ ስነስረዓት በፈፀመ የ28 አመት ዲያቆን ጌታቸው ላይ የ1 ዓመት ከ8 ወር የእስራት ቅጣት ተወሰነበት በምስራቅ ጎጃም ዞን በግንደወይን ከተማ አስተዳደር የ12 አመት ህፃን ልጅ ላይ የጋብቻ ስነስረዓት በፈፀመ የ28 አመት ወጣት ላይ የ1ዓመት ከ8ወር የእስራት ቅጣት የተወሰነበት መሆኑን ፋስት መረጃ ከጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ፍትህ ጽ/ቤት ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
ተከሳሽ ዲያቆን ጌታቸው አለልኝ አግባብ ባለው የቤተሰብ ህግ ከተፈቀደው ውጭ ለአካለ መጠን ያልደረሰች ልጅ ለማግባት በማሰብ ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም በግምት ከሌሊቱ 11፡0ዐ ሲሆን በግ / ወይን ከተማ አስተዳደር ዐ1ቀበሌ ልዩ ቦታው አርሴማ ቤተክርስቲያን ውስጥ የግል ተበዳይ የ12 ዓመት ህፃንን በተክሊል ጋብቻ ወይም በሀማኖት ስርዓት ያገባት በመሆኑ ተከሳሽ በፈፀመው ለአካለ መጠን ያልደረሰችን ልጅ ማግባት ወንጀል ዓ/ህግ የሰውና ጋብቻው ሲፈፀም የሚያሳይ የፎቶ ማስረጃ በማያያዝ ክስ መስርቶ ተከሳሽም የዓ/ህግ ክስ በችሎት ተሰጥቶት የዓ /ህግ ክስ በችሎት ተነቦለት ክሱን እንዲረዳው ከተደረገ በኋላ ወንጀሉን መፈፀሙን አምኖ ነገር ግን ህፃናትን ማግባት በቤተክርስቲያ ህግ የተፈቀደ ነው ወንጀል አይደለም በማለት ተከራክሮ ፍ/ቤቱም የህግ ምስክሮችን ሰምቶ በወ/መ/ስ/ስ/ህ/ ቁ113/2 / መሠረት ፍ/ቤቱ ወደ ወንጀል ህግ አንቀጽ 648 /ሀ/በመቀየር እንዲከላከል ቢጠይቀውም ተከሳሽ ግን የመከላከያ ምስክር የለኝም በማለት በማመልከቱ በቀን 13/6/2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሹን እና ሌላውን የህብረተሰብ ክፍል ያስተምራል ተብሎ የታሰበውን የአንድ ዓመት ከስምንት ወር ቅጣት ውሳኔ ተላልፎበታል ፡፡
https://t.me/ethio24newhttps://t.me/ethio24new
138 viewsedited 14:53