Get Mystery Box with random crypto!

መረጃ//mergaa

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethomergaa — መረጃ//mergaa
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethomergaa — መረጃ//mergaa
የሰርጥ አድራሻ: @ethomergaa
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.11K
የሰርጥ መግለጫ

@ethomergaa
🎩ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ ፣
🎩የአስተሳሰብ ምህዳሮች ፣
🎩የምሁራን እይታዎች እና መጽሐፈቶች ፣
🎩የአለም ሙሉ መረጃ እና የታሪክ ልዩ መዛግብቶች ።
ለማንኛውም መረጃ 👉 @Natiyt
ኢትዮጵያዊ ሆኘ የተወለድኩ ኢትዮጵያዊ ሆኘ ያደኩ ኢትዮጵያዊ ሆኘ መሞት የምፈልግ ኢትዮጵያዊ ነኝ። ኢትዮጵያ በክብር ለዘለአለም ትኑር አሜን !!!
የናንተው ቻናል ነው

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-30 08:55:24 እሸቴ ሞገስና ቤተሰቡን አስታውሰህ ታገል!

ወያኔ በአፋር በኩል ጦርነት ሲከፍት የትም ሳይደርስ ከአንዴም ሁሉት ግዜ አሩን በልቶ ተመልሷል! ህዝብ ለመከላክያም ለልዩ ሃይሉም ሚሊሻው ሞራል እየሰጥ ተጋድሏል ወያኔ መጣ ሲባል ጏዙን ጠቅሎ ጥሎ አልሄደም ስንቅ ይዞ ሞራል እየሰጠ ነበር ወያኔም መሄድ ማለፍ ሳይችል የአፋር በርሃ ውስጥ ያስቀሩት!

ወያኔ በወልቃይት ጠገዴ በኩል እንኳን ሊዋጋ እስከዛሬ አንድም ነገር ሞክሮ አያውቅም ጅራፍ እንኳን አላጮኸው አይደለም ጥይት! ለምን? የጎንደርን ህዝብ ወያኔ ጠንቅቆ ያውቀዋል አልደፈር ባይ ነው ይህ እየመረረህ እምትውጠው ግልጽ ጉዳይ ነው!

ወያኔ ከአንድም ሁሉት ግዜ በራያ በኩል ጥቃት አድርሶ የመጀመሪያው እስክ ሸዋሮቢት ደርሶ ተመልሷል አሁን ቆቦ ነው ያለው ለምን ተመሳሳይ ነገር ወያኔ በዚህ አቅጣጫ እዲህ ሊፈነጭ ቻለ ጠይቅ እራስህን መርምር! ከሌላው ተማር!

እንደ አፋር ህዝብ ለመከላክያ ልዩ ሃይል ፋኖ ደጀን ሁን ወያኔ መጣ ሲባል ጏዝህን ጠቅለህ አትውጣ:: አንተ ለመከላክያ ልዩ ሃይል ፋኖ ደጀን ሆነህ ሞራል ካልሰጠኸው አንተ ጏዝህን ጠቅለህ ስትወጣ የትግል ስሜትን ትገላለህ! ከትግል በላይ ለታጋዩ ጦረኛው ወኔ እየሰጠህ አይዞ ነው ማለት ያለብህ! ይህን ካላደረክ ዝም በል አንተ ተሸብረህ ሌላውን የሚያግዘውን አታሸብር ስራውን ለመከላክያ እና ደጀን ለሚሆኑት ጀግና የአካባቢው ሰዎች ተውለት መከላክያም ሆነ ጥምር ሃይሉ ከድጀን ህዝቡ ጋር ሲፈልግ ያፈግፍግ ሲፈልግ ያጥቃ::

ይኸው ነው!
427 viewsmenty (ßoss), 05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 08:55:24
በጦርነት ወቅት በጊዜያዊነት ስለሚወሰነው ስልታዊ ማፈግፈግ ማወቅ የጠላት የቅጥፈት ፕሮፖጋንዳ ሰለባ ከመሆን ያድናል። በውጊያ ውስጥ የሚገኝ አንድ የወገን ኃይል በተለያዩ ምክንያቶች የማፈግፈግ ቁመናን በጊዜያዊነት ሊይዝ ይችላል። ይኸውም እየተካሄደ ያለው ውጊያ ሊያስከትል የሚችለው ጉዳት ከጥቅሙ ልቆ ከተገኘ፣ በሕዝብና በሠራዊቱ ላይ አላስፈላጊ መስዕዋትነት የሚያስከፍል ከሆነ፣ ጠላት ቆርጦ በመግባት ከወገን ኃይል ደጀን ጋር እንዳይነጣጥል እንዲሁም የትጥቅና ስንቅ መስመሮችን እንዳይዘጋ ለማድረግ፣ የጠላት ኃይልን ወደ መግደያ ወረዳ ስቦ ቅርቃር ውስጥ በማስገባት በአነስተኛ ኪሳራ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ፤ የማፈግፈግ ቁመና አመቺ ነው በሚባልበት ወቅትና ሁኔታ ሊያዝ ይችላል።

ይህ በስፍራው የሚገኝ ታክቲካል የሠራዊት መሪ አሊያም የስትራቴጂክ መሪዎች ውሳኔ ሊሆን ይችላል። እናም በማናውቀው ታላቅ ሙያ ውስጥ እየገባን አንፈትፍት። ውጊያ "የጌም ጨዋታ" አይደለም። ሕይወትን የመስጠት ታላቅ ሀገራዊና ሕዝባዊ ኃላፊነት ያለበት፣ በጥበብ የሚሰራ ድንቅ ተጋድሎ ነው። ስለሆነም "የቄሳርን ለቄሳር፣ የእግዚሐብሔርን ለእግዚሐብሔር" እንደሚባለው፤ የውትድርናን ሙያ ለባለሙያው እንተወው።

እምነታችንን በጠላት አሉባልታ ሳይሆን፤ ውጊያውን በታላቅ ጀግንነት በሚመራው በባለድሉ አይበገሬው ሠራዊታችን ላይ እንጣል። ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን የኢትዮጵያዊነት ፅናት አርማ ነው። በጠላቶቻችን የፈጠራ ወሬ አንመራ። የጠላቶቻችንን የለየለት ቅጥፈት በመመከት፣ በዓለም ፊት ቅሌቱን እናከናንበው። ይህን ስናደርግ፤ የወገን ኃይል ተደማሪ አቅምና ደጀን፣ የጠላቶቻችን መቅሰፍትና ራስ ምታት ሆነን እንቀጥላለን

ድል ለጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን

Good Night Ethiopiaዬ
424 viewsmenty (ßoss), 05:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 15:17:57 የተመድ የኒውክሌር ተቆጣጣሪ ቡድን ወደ ዛፖሪዝሂያ የኒውክሌር ጣቢያ አቀና

የዓለም አቀፉ አቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ ኃላፊ ግሮሲ "የዩክሬን እና የአውሮፓ ትልቁን የኒውክሌር ጣቢያ ደህንነት መጠበቅ አለብን" ብለዋል
https://am.al-ain.com/article/iaea-mission-heads-to-ukraine-s-zaporizhzhia-nuclear-plant-near-war-frontline
485 viewsmenty (ßoss), 12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 15:17:57
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በዛሬው ዕለት ተከታታይ የደንበኞች የኔትወርክ አገልግሎት ሙከራ በድሬዳዋ ከተማ መጀመሩን አስታወቀ፡፡የደንበኞች የሙከራ ምዕራፍ፥ ኩባንያው በአገር አቀፍ ደረጃ አገልግሎቱን ለመስጠት ከሚዘጋጅበት ጊዜ አስቀድሞ በተለያዩ ክልሎች እና ከተሞች የኔትወርክ እና የአገልግሎት ጥራቱን በተጠናከረ ሁኔታ የሚፈትሽበት ሂደት መሆኑ ተመላክቷል፡፡

በድሬዳዋ ከተማ የደንበኞች የኔትወርክ ሙከራ በ2G፣ 3G እና 4G ኔትወርኮች የሚካሔድ ሲሆን÷ ደንበኞች በ07 በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ መስመር የስልክ ቁጥሮቻቸውን መርጠው ሲም ካርድ መግዛት እንደሚችሉ ተገልጿል፡ደንበኞች የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ሲም ካርዶች የድርጅቱ መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች ማግኘት እንደሚችሉ እና ኔትወርኩን ለአንድ ወር ያህል እንዲሞክሩት የሚረዳ የደንበኝነት ማስጀመሪያ የዳታ፣ የድምጽ እና የጽሑፍ መልዕክቶች ጥቅል ያገኛሉም ተብሏል፡፡

የደንበኝነት ማስጀመሪያ ጥቅሉ በሚያልቅበት ጊዜ ደንበኞች የአየር ሰዓት ከሽያጭ ማዕከላት ወይም መለያ ከተለጠፈባቸው መደብሮች እና ሱቆች በመግዛት መሙላት እና አገልግሎቱን በቀጣይነት መጠቀም እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡በድሬዳዋ ከተማ አገልግሎት በሚጀምረው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የሙከራ ኔትወርክ ደንበኞች፥ ዳታ መጠቀም፣ ጥሪዎች እና የጽሑፍ መልዕክቶችን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ከኢትዮ ቴሌኮም ደንበኞች ጋር መለዋወጥ እንዲሁም ዓለም አቀፍ ጥሪዎችን ማድረግ እንደሚችሉ መገለጹን ከሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

[Reporter]
457 viewsmenty (ßoss), 12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:57:28
ለብዙ ወራቶች በድንገት ለሚከፍተው ለጦርነት በእርዳታ የመጣ እህልን በመሳርያ በመለለወጥ በዝግ ሰራዊቱን እና ጦርን ሲያደራጅ የከረመው ህወሃት በአጭር ጊዜ ውስጥ ሽንፈትን እየተከናነበ ይገኛል።

በጦር እና በሰራዊት ተደራጅቶ እንደመጣ ቢሰማው ዳሩ የወገን ኃይል የሚወስደውን እርምጃ ለቀናት እንኳን መቋቋም አልቻለም። ወደ ወልድያ ጉዞ አረጋለው የሚል ተስፋን ይዞ ቀድሞ ሳይደርሱ ፕሮፖጋንዳ ሲነዙ የነበሩት የወያኔ ቅጥር ሚዲያዎች እና አክቲቪስቶች ህልማቸው መቼም የማይሰካ ቅዥት እንደሆነ አረጋግጠዋል።

ብዙ ተስፋ የጣሉበት የወያኔ ጦር መነሻውን ባረገበት ቆቦ ከተማ ዳግም እንዳይንቀሳቀስ፣ በ4ቱም አቅጣጮች ከፍተኛ ጥቃት እንደደረሰበት የደረሰን መረጃ ያስረዳል።

ታጣቂዎች በተወሰደባቸው ከፍተኛ እርምጃም ለማምለ ጥቂፆች እንደሸሹ እና በርካተቹ በፍቃዳቸው እንደተማረኩ መረጃዎች ያስረዳሉ።

“በድል እናጠናቅቀዋለን፣ ኢትዮጵያን እናፈርሳለን” ብለው የተነሳው ጁንታ በሁሉም አቅጣጫ ያለው የወገን ጦር አስደንብሮት እግር አውጪኝ ፍርጠጫን ጀምሮል፤ በተቃራኒው የወገን ጦር በጥምር ኃይል ተጠናክሮ፣ ኢትዮጵያን መጠበቅ ዋነኛው ተልዕኮ አድርጎ ለድል ብስራት ወደፊት እየገሰገሰ ውጤት እያመጣ ይገኛል።

“ተው ሲባል አልሰማ ያለን የሀገር ጠላት፣ ሰላም ፈላጊነት እንደ ሽንፈት የሚቆጥርን ዱርዬ ቡድን መታገስ አያስፈልግም!!!” በሚል ቆራጥነት የተነሳው የኢትዮጵያ ጥምር ኃይል በአጭር ጊዜ ውስጥ ንፁኃን ዜጎችን ሳይነካ ጁንታን እንደሚቀብረው ግልፅ ነው። ለዚህም ውጤት በተለያዩ መንገዶች የሚደረገው የህበረተሰቡ ድጋፍ የሚኖረው ዋጋ ደሞ ከፍተኛ ነው።
451 viewsmenty (ßoss), 09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:57:27
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአልጄሪያ ዋና ከተማ በሚገኘው የሰማዕታት ሀውልት የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ ስርዓት አከናውነዋል

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአልጄሪያ ዋና ከተማ በሚገኘው የሰማዕታት ሀውልት የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ ስርዓት አከናውነዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በአልጀሪያ እያደረጉት ባለው ይፋዊ የስራ ጉብኝት በርዕሰ መዲናዋ አልጀርስ የሚገኘውን የሰማዓታት መታሰቢያ ሙዚየም ጎብኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በስፍራው የአበባ ጉንጉንም አኑረዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትር  ዐቢይ አሕመድ በትናነትናው እለት ለይፋዊ የስራ ጉብኝት አልጀሪያ መግባታቸው ይታወሳል።
407 viewsmenty (ßoss), 09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:57:27
387 viewsmenty (ßoss), 09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:57:27
385 viewsmenty (ßoss), 09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 12:57:27
380 viewsmenty (ßoss), 09:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 07:57:28
ሰውየው አልጄርስ ነው::

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤትዝናሽ ታያቸው ከልዑካን ቡድናቸው ጋር ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት በሰሜን አፍሪካዋ የአልጄርስ ከተማ ተገኝተዋል።
438 viewsmenty (ßoss), 04:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ