የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
82.92K
የሰርጥ መግለጫ
ይህ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው።
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
0
3 stars
1
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6
2024-03-14 09:35:16
ከፎቶ ማህደራችን።
#ትውስታ #የኢትዮጵያአየርመንገድ
15.4K views06:35
2024-03-13 11:30:19
የዛሬውን #የመስኮትምልከታ ያጋሩን shalom.shewamoltot ናቸው፤ እናመሰግናለን! እርስዎም ከእኛ ጋር ሲበሩ ያነሱትን ምስል በመልዕክት መቀበያ ሳጥን በኩል ይላኩልን መልሰን እናጋራዎታለን።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
13.2K views08:30
2024-03-12 23:36:57
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ‘የኢትዮጵያ ተቋማት የስኬት ሽልማት’ን ተቀዳጀ። ብሔራዊ አየር መንገዱ ሽልማቱን ከክቡር የኢፊዴሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እጅ ተቀብሏል። አየር መንገዳችን በአህጉር አቀፍ ደረጃ ላሳየው አመርቂ እድገት በተለይም በኮሮና ወረርሽኝ ጊዜ ላበረከተው ዓለም-አቀፍ አስተዋጽኦ ሽልማቱ ተበርክቶለታል። ሽልማቱን አቶ መስፍን ጣሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ ተቀብለዋል። ዋና ስራ አስፈጻሚው ሽልማቱ ‘የመላው የአየር መንገዱ ሰራተኛ የትጋት ውጤት' መሆኑን ተናግረዋል። #የኢትዮጵያአየርመንገድ
14.5K views20:36
2024-03-12 14:32:06
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰሞኑን በቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ከመንገደኞች አገልግሎት አሠጣጥ ጋር በተያያዘ በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ላይ ቅሬታዎች እየተነሱ መሆኑን ተገንዝቧል።
አየር መንገዱ ከክቡራን ደንበኞቹ ለሚቀርቡ ቅሬታዎች እና አስተያየቶች ከፍተኛ ትኩረት የሚሠጥ በመሆኑ ሂደቱን በጥሞና ሲከታተል ቆይቷል።
በመሆኑም እየተሰሙ ያሉ ቅሬታዎችን መርምሮ መፍትሄ ለመስጠት አየር መንገዱ በአዲስ አበባ ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ አገልግሎት ከሚሰጡ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ቅሬታዎችን የማጣራት ስራ እየሠራ መሆኑን ለማሣወቅ እንወዳለን።
ይህንንም ተከትሎ በማጣራቱ ሥራ ላይ በሚገኙ ውጤቶች ላይ በመመርኮዝ ተገቢው የማስተካከያ እርምጃ በፍጥነት እንዲወሠድ ይደረጋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁልጊዜም ጥረቱ ለውድ ደንበኞቹ ቀልጣፋ እና ምቹ አገልግሎት መስጠት ነው። አሁንም የክቡራን ደንበኞቹን ጥቆማ ተቀብሎ አስፈላጊውን ማስተካከያ በማድረግ ይህንኑ ጥረቱን አጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በአክብሮት እንገልጻለን።
16.0K views11:32
2024-03-11 19:55:06
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለረመዳን ፆም በሰላም አደረሳችሁ። ረመዳን ከሪም!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
15.5K views16:55
2024-03-11 09:06:44
በላቀ አገልግሎታችን እየተደሰቱ ከእኛ ጋር በምቾት ይብረሩ። #የኢትዮጵያአየርመንገድ
13.0K views06:06
2024-03-10 10:09:57
ከአፍሪካ ኩራት ጋር ከፍ ብለን እንብረር!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
14.0K views07:09
2024-03-09 10:45:05
የማይረሳ የበረራ ትዉስታ ከእርስዎ ጋር ለማድረግ ዝግጅታችንን ጨርሰናል። ብሩህ የእረፍት ቀናት ተመኘንልዎ!
#የኢትዮጵያአየርመንገድ
15.5K views07:45
2024-03-07 21:41:37
ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል የመንግስት ሀላፊዎች፣ ዲፕሎማቶችና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በደመቀ መልኩ ተከብሯል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይህን ቀን አስመልክቶ ወደ እንግሊዝ ለንደን በሴቶች ብቻ የሚደረግ በረራ ያደርጋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ዓለምአቀፍየሴቶችቀን
16.7K views18:41
2024-03-06 18:20:29
ዓመታዊው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ሊከበር እነሆ አንድ ቀን ቀርቶታል። የኢትዮጵያ አየር መንገድም ይህን ቀን በሴቶች ብቻ በሚደረግ በረራ ሲያከብረው ቆይቶ የዘንድሮውንም የሴቶች ቀን በተመሳሳይ መልኩ በድምቀት ሊያከብር ዝግጅቱን አጠናቅቋል።
#የኢትዮጵያአየርመንገድ #ዓለምአቀፍየሴቶችቀን
16.7K viewsedited 15:20