Get Mystery Box with random crypto!

ebstv worldwide📡☑️

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebstvworldwide — ebstv worldwide📡☑️ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebstvworldwide — ebstv worldwide📡☑️
የሰርጥ አድራሻ: @ebstvworldwide
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 40.22K
የሰርጥ መግለጫ

Welcome to EBS TV WORLDWIDE Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates. Don’t forget to share it with your friends.
@ebstvworldwidebot
@EbswhatsnewBot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-05-10 20:44:16

550 views17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:24:06

761 views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:23:11

702 views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 20:22:37

627 views17:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:25:19 #ቱርክ
የቱርክ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን የሱዳን ጦርነት እንዲቆም ሁለቱንም ተፋላሚ ኃይሎች ለማደራደር ሀገራቸው ዝግጁ መሆኗን ይፋ አደረጉ።

ኤርዶሀን ከሱዳን ጦር ኃይል አዛዥ ከጄኔራል አብደል ፈታ አል ቡርሃን ጋር ባደረጉት የስልክ ውይይት በሱዳን የቀጠለው ግጭት አሳሳቢ መሆኑን ነግሬአቸዋለሁ ብለዋል ::
ፕሬዝዳንት ኤርዶሃን በሱዳን የአስቸኳይ ሰብዓዊ ድጋፍ ለሚሹ ሰዎች ድጋፍ ለማቅረብ ከመንግስታቱ ድርጅት ጋር እየመከሩ መሆኑን ነው አር ቲ የዘገበው ።

*********
የቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶሀን ለቱርክ የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪ ማድረጋቸውን አስታወቁ።
ፕሬዝዳንቱ ለ700ሺ የመንግስት ሰራተኞች የሚከፈለውን ደሞዝ በ45 ከመቶ መጨመራቸው የተሰማው በአገሪቱ ከ 3 ቀናት በኃላ ከሚካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ቀደም ብሎ ነው።
ኤርዶሀን፣ “ከዚህ በኋላ የመንግስት ሰራተኞች በዋጋ ግሽበት ምክንያት የሚጐዱበት ጊዜ አይኖርም፤” ሲሉ ተደምጠዋል ከውሳኔው በኋላ፡፡
ዘገባው የአር ቲ ነው፡፡

#አሜሪካ
ግዙፉ የአሜሪካው ጐልድ ማን ባንክ መድልኦ አድርሶባቸዋል ለተባሉ ሴት ሰራተኞቹ የ 215 ሚሊዮን ዶላር የካሳ ክፍያ ለመፈፀም መስማማቱ ተሰማ።

የባንኩ 2 ሺ 8 መቶ የቀድሞ ሴት ሰራተኞቹ ባንኩ የሚከፍለው ደሞዝ ላይ አድሏዊ አሰራር ፈፅሞብናል ሲሉ በአውሮፓውያኑ 2010 የመሰረቱት ክስን ተከትሎ ነው ባንኩ የካሳ ክፍያውን ለመክፈል የተስማማው፡፡
የቀድሞ የባንኩ ሰራተኞች የክስ ሂደትን የተከታተሉት አሊሰን ጋምባ የተባሉት ጠበቃ ውሳኔው የሴቶችን የእኩልነት ጥያቄ የሚመልስ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብለዋል።
ዘገባው የአሶሼትድ ፕሬስ ነው፡፡
1.1K views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 19:25:02
#ዩክሬን
የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ፀሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የዩክሬን ጦርነት እንዲቆም በሩሲያ እና ዩክሬን መካከል የሰላም ውይይት ይደረጋል ብለው እንደማይጠብቁ አስታወቁ።

ዋና ፀሐፊው ጉቴሬዝ ዩክሬንም ሆነ ሩሲያ በወታደራዊ እርምጃዎች ብቻ ጥቅማቸውን ለማስከበር መወሰናቸው እና ለውይይት ዝግጁ ባለመሆናቸው ነው የድርድር ተስፋ እንደማይታያቸው ያስታወቁት፡፡

ጉቴሬዝ ለአስተያየታቸው ምክንያታቸውን ሲያቀርቡ ሩሲያ ከያዘቻቸው የዩክሬን ግዛቶች ለመልቀቅ አለመፈለጓና ዩክሬን ደግሞ በሞስኮ የተያዙባትን ግዛቶች በኃይል አስመልሳለሁ ማለቷ ድርድር የሚባል ነገር እንዳይታሰብ የሚያደርግ ነው ብለዋል።
አሜሪካ እና የአውሮፓ ሕብረት በበኩላቸው ቻይና የዩክሬን ጦርነት እንዲቆም ይረዳል ያለችውን የሰላም ሀሳብ ይዛ መምጣቷን ተቃወመውታል፡፡
ዘገባው የአር ቲ ነው፡፡
1.1K views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 20:24:33

2.6K views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 19:24:16 #ሩሲያ
የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዓለማችን እጅግ ወሳኝ የታሪክ ምዕራፍ ላይ ደርሳለች አሉ።

ፑቲን አክለውም ምዕራባዊያኑ በሩሲያ ላይ የከፈቱትን ጦርነት በድል አድራጊነት እንደሚወጡ ተናግረዋል ።
ፕሬዚዳንቱ ሩሲያ ናዚ ጀርመን ላይ ድል የተቀዳጀችበት የድል በዓል ላይ ባደረጉት ያለ ንግግር የጀርመን ናዚዎችን የተዋጋነውን ያህል ዛሬም የሩሲያን ነጻነት ለማስከበር ተገቢውን ተጋድሎ እናደርጋለን ብለዋል ።
ዘገባው የቢቢሲ ነው፡፡

#አሜሪካ
በአሜሪካ ባለፉት አምስት ወራት ውስጥ ብቻ በጦር መሳሪያዎች በተፈፀሙ የጅምላ ግድያዎች 14ሺ 6 መቶ ሰዎች መገደላቸው ተሰምቷል።

በተያዘው የአውሮፓውያኑ 2023 ያለፉት 5 ወራት ውስጥ በአሜሪካ 199 የጅምላ ግድያዎች ሲመዝገቡ 93 ህፃናትን ጨምሮ 14 ሺ 6 መቶ አሜሪካውያን በጅምላ ግድያዎቹ ህይወታቸውን ማጣታቸው ነው የተገለጸው፡፡
በቴክሳስ ግዛት አንድ ታጣቂ በፈፀመው ጥቃት በትንሹ 8 ሰዎች መገደላቸው ነው የተነገረው፡፡
ዘገባው የቲአር ቲ ወርልድ ነው፡፡

******************

ግዙፉ የማኅበራዊ ሚዲያው ፌስቡክ በወር አንዴ የትስስር ገፁን የሚጐበኙ ተጠቃሚዎቹ ቁጥር 3 ቢሊዮን መድረሱን አስታወቀ።

የፌስቡክ የማህበራዊ የትሰስር ተጠቃሚዎች በአብዛኛው እድሜቸው የገፋ መሆኑ ሲነገር ኩባንያው በተለይ ወጣት ተጠቃሚዎችን የትስስር ገፁ ደንበኛ ለማድረግ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ያሉ ቴክኖሎጂዎችን ለመጠቀም ማቀዱ ተነግሯል፡፡
በአሜሪካ እድሜያቸው ከ18 እስከ 34 ያሉ ወጣቶች ውስጥ 46 ከመቶ የቲክ ቶክ መተግበሪያ የሚጠቀሙ ሲሆን ፌስቡክን የሚጠቀሙት 28 ከመቶ ብቻ እንደሆኑ አንድ ጥናት ጠቁሟል።
ዘገባው የአሶሼትድ ፕሬስ ነው።

******************

የሰው ሰራሽ አስተውሎት ወይም አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ከአየር ንብረት ለውጥ በባሰ ሁኔታ በሰው ልጆች ላይ አደጋ ሊደቅን እንደሚችል አንድ ሳይንቲስት ተናገሩ፡፡

“የሰው ሰራሽ አስተውሎት የጡት አባት” በመባል የሚጠሩት ጆፍሬይ ሂንተን የሰዉ ሰራሽ ቴክኖሎጂ ከአየር ንብረት ለውጥ በከፋ ሁኔታ ለሰው ልጅ አደጋ ሊሆን እንደሚችል ነው የገለጹት፡፡
ሳይንቲስቱ ጂኦፍሬይ ሂንተን የሰዉ ሰራሽ አስተውሎት የሚያስከትላቸውን አደጋዎች በነጻነት ለመግለፅ ስል ከግዙፉ የአልፋቤት ኩባንያ በገዛ ፈቃዴ ሥራዬን ለቅቄአለሁ ብለዋል።
የአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ቴክኖሎጂ ውስጥ የሚካተቱት እንደ ቻት ጂፒቲ ያሉት መተግበሪያዎች የተማሩ ሰዎች የሚሰሯቸውን ሥራዎች ሊተኩ የሚችሉ መሆናቸው ይበልጥ ስጋት አንብሯል፡፡

የትዊተር ኩባንያ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢሎን መስክንና የዘርፉ ምሁራን እንደ ቻት ጂፒቲ ያሉ የሰው ሰራሽ ቴክኖሎጂዎች ላይ የ6 ወራት እገዳ እንዲጣል መጠየቃቸው ተነግሯል፡፡
ዘገባው የሲጂቲኤን ነው፡፡
2.8K views16:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-09 19:23:43
#ሱዳን
የሱዳኑ የጦር አዛዥ ጄኔራል አብደል ፈታ አልቡርሃን የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ተኩስ አቁመው ትጥቅ እንዲፈቱ ጠየቁ።

ብዙ መረጃ በማይወጣበት የጅዳ የሰላም ውይይት ላይ መካከል ለግብፅ የመገናኛ ብዙሃን አሉ እንደተባለው እውነተኛ የተኩስ አቁም ካልተደረገና የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ትጥቅ እስካልፈታ ድረስ የሚደረስ ሰላም የለም፡፡
በሳዑዲ አረቢያ እና በአሜሪካ ሸምጋይነት በጂዳ ከተማ በሱዳን ተፈላሚዎች መካከል እየተካሄደ ያለው የሰላም ውይይት ለ4ኛ ቀን እየተካሄደ ነው፡፡
ዘገባው የአል ቃኸራና ቢቢሲ ነው፡፡
2.4K views16:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 21:32:16

3.1K views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ