Get Mystery Box with random crypto!

ebstv worldwide📡☑️

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebstvworldwide — ebstv worldwide📡☑️ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebstvworldwide — ebstv worldwide📡☑️
የሰርጥ አድራሻ: @ebstvworldwide
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 40.25K
የሰርጥ መግለጫ

Welcome to EBS TV WORLDWIDE Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates. Don’t forget to share it with your friends.
@ebstvworldwidebot
@EbswhatsnewBot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-06 21:03:43

1.7K views18:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 19:25:23 #ሱዳን
በሱዳን ለ7 ሳምንታት በቀጠለው ውጊያ በትንሹ 3 ነጥብ 4 ቢሊዮን ዶላር ውድመት መድረሱ ተነገረ ።

የሱዳን የቀድሞው የገንዘብ ሚኒስትር ኢብራሂም ኤልባዳዊ ከቢቢሲ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ነው የኢኮኖሚ ኪሳራውን የገለጹት፡፡
የቀድሞው ሚኒስትር ኢብራሂም ኤልባዳዊ በሱዳን ግጭት የአገሪቱ ኢኮኖሚ ድቀት ውስጥ ገብቷል የሸቀጦች የአቅርቦት ሰንሰለትም ተጐድቷል ብለዋል።
ሚኒስትሩ በሱዳን የቀጠለው ግጭት እልባት የማያገኝ ከሆነ ወደ ለየለት የእርስ በርስ ጦርነት ሊቀየር ይችላል ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡
ዘገባው የቢቢሲ ነው፡፡

#ሊቢያ
የሊቢያው የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሙአመር ጋዳፊ ልጅ በቁጥጥር ስር በዋሉበት ሊባኖስ በሚገኝ አንድ ማረሚያ ቤት ውስጥ የረሃብ አድማ መምታታቸው ተነገረ፡፡

የሙአመር ጋዳፊ ልጅ ሀኒባል ጋዳፊ በሊባኖስ ማረሚያ ቤት የረሃብ አድማ የመቱት ያለ ፍርድ ለ 8 አመታት በእስር ላይ መቆየታቸውን በመቃወም ነው ሲሉ ጠበቃቸው ተናግረዋል፡፡
ሃኒባል ጋዳፊ ከሶሪያ በሊባኖስ ታጣቂዎች ታግተው ከተወሰዱ በኋላ በሊባኖስ ማረሚያ ቤት ለ8 አመታት በእስር ላይ መቆየታቸውን ቢቢሲ ዘግቧል ።
ጠበቃቸው ፓል ሮማኖስ ሃኒባል ጋዳፊ ያለ አንዳች ፍትህ ለ8 አመታት በማረሚያ ቤቱ መቆየታቸው ተገቢ አይደለም ብለዋል።

#አሜሪካ
አሜሪካ፣ እስራኤል እና ሳዑዲ አረቢያ የሰላም ስምምነት እንዲፈራረሙ ግፊት እንድምታደርግ አስታወቀች ።

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን አሜሪካ እስራኤል እና ሳኡዲ አረቢያ በተለምዶ የአብርሃም ስምምነት የሚባለውን የሰላም ስምምነት እንዲፈራረሙ በትጋት እየሰራች ነው ብለዋል።
ብሊንከን በዚህ ሳምንት በሳዑዲ አረቢያ በሚያደርጉት ጉብኝት ቴላቪቭ እና ሪያድ በአስቸኳይ የሰላም ስምምነቱን እንዲፈራረሙ ያግባባሉ ተብሏል።
በሌላ በኩል የእስራኤል መንግስት በእስራኤል በኃይል በተያዘው የዌስት ባንክ ግዛት እያካሄደ ያለው የቤት ፈረሳ አሜሪካንን እንደሚያሳስብ ብሊንከን መናገራቸውን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል ።

#ኢራን
ኢራን ከ 7 አመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሳዑዲ አረቢያ የሚገኘው ኤምባሲዋን ልትከፍት መሆኑን የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ነው፡፡

በቻይና አሸማጋይነት ከዛሬ 4 ወራት በፊት ኢራን እና ሳዑዲ አረቢያ የሰላም ስምምነት መፈራረማቸው ይታወሳል።
በኢራን የሚገኘው የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ በኢራናዊያን ተቃዋሚዎች በአውሮፓውያኑ 2016 ጥቃት ከደረሰበት በኋላ ሪያድ ከቴህራን ጋር የነበራትን ግንኙነት ማቋረጧ ይታወሳል።
ዘገባው የአሶሺየትድ ፕሬስ ነው ።
2.2K views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 19:25:02
#ዩክሬን
ዩክሬን ሩሲያ በፈፀመችው ጥቃት የኬሮሶን ግድብን አውድማዋለች ስትል ከሰሰች፡፡

የዩክሬን የመከላከያ ሚኒስቴር ሩሲያ ባካሄደችው ጥቃት በኬርሶን ግዛት ያለው የካኮቫ ግድብ መውደሙንና በግድቡ ዙሪያ ያሉ 16 ሺ ነዋሪዎች ከአካባቢው ለቀው እንዲወጡ እየተደረገ ነው ሲል ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
ይሁን እንጂ የሩሲያ መንግስት በኬርሶን ያለውን ግዙፉ የካኮቫ ግድብ የዩክሬን ኃይሎች ናቸው ያወደሙብት አፈንድተውታል ሲል መወንጀሉን ኤፒ ዘግቧል።
2.0K views16:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 21:49:48

2.8K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 19:49:44 #እስራኤል
የመንግስታቱ ድርጅት ባለፉት 6 ወራት በእስራኤል የፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ እርምጃ 112 ፍልስጤማውያን መገደላቸውን አስታወቀ።
የተመድ የእርዳታ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት (ኦቻ) ባወጣው መረጃ ከሞቱት ፍልስጤማውያን በተጨማሪ 4ሺ 209 የሚሆኑ ለጉዳት ተዳርገዋል ብሏል፡፡
በእስራኤል ጥቃት የተገደሉት አብዛኞቹ ፍልስጤማውያን በምስራቅ ኢየሩሳሌም እና እስራኤል በኃይል በያዘችው የዌስት ባንክ የሚኖሩ እንደነበር ቲ አር ቲ ዘግቧል ።
የእስራኤል የፀጥታ ሃይሎች በዌስት ባንክ እና በምስራቅ ኢየሩሳሌም 575 የፍልስጤም መኖሪያ ቤቶችን እንዳፈረሱ ተመድ ማስታወቁን ነው ዘገባው አክሎ ያስረዳው፡፡
#ሳዑዲ አረቢያ
ሳዑዲ አረቢያ በመጪው ሐምሌ ወር ዕለታዊ የነዳጅ ዘይት ምርት መጠኗን በ 1 ሚሊዮን በርሜል እንደምትቀንስ ይፋ ማድረጓን ተከትሎ በዓለም አቀፍ ደረጃ የነዳጅ ዘይት ዋጋ ጭማሬ ማሳየቱ ተገለፀ።
የሳዑዲ ዕቅድ በእስያ ሀገራት የነዳጅ ዘይት ዋጋ በ 2 ነጥብ 4 ከመቶ ጭማሪ ማሳየቱ ነው የተዘገበው።
ከነዳጅ አምራች እና ላኪ አገራት ድርጅት (ኦፔክ) ጋር የሚሰሩት ኦፔክ ፕላስ የተባሉት ነዳጅ ላኪ ሀገራት ሚኒስትሮች የነዳጅ ዘይት ምርታቸውን ለመቀነስ መስማማታቸው ነው የተነገረው
የዩክሬን-ሩሲያ ጦርነት የነዳጅ ዋጋ እንዲዋዥቅ በማድረግ የነዳጅ አምራች እና ላኪ ሀገራትን መጉዳቱን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ዘገባው የቢቢሲ ነው፡፡

#ቻይና
የቻይናው የመከላከያ ሚኒስትር ሊ ሻንፍፉ የቻይና እና የአሜሪካ ጦርነት ዓለም አይታው የማታውቀው የከፋ ቀውስ ሊያስከትል ይችላል ሲሉ አስጠነቀቁ።
የመከላከያ ሚኒስትሩ በሲንጋፖር በተካሄደ የሀገራት የፀጥታ ጉባኤ ላይ ነው ይህንን የተናገሩት፡ ፡ አክለውም ጥቂት ሀገራት በእስያ ወታደራዊ ፍጥጫን ለማባባስ እየሰሩ ነው ብለዋል፡፡
ሚኒስትሩ ኃያላኑ አሜሪካ እና ቻይና ልዩነቶቻቸውን በውይይት ሊፈቱ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።
ይሁንና በአሜሪካ ማዕቀብ የተጣለባቸው የቻይናው የመከላከያ ሚኒስትር ሊ ሻንግፉ ከአሜሪካው የመከላከያ ሚኒስትር ኦስቲን ሎይድ የቀረበላቸውን የእንወያይ ጥያቄ ውድቅ ማድረጋቸውን ቢቢሲ ዘግቧል ።
2.9K viewsedited  16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 19:49:42
#ሱዳን
በሱዳን ተባብሶ የቀጠለውን ጦርነት ተከትሎ በጤና ተቋማት የመብራት ኃይል በመቋረጡ የጤና ባለሙያዎች የሞባይል ስልካቸውን መብራት በመጠቀም እያዋለዱ መሆኑ ተሰማ፡፡
በሱዳን ካርቱም ባለ አንድ የጤና ተቋም የሚሰሩት ዶ/ር ሆዋይዳ አህመድ ለቢቢሲ እንደተናገሩት በሚሰሩበት ሆስፒታል የመብራት አገልግሎት ባለመኖሩ የደረሱ እናቶችን በቀዶ ጥገና የሚያዋልዱት በተንቀሳቃሽ ስልካቸው የባትሪ ብርሃን ታግዘው ነው፡፡
ዶ/ር ሆዋይዳ እንዳሉት በሱዳን ውጊያው ተባብሶ በመቀጠሉ ሳቢያ በካርቱም ያሉ ሆስፒታሎች እጅግ የከፋ ችግር ውስጥ ገብተዋል።
የመንግስታቱ ድርጅት በሱዳን 219ሺ ነፍሰ ጡር እናቶች አደጋ ሊያጋጥማቸው ይችላል ሲል ከወራት በፊት ማስጠንቀቁ በዘገባው ተመላክቷል፡፡
2.4K views16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 14:28:35

2.5K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 14:28:25

2.5K views11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-05 14:23:35

2.3K views11:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-04 18:45:31

3.0K views15:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ