Get Mystery Box with random crypto!

ebstv worldwide📡☑️

የቴሌግራም ቻናል አርማ ebstvworldwide — ebstv worldwide📡☑️ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ebstvworldwide — ebstv worldwide📡☑️
የሰርጥ አድራሻ: @ebstvworldwide
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 40.25K
የሰርጥ መግለጫ

Welcome to EBS TV WORLDWIDE Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates. Don’t forget to share it with your friends.
@ebstvworldwidebot
@EbswhatsnewBot

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-26 21:33:00

1.0K views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 21:30:21

1.1K views18:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 21:29:20

858 views18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 19:06:31 #አፍጋኒስታን
አፍጋኒስታንን እያስተዳደረ ያለዉ ታሊባን የዛሬ 3 አመት በካቡል የደረሰውን የቦንብ ፍንዳታ ያቀነባበረውን የአሸባሪውን የአይ ኤስ ኤስ መሪ መግደሉ ተሰምቷል ።
የአሜሪካ ባለስልጣናት እንደሚሉት በታሊባን የተገደለው የአሸባሪው የአይ ኤስ ኤስ መሪው ሳኑላህ ጋፋሪ በአውሮፓውያኑ 2021 በካቡል መዲና የደረሰውን እና 170 ንፁሃን ዜጐች እና 13 የአሜሪካ ወታደሮች የሞቱበትን የቦንብ ፍንዳታ ያቀነባበረ ነው ።
አሜሪካ የአይ ኤስ ኤስ መሪ ሳኑላህ ጋፋሪን አድራሻ ለጠቆመ 10 ሚሊየን ዶላር ወሮታ እከፍላለሁ ስትል ከዚህ ቀደም መጠየቋ ይታወሳል፡፡
ዘገባው የቢቢሲ ነው ።
#ደቡብ አፍሪካ
የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ሲሪል ራማፎሳ ሀገራቸው ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት " አይ ሲሲ" ልትወጣ መሆኑን አስታወቁ፡፡
ፕሬዚንዳንቱ ይሄን ያሉት ከፊንላንዱ ፕሬዚዳንት ሳዑሊ ሻይናሞ ኒሲቶ ጋር በኘሪቶሪያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ነው፡፡
ፕሬዚዳንት ራማፎሳ የገዢው የ "ኤኤንሲ" ፓርቲ ደቡብ አፍሪካ ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ጠቅልላ እንድትወጣ ውሳኔ አሳልፏል ብለዋል።
ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በደቡብ አፍሪካ አዘጋጅነት በሚካሄደው የብሪክስ አገራት ጉባኤ ላይ በሚታደሙት የሩሲያው መሪ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ላይ የእስር ማዘዣ ማውጣቱን ተከትሎ ደቡብ አፍሪካ ከፍርድ ቤቱ ለመውጣት ወስናለች ሲሉ ራማፎሳ ይፋ አድርገዋል፡፡
ዘገባው የሳባክ ቴሌቪዥን ነው፡፡
#ቻይና
ቻይና ከአሜሪካ በ4 አመት ቀደም ብላ በአውሮፓውያኑ 2030 በጨረቃ ላይ አዲስ የጠፈር ጣቢያ ልታቋቁም ማቀዷ ተሰማ፡፡
ቻይና ከ7 አመታት በኋላ በጨረቃ ላይ የራሷን የጠፈር ጣቢያ የማቋቋም ትልሟ ከተሳካ አሜሪካንን ቀድማ የመጀመሪያዋ ሀገር እንደምትሆን ነው የተዘገበው ።
ዘገባው የሜል ኦን ላይን ነው ።
1.6K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 19:06:29
#ሱዳን
የመንግስታቱ ድርጅት በሱዳን በቀጠለው ግጭት ሳቢያ ከአገሪቱ በ መቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ አስጠነቀቀ፡፡
የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ቃለ አቀባይ ኦልጋ ሳራዶ ይሄን የተናገሩት ከሱዳን በትንሹ 20ሺ ዜጐች ወደ ቻድ መሰደዳቸውን እና ሌሎች በርካቶች ወደ ግብፅ እየተሰደዱ መሆኑን ለጋዜጠኞች ሲያብራሩ ነው፡፡
ኃላፊዋ አክለውም ግጭቱን ተከትሎ ወደ ጐረቤት ሀገራት ከተሰደዱት ሱዳናዊያን ባሻገር ሌሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በአገር ውስጥ ተፈናቅለዋል ብለዋል ።
ዘገባው የአሶሺትድ ፕሬስ ነው።
*********

በእስር ላይ የነበሩት የቀድሞው የሱዳን ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር እና ሌሎች በርካታ ባለስልጣናት ከማረሚያ ቤት መውጣታቸው ተነገረ።
በመፈንቅለ መንግስት ከስልጣን የወረዱት የሱዳን የቀድሞ የሱዳን መሪ አልበሽርና ሌሎች 30 ባለስልጣናት "ኮበር" ከተባለ ማረሚያ ቤት መውጣታቸውን አንድ ባለስልጣንን ዋቢ አድርጎ ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
1.5K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-26 11:46:25

2.3K views08:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 21:13:14

2.9K views18:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 19:20:13 #ሕንድ
ሕንድ በህዝብ ብዛት ቻይናን በልጣ የዓለም ቁጥር ቀዳሚ ሀገር ደረጃን መያዟ ተነገረ፡፡

ሕንድ ከ1.4 ቢሊዮን ሕዝብ በላይ ያላትንና ላለፉት 73 አመታት በሕዝብ ብዛት ቀዳሚ የነበረችውን ቻይናን መብለጧን ነው የመንግስታቱ ድርጅት ያስታወቀው ።
በሕንድ በየእለቱ 86 ሺ ሕጻናት እንደሚወለዱ ሲነገር በቻይና ደግሞ 49 ሺ 4 መቶ ሕፃናት ምድሪቱን እንደሚቀላቀሉ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
ሕንድ ቻይናን በአውሮፓውያኑ 2027 በህዝብ ብዛት ትበልጣለች በሚል ከተቀመጠው ትንበያ 4 አመት አስቀድሞ ነው መሪነቱን የተቆናጣጠችው፡፡
ዘገባው የዘ ጋርዲያን ነው፡፡

#አሜሪካ
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን በአውሮፓውያኑ 2024 ለሚካሄደው የአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ ይፋ አደረጉ፡፡

ፕሬዚዳንቱ በለቀቁት የቪዲዮ መልዕክታቸው ከ1 አመት በኋላ በሚደረገው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ እንደሚወዳደሩ ገልፀው ምርጫው በፈተና ውስጥ ያለውን የአሜሪካን ዴሞክራሲ በተግባር መታደግ ዋና ግቡ መሆኑን ገልጸው “የጀመርኩትን ጠንካራ ሥራ ከዳር ለማድረስ ምረጡኝ፤” ብለዋል።
ዘገባው የቢቢሲ ነው፡፡

#ቡርኪናፋሶ
በቡርኪናፋሶ ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት 60 ንፁሃን ሰዎች መገደላቸውን የሀገሪቱ መንግስት አስታውቋል።

የቡርኪናፋሶ አቃቤ ህግ ባወጣው መግለጫ በያቴንጋ ግዛት ባርጋ በተባለ አካባቢ ታጣቂዎች በፈፀሙት ጥቃት 60 ሰዎች ሲገደሉ በርካቶች መጎዳታቸውን ነው የገለጸው።
የሀገሪቱ መንግስት ጥቃቱን ፈፅመዋል ብሎ በሚያስባቸው የፀጥታ ኃይሎች ላይ ምርመራ እንዲደረግ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ኤ ኤፍ ፒ ዘግቧል።
3.1K views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 19:19:54
#ሱዳን
የሱዳን ተፋላሚ ኃይላት ለ3ኛ ጊዜ ለ72 ሰአታት የሚዘልቅ የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማታቸው ተሰማ።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከሳዑዲ አረቢያ ባለስልጣናት ጋር ባደረጉት ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ነው ጦርነት ውስጥ ያሉት አካላት ለ72 የሚዘልቅ ስምምነት እንዲደርሱ ማስቻላቸው ነው የተነገረው ።
ብሊንከን የሱዳን ጦር እና የሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ሀይላት አዲስ ለተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈጻሚነት አበክረው እንዲሰሩ መጠየቃቸውን አልጀዚራ ዘግቧል።

******
የምስራቅ አፍሪካ አገራት በሱዳን በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጐቻቸውን ከሀገሪቱ ማውጣት ጀመሩ፡፡
ሶማሊያ ፣ ጅቡቲ እና ኬንያ በሱዳን ያሉ ዲፕሎማቶቻቸውን እና ዜጐቻቸውን እያወጡ መሆኑ ሲነገር የሶማሊያ 27 ዜጐች ከሱዳን ወጥተው ኢትዮጵያን ከሱዳን በሚያዋስነው መተማ መግባታቸው ነው የተዘገበው፡፡
ኬንያ በበኩሏ ከሱዳን የነበሩ 29 ዜጐቿን አስወጥታ ኢትዮጵያ እንዲገቡ ማድረግ መቻሏን አናዶሉ ዘግቧል።

******
አሜሪካ ከሱዳን የሚወጡ ዜጎቿን ለመደገፍ የጦር መርከቦቿን በቀይ ባሕር ላይ ማስፈር መጀመሯን አስታወቀች።
ይህንን የተናገሩት ለኤቢሲ ኒውስ ቃለ መጠይቅ የሰጡት የአሜሪካ የብሔራዊ ደህንነት ቃለ አቀባይ ጆን ኪርቢ ናቸው፡፡
እንደ ቃል አቀባዩ ገለጻ ሀገራቸው ዜጎቿን ከሱዳን ለማስወጣት የጦር መርከቦችን በፖርት ሱዳን አቅራቢያ እያስጠጋች ነው፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለም በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አማካይነት በተዘጋጀ የበረራ ፕሮግራም በርካታ አሜሪካውያን ከካርቱም እየወጡ መሆኑንም ነው ጆን ኪርቢ አክለው የገለጹት፡፡
2.7K views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-25 12:52:12

3.0K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ