Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 25.10K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 20

2022-12-05 21:37:38 የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ህግ ት/ቤት የሙስና ወንጀልን ለመከላከል፣ ስለመመርመርና ከወንጀሉ የሚገኝ ንብረት ስለመውረስ በተመለከተ ከ23-24/03/ 2015 ዓ.ም ስልጠና ተሰጠ፡፡
==============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፦ ህዳር 26/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) ስልጠናው ለ4ኛ እና 5ኛ አመት ህግ ተማሪዎች እና ከዩኒቨርሲቲው ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት እንዲሁም ከፋይናንስና ጠቅላላ አገልግሎት ለተውጣጡ ሰራተኞች የተዘጋጀ ስልጠና እንደሆነ ተገንዝበናል።

በዩኒቨርሲቲያችን እየገነነ የመጣውን የሙስና ወንጀልን ለመከላከልና በሙስናና ተያያዥ ምክንያቶች የሚመጣን ሀብት እንዴት መውረስ እንደሚቻል ተማሪዎች ክፍል ውስጥ ከሚሰጣቸው ትምህርት በተጨማሪ ከስልጠናው የሚያገኙት ዕውቀት፣ ክህሎትና ግንዛቤን ለመጨመር እንደሚያስችል የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ህግ ት/ቤት ዲን አማረ ስጦታው በስልጠናን ባስጀመሩበት ወቅት ገልፀዋል ፡፡

የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ ቢኒያም ሽፈራው ስልጠና ሲሰጡ እንደገለጹት ሙስና የሀገርን ኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ያለው አሉታዊ ተጽዕኖ ውስብስብ ስለሆነ ይህንን ለመከላከልና የሀገራችንን ጥቅሞች ለማስከበር ከግለሰብ ጀምሮ ሁሉም መረባረብ እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ስልጠናውን በማጠቃለያ ንግግር የዘጉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ይህይስ አረጉ (ዶ/ር) እንደገለጹት ሙስና በባህሪው ውስብስብ በመሆኑ ስርቆት የሚፈጸመው ደግሞ በጥናት፣ በቀመር፣ በስሌትና በባለሙያ እየታገዘ ስለሆነ የተፈጸመን ወንጀል መርምሮ ለህግ ለማቅረብ ያስቸግራል ስለዚህ እናንተን ከሚፈታተናችሁ ስጋዊና ደመነፍሳዊ ፍላጎት በተጨማሪ የሙስና ወንጀል ባህሪ እረቂቅነት ጭምር እንደሆነ ገልፀዋል። ተማሪዎች ወደ ስራ አለም ውስጥ ስትገቡም ይሄ ችግር ስለሚፈታተናችሁ ከወዲሁ ራሳችሁን ነፃ ለማድረግና ሰለእውነት ኑራችሁ ህዝባችሁንና ሀገራችሁን በንፅህና ለማገልገል ዝግጁ እንድታደርጉ በማለት አሳስበዋል።
1.6K views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-05 21:37:27
1.6K views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 14:11:36 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ያዘጋጀው የውይይት ጉባዔ ተካሄደ
=============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፦ ህዳር 23/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) "ሙስናን መታገል በተግባር " በሚል መሪ ቃል የተደረገው ይህ ጉባዔ ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች፣ መምህራንና ሰራተኞች እና ለባለድርሻ አካላት የተዘጋጀ ሲሆን የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶር. ታፈረ መላኩ የውይይት መድረኩን ዓላማና አስፈላጊነት በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል። በገለፃቸውም ስለ ሙስናና ስነ ምግባር ጉድለቶች መወያየት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ባይቻልም የሙስናና የስነ ምግባር ብልሹነት ተግባር ከአሳሳቢነት አልፎ ህጋዊነት የተሰጠው እየመሰለ በመምጣቱ ችግሩ እየከፋ በመምጣቱ ለመፍትሔ የሚሆኑ ሀሳቦችና ተሞክሮዎችን ለመለዋወጥ መወያየቱ መልካም ነው ብለዋል።

የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮማንደር ይበልጣል ደምሰው የዩኒቨርሲቲውን አጠቃላይ የአሰራርና የስነ ምግባር ክፍተቶችን በተመለከተ የመወያዬ መነሻ ሀሳብ ሰነድ አቅርበዋል።

ቀመነሻ ሰነዳቸውም ከዚህ ቀደም በአሰራርና ስነ ምግባር ዙሪያ በዩኒቨርሲቲያችን ውስጥ የተከሰቱ ችግሮችን በተመለከተ ሰፋ ያለ ገለፃና ማብራሪያ አቅርበዋል።

በቀረበው የውይይት መነሻ ሀሳብ መሰረትም ከተሳታፊዎቹ የተለያዩ ጥያቄዎችና የመፍትሔ አስተያየቶች ተሰጥተው የዕለቱ ጉባዔ ፍፃሜ ሆኗል።
1.1K viewsedited  11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 14:11:23
1.1K views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 13:28:56 የ5ኛ ዙር ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ ማህበረሰብ ልማት ሰልጣኞች ተመረቁ
=======
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፦ ህዳር 24/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) በሰላም ሚኒስቴር እና በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ትብብር ላለፉት 33 ቀናት ሲስለጥኑ የቆዩ ብሔራዊ የበጎ ፈቃድ ማህበረሰብ ልማት ሰልጣኞች የሰላም ሚኒስቴር ምንስትር ዲኤታ እና የዕለቱ የክብር እንገዳ #ክቡር_ዶክተር_ስዩም_መስፍንን ጨምሮ የሚኒስትሩ አማካሪዎች እና በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር #ታፈረ_መላኩ ፣ የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ #አቶ_ስለሺ_ተመስገን እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው ልዩ ልዩ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት የምረቃ ስነ ስርዓቱ ተፈፅሟል።
1.3K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 13:28:39
1.3K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 13:28:37
1.2K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-03 13:28:32
1.3K views10:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 11:21:24 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የሚሰሩ እናቶች የህፃናት ማቆያ ስራ መጀመሩ እንዳስደሰታቸው ገለፁ
===========
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ:- ህዳር 23/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የስራ ክፍሎች የሚሰሩ ሴት መምህራንና የአስተዳደር ሰራተኞች ስራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ ለማከናወን ያመች ዘንድ ዩኒቨርሲቲው በ2013 ዓ.ም የህፃናት ማቆያ በማዘጋጀት ከ6 ወር አስከ 3 ዓመት ዕድሜ የሚሆናቸው ህፃናት ተቀብሎ አገልግሎቱን እየሰጠ ይገኛል፡፡

በማዕከሉ ላይ ተግኝተው ሀሳባቸውን የሰጡት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ወጣቶች እና ኤች.አይ.ቪ ኤድስ መከላከል ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላም መክብብ እንደገለጹት ሴት ሰራተኞች በስራ ገበታቸው ተረጋግተው ስራቸውን እንዲሰሩ ለማድረግና በስራቸውም ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል፣ ልጆቻቸውንም ማጥባትና መጎብኘት በሚፈልጉበት ሰዓት በቅርበት እንዲጎበኙ ለማድረግ በማሰብ 4 የሞግዚት እና 3 የጽዳት ባለሙያዎችን በድምሩ 7 ሰዎችን በመቅጠር 25 ለሚሆኑ ህፃናት አገልግሎቱን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል ፡፡
በማዕከሉ ከሴት ሰራተኞች በተጨማሪ ሚስቶቻቸው በስራ ምክንያት ሩቅ ቦታ ለሚኖሩባቸው አባቶችም ልጆቻቸውን በማቆያ ማዕከሉ በማስገባት ተጠቃሚ በመሆን ላይ ናቸው ብለዋል። ዩኒቨርሲቲያችን ከKG እስከ 12ኛ ክፍል ድረስ ለማስተማርያ የሚሆን የማህበረስብ ት/ቤት በመገንባት ላይ ይገኛል። በቅርብም ወራትም ግንባታው ተጠናቆ ወደ ስራ ሲገባ ከዚህ በበለጠ የህፃናትንና የባለሙያዎችን ቁጥር በመጨመር አገልግሎቱ እንደሚሰጥ አክለው ገልፀዋል። በመጨረሻም በዚህ ማዕከል ውስጥ ህፃናትን ልክ እንደወላጅ ሆነው እየተንከባከቡ ንፅህናቸውንና ደህንነታቸውን ለሚጠብቁ ባለሙያዎች ምስጋና ይድረሳቸው በማለት ሀሳባቸውን አጠናቀዋል፡፡

በህፃናት ማቆያ ማዕከሉ ውስጥ በሞግዚት ባለሙያነት ስታገለግል ያገኘናት እንይሽ ሽቴ እንዳለችው የዚህ ማዕከል መከፈቱ የስራ እድል ፈጥሮልናል፤ ህይወታችንን እየመራንበት እንገኛለን ፤ በስራችንም በጣም ደስተኛ ነን ፤ ከዚህ በተጨማሪ ከህፃናት ጋር መዋል ልዩ ስሜትና ደስታን ይፈጥራል፤ እኛ ባንወልዳቸውም እንኳ እንደወላጅ በመሆን ለህፃናት ልዩ እንክብካቤ በማድረግ ለወላጆቻቸው እናስረክባለን። ከዚህ በተጨማሪ ዩኒቨርሲቲ ለባለሙያዎች የንጽህና መጠበቂያ የሚሆኑ ግብዓቶችን እንዲሟሉ ጠይቃለች፡፡

በሌላ በኩል በህፃናት ማቆያ ልጆቻቸውን ሲያስገቡ ያገኘናቸው ወ/ሮ ይታይሽ መኩሪያውና የዝና ነጋሽ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ለሰራተኞቹ ልጆች ይህን የህፃናት ማቆያ በማዘጋጀት ልጆቻችን በማቆያው እንዲውሉ በማድረጉ ከልብ እንደሚያመሰግኑና ከተለያየ ወጭም እንደታደጋቸው ስራቸውንም በጥሩ ስነ ልቦና እንዲሰሩ እንዳገዛቸው ገልፀዋል። "ልጆቻቸውንም ማየት ስንፈልግ በቅርበት እንድንከታተል አድርጎናል ካሉ በኋላ በመጨረሻም በማዕከሉ ለሚሰሩ ባለሙያዎች ልጆቻችንን በጥሩ ሁኔታ እንደራሳቸው ልጆች እየተንከባከቡ በመያዛቸው ከልብ እናመሰግናለን፤ ይህ የህፃናት ማቆያ ከዚህ የበለጠ እንዲያድግና አገልግሎቱን በስፋት እንዲሰጥ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
2.3K views08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-02 11:21:10
2.2K views08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ