Get Mystery Box with random crypto!

የጥያቄዎቻችሁ መልስ

የቴሌግራም ቻናል አርማ apostolicsuccession — የጥያቄዎቻችሁ መልስ
የቴሌግራም ቻናል አርማ apostolicsuccession — የጥያቄዎቻችሁ መልስ
የሰርጥ አድራሻ: @apostolicsuccession
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.61K
የሰርጥ መግለጫ

የዚህ ኦርቶዶክሳዊ ገጽ ዋና ዓላማ የወጣቱን ጥያቄ መመለስ ነው። ወጣቶች ማንኛውም በሕይወታቸው የገጠማቸውንም ይሁን መንፈሳዊ ጥያቄ በሚረዱት መልክ መልስ ይሰጥበታል
YouTube
https://www.youtube.com/channel/UCPLJimNlqTFBnlbsh_vccgg
ለጥያቄዎችና ለአስተያየቶች
@AbuNak
@Rhripsime

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-12-12 23:08:46 ...ክፍል ፪

                          ምዕራፍ ፬

በዚህ ምዕራፍ ሊቁ ቀደሞ በምዕራፍ ሦሥት ላይ የተረጎመውን የዮሐንስ ወንጌል ፩፡፩{1፡1}ን ቃል ከመለኮት ባህርይ አውጥተን መተርጎም እንደሌለብን ያስረዳል የእርሱን {የክርስቶስን} መለኮታዊ ማንነት እና ሰዋዊ ማንነት በሚገባ ለይተን ካላወቅን¹ ለቃየል የተነገረው ቃል {ዘፍጥረት ፬፡፯{4፡7}ሊቁ ይህን ቃል ከመናፍቃን ጋር አገናኝቶ ይተረጉመዋል ክፍል ፩ን ይመልከቱ} ለእኛም አነደሚገባ ይናገራል።
በመቀጠልም ክርስቶስ የሰውን ሥጋ አልነሣም የሚለውን የማኒን አስተምህሮ ይቃወማል ክርስቲያኖችም በእርሱ {በማኒ} አስተምህሮ ቢያምኑ "የቤተክርስቲያን ልጆች መሆን እንዳልጀመሩ"² አበክሮ ይናገራል።

አስከትሎም በማቴዎስ ወንጌል {፲፮፡፲፭{16፡15}} ላይ ሐተታ {ትርጓሜ} ይሰጣል።
በሐተታው ያነሳቸውን ነጥቦች በሁለት ማየት ይቻላል

፩. በዚህ የወንጌል ክፍል ላይ ጌታችን ኢየሱስ "የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?" "ብሎ ሐዋርያትን ሲጠይቃቸው ሐዋርያትም አንዳንዶቹ ኤርምያስ አንዳንዶቹ ኤልያስ አንዳንዶቹ ከነብያት አንዱ ነህ ይሉሀል ብለው መለሱለት እርሱ ግን ለአንዱም መልስ እውቅና አልሰጠም ትክክል ነው አላለም “እርሱም፦ እናንተስ እኔን ማን እንደ ሆንሁ ትላላችሁ? አላቸው።” ባላቸው ጊዜግን ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ ምላሽ ሰጠ ምክንያቱም እርሱን የሚመለከት እና የእርሱን ማንነት የሚገልጽ ነበርና ለእርሱ ምላሽ ብቻ እውቅና መስጠቱን ከአምላክነቱ አንፃር ማለትም አምላክ መሆኑን የሚገልጽ ነው ብሎ ተርጉሞታል {መጽሐፉ ለአርዮሳውያንም ምላሽ እንደሚሰጥ ልብ ይሏል} እንዲያውም አርዮሳውያንን እንዲህ ብሎ ይጠይቃቸዋል "አርዮሳውያን ሆይ ዮሐንስ እና ጴጥሮስ ያላመኑ ናቸው ብላችሁ ታስባላችሁን?"³ በማለት ይጠይቃቸዋል ምክንያቱም ይህ ቃል የክርስቶስን እውነተኛ አምላክነት ወልደ እግዚአብሔር መሆኑ የተገለጸበት ስለሆነ አርዮሳውያን ደግሞ ከዚህ ቃል አፈንግጠው በራሳቸው ሀሳብ ፍልስፍና ወድቀው ከቤተክርስቲያን አካልነት ተነጥለዋልና!
ቃሉን ሲተረጉምም ከዚህ አንፃር ይተረጉመዋል።

፪. የጴጥሮስ ምላሽ "በመጀመሪያ ያለህ" "ፍጡር የሆንኽ" የሚል ሳይሆን "የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ"  የሚል ነበር ይህ ቃል የውሸተኛዋ ቤተክርስቲያን የአርዮሳውያን ኅብረት መሠረት አይደለም ነገርግን ክርሰቶስ በደሙ የመሠረታት የኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን መሠረቷ ነው በዚህም አርዮሳውያን የእውነተኛዋ ቤተክርስቲያን ልጆች አለመሆናቸውን አሳወቁን ምክንያቱም በዚህ ቃል መሠረትነት አልተማሩምና ነው
ሊቁ በዚህ አውድ ማሳየት የፈለገው ጉዳይ ይህ ቃል መሠረታችን መሆኑን ነው {በዚያውም ለአርዮሳውያን መሠረት አለመሆኑንም ማሠየት አንዱ አውዱ ነው እንዲህ ከሆነ ደግሞ አርዮሳውያን የእውነተኛዋ ቤተክርስቲያን አካላት አለመሆናቸውን ያርጋግጣልና!}ይህ ቃል እንዴት መሠረታችን እንደሆነ ሲያብራራም እንዲህ ይላል "መሠረት ተብሎ ተጠራ ነገርግን የሁላችንም {የቤተክርስቲያን} መሠረት ነው ምክንያቱም እርሱ ራሱን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም መጠበቅ ያውቃልና ነው።
ክርስቶስም ከእርሱ ጋር ተስማማ አብም ገለጠለት።"⁴

                          ምዕራፍ ፭
"መሠረተ ቤተክርስቲያን የተባለው እምነቱን እንጂ ሥጋውን አይደለም የጴጥሮስን ሥጋ አልነበረም ነገርግን እምነቱን የገሀነም ደጆች አይችሉትም {ሊቆጣጠሩት አይችሉም} ነገርግን የእርሱ ምስክርነት ገሀነምን ይቆጣጠራል።
ቤተክርስቲያንም ልክ እንደ መልካም መርከብ በብዙ ማዕበል {ምንፍቅና} ትመታለች የቤተክርስቲያን መሠረት ሁሉንም ምንፍቅናዎች ተቃውሞ ያሸንፋልና ይህ ምስክርነት በምንፍቅና አይሸበርም!"⁵

እንዲህ በማለት ቤተክርስቲያን የተመሠረተችበትን የቅዱስ ጴጥሮስ ምስክርነት ያጸናል።
እንዲሁም በዚህ የመጽሐፉ ክፍል ወልደ እግዚአብሔርም ወልደ ማርያምም እርሱ እንደሆነ፤ምስጢረ ሥጋዌ ሁለቱን አካላት {ሥጋ እና መለኮትን}አንድ እንዳደረገ፤ሁለቱ ማንነቶች አንድ {የእርሱ ገንዘቦች}፤እንዲሁም በዚህ ሁለት ማንነቶች ሳይሆን አንድ ክርስቶስ ተብሎ እንደሚጠራ ያብራራል።

በዚህም ይህ የመጽሐፉን ክፍል ከቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ ተአምር ቃለ ውግዘት ጋር አዋህደን ማየት እንችላለን ሊቁ እንዲህ ይላል "ዓለም ሳይፈጠር የተወለደው የእግዚአብሔር ልጅ ሌላ ነው፤ከማርያም የተወለደው ሌላ የሚል ዓለም ሳይፈጠር የነበረው እርሱ ራሱ ቀዳማዊ ደኃራዊውም ያው አንዱ ብቻ እንደሆነ እንደተጻፈ በኋላ ዘመንም ከማርያም ሥጋን የነሣው እርሱ ራሱ እንደሆነ የማያምን የተወገዘ ይሁን"⁶

አክሎም የአንዱን ሥግው ቃል {The one incarnated word} ባህርይ ሲያብራራም የታመመው ያልታመመውም ያው እርሱ ነው፤የሞተውም ያልሞተውም ያው እርሱ ነው {መለኮት በባህርይው ሞት አይስማማውምና ለሥግው ቃል ሞት ሲነግርለት በሥጋው ነው የሚባልለት}፤የተቀበረውም ያልተቀበረውም ያው እርሱ ነው፤ከሞት የተነሣው ያልተነሣውም {ለመለኮት መነሣት መውጣት መውረድ የለበትምና!} ያው እርሱ ነው አንዱን ክርስቶስ ሳንነጣጥል መረዳት እንዳለብን እና እነዚህ ሁሉ ግብራት የአንዱ ሥግው ቃል ግብራት እንደሆኑ ያስረዳል።

በመቀጠልም አንዱ በመዝሙር {፳፩፡፩{21፡1}} ላይ ያለውን ቃል ማለትም “አምላኬ፥ አምላኬ፥ ለምን ተውኸኝ? እኔን ከማዳንና ከጩኸቴ ቃል ሩቅ ነህ።”
የሚለውን ቃል በመስቀል ላይ ሳለ ከምን አንፃር እንደተናገረ ያብራራል እንዲህም ይላል "በሥጋ ብቸኛ {Forsake} ይሆናል በመለኮቱ ግን ሊጎዳም ሆነ ብቸኛ ሊሆን አልቻለም።"⁶

የመለኮት እና የሥጋ ተዋሕዶ ያለ መጠፋፋት፣ያለ መለወጥ፣ያለ መቀላቀል እና ያለ መለየት የተደረገ የተደረገ ከመሆኑ ጋር አገናዝቦ ማየት ይቻላል።
"ኢየሱስ ክርሰቶስ አንድና ተመሳሳይ ነው እንላለን ቢሆንም የባህርያቱን {የሥጋና የመለኮትን} ልዩነት እርስ በእርስ አለመቀላቀል {አለመምታታት} እውቅና እንሰጣለን።"⁷
እንዲል ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ቅዱስ አምብሮስም ይህን ቅርጽ እና መንገድ ለማብራራት ተጠቅሞቀታል።
ይህንም ክፍል እንዲህ በማለት ያጠቃልላል "ሥጋው በባህርይው ታሟል እንዲሁም የመለኮት ባህርይ በሕማሙ ባህርይው አልተለወጠም ትንሣኤያችን በእውነት ነው የክርስቶስ ሕማምም በእውነት ይሰበካል።"⁸

                             ምዕራፍ ፮
በዚህ ምዕራፍ ሊቁ የክርስቶስ መገለጥ ምትሐት ነው ያሉ {በእውነት ሰው አልሆነም እውነተኛ ሥጋን ከቅድስት ድንግል ማርያም አልነሣም የሚሉ} ቫለንቲኑስን እና ማኒን እንዲህ በማለት ይቃወማቸዋል "ብዙዎች እንደሚሉት ክርስቶስ በምትሐት አልታመመም ምክንያቱም በባህር ላይ በምትሐት አልተራመደምና!"⁹
ኢየሱስ ክርስቶስን ወልደ እግዚአብሔር ወልደ ማርያም ብል መከፋፈል መለያየት እንደማይገባ ንስጥሮሳዊ የሆነውን ትምህርት በድጋሚ ይቃወማል ያስተምራልም ማመን የሚገባን በአንዱ በሥግው ቃል በኢየሱስ ክርሰቶስ እንጂ በሁለት ኢየሱስ ክርስቶስ እንዳይደለ በአጽንኦት ያስረዳል።
944 views20:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-10 21:24:05 ላይቭ ነን

https://vm.tiktok.com/ZMFgy613d/
423 views18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-09 19:13:50
ባህርዳር ያላችሁ ወንድም እኅቶቻችን ተሳተፉ
1.0K views16:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-08 20:08:40
አዳማ ያላችሁ ወንድም እኅቶች ከቻላችሁ ተሳተፉ
1.1K views17:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 23:06:39 #ማጣቀሻዎች

፩. The sacrament of thr incarnation of our lord chapter 7፡63
፪. St. Ambrose theological and dogmatic works page 217
፫. አቡሊናርዮስ (አቡርዮስ) የሎዶቂያ ጳጳስ የነበረ ሰው ሲሆን የቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ጓደኛ የነበረ እና ስለ ነቂያው የእምነት ድንጋጌ አጥብቆ የተጋደለ ሰውም ነበር ቅዱስ ጄሮምም ከእርሱ ተምሮ እንደነበር ይነገራል {F.r tadros y.malaty apanaromic view of patristics in the six centuries page 154} ቢሆንም የክርስቶስ ፍፁም የሰውን ነፍስ አልነሳም የሚል እንግዳን ትምህርት በቤተክርስቲያን ስላመጣ በሁለተኛው ዓለም አቀፍ ጉባኤ {Universal council} በቁስጥንጥንያ ትምህርቶቹም እርሱም ተወግዟል።
፬. The sacrament of thr incarnation
of our lord chapter 7፡63
፭. የአበው ጽሑፎች በዙውን ጊዜ ለሕዝብ የሚሰጡ ትምህርቶች {Oration,lecture,sermon} ናቸው በኋላ ነው ወደ ጽሑፍ የሚገለበጡት
፮. Life of st. Ambrose 18
፯. ይህ ምንፍቅና አርዮስ ዘመም {Neo arianism} ልንለው እንችላለን የክርስቶስን ከአብ ጋር መተካከል ቢያምኑም ነገርግን ለእርሱ ይገዛል ብለው ያምናሉ {F.r tadros y.malaty apanaromic view of patristics in the six centuries page 201}
፰. The sacrament of thr incarnation of our lord chapter 1፡3
፱. ብናጥስ{ኖቫትያን} የሮም ቤተክርስቲያን ቄስ የነበረ ሲሆን ከሃይማኖት አደጠው ለተመለሱ የሚደረገውን የንስሀ ጥምቀት {Re baptism} የተቃወመ ሲሆን በወቅቱ በነበሩት በቅዱስ ቆጵርያኖስ በቅዱስ ዲዮናስዮስ ዘእስክንድርያ በቅዱስ ዲዮናስዮስ ሮም ምላሽ የተሰጠው ቢሆንም ባለመመለሱ በሮም በተደረገ አከባቢያዊ ጉባኤ {Local council} ትምህርቱም እርሱም ተወግዘዋል።{የታኅሣሥ ፲፱{19} ስንክሳር}
ዶናተስም የዚህ ምንፍቅና አቀንቃኝ ነበር
፲.The sacrament of thr incarnation of our lord chapter 2፡13

... ይቀጥላል

@orthodoxdigitallibrary
905 views20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-07 23:06:39 የመጽሐፍ ርዕሰ = በእንተ ሚስጢረ ሥጋዌሁ ለእግዚእነ {The sacrament of the incarnation of our lord}
ጸሐፊ= ቅዱስ አምብሮስ ዘሚላን
የተጻፈበት ጊዜ = ፫፻፹፩{፫፹፪}{381{382}} ዓ/ም
ይዘት = ነገረ ክርስቶስ

#መግቢያ

፩.፩ የመጽሐፉ ስያሜ
የመጽሐፉ ጸሐፊ ቅዱስ አምብሮስ "Mystery of our lord's incarnation"{De incarnationis dominicae sacramento} ብሎ ሲጠራው [፩]
የቅዱሱን ታሪክ የጻፈው ጳውሊኖስ እና ቄሳዴሮስ "The incarnation of our lord" ሲሉት ሌሎች ደግሞ "Against apollinarsts" {መድፍነ አቡሊናርዮሳውያን} ይሉታል [፪] እንዲህም ያሉት መጽሐፉ ለአቡሊናርዮስን [፫] ምንፍቅና ምላሽ ስለሰጠ ይሆናል።

፩.፪ ምክንያተ ጽሑፍ
መጽሐፉ ከOn the faith {De fide} On the Holyspirit {De Spiritusancto} በኋላ ሦሥተኛ የዶግማ ሥራው ነው {ስለ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ሃይማኖት ያብራራበት} መጽሐፍ ነው።

"ነገርግን ምንላርግ? በየቀኑ አዳዲስ ጥያቄዎች ይመጣሉ... ለተቃውሞ ገደብ {ልክ} ከሌለው ለምላሽስ እንዴት ገደብ {ልክ} ሊኖረው ይችላል?" [፬] በማለት ሊቁ ይህን መጽሐፍ እንዲያዘጋጅ ያደረገው አምስት ጥራዝ ባለው በOn the faith{ De fide}መጽሐፍ ምላሽ የሰጣቸው የመድኅን ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስን ፍፁም አምላክነት ለሚክዱት ለአርዮስ ተከታዮች የማያባራ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት እንዲሁም ምእመናነ ክርስቶስን በእምነት ለማፅናት ነው።

አንድም ታሪኩን ያዘጋጀው ጳውሊኖስ ስለ መጾሐፉ መዘጋጀት ምክንያት የንጉሥ ግራትያን ዘቦች {እልፍኝ ከልካይ} የሆኑ ሁለት አርዮሳውያን ስለ ጌታችን ሥጋዌ ጥያቅ ጠየቁ በበነገታውም በቤተክርስቲያን ተገኝተው ቅዱሱ ምላሽ እንዲሰጣቸው እና በትምህርቱ ለመሳተፍ ቃል ገብተው ስለ ነበር ለእነርሱ ምላሽ ለመስጠት መጽሐፉ እንደተጻፈ ይናገራል።
ነገርግን ሊቁ ቃሉን አክብሮ በሚስጢረ ሥጋዌ ላይ ትምህርት ሰጥቶ በመጽሐፍ መልክ ቢጻፍም [፭] አርዮሳውያኑ ግን ቃላቸውን ሽረው በትምህርቱም ሆነ የጠየቁትን ጥያቄ ምላሽ ለመስማት አልተገኙም[፮] ነበር በዘመኑ አርዮሳውያን በእነ ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ ላይ እንዳደረጉት ሁሉ በእርሱም ላይ መከራዎችን አድርሰውበታል።
የተለያዩ የስም ማጥፋት ወሬዎችንም በእርሱ ላይ ይነዙ ነበር።

፩.፫ አጠቃላይ የመጽሐፉ ባህርይ
መጽሐፉ የሚያጠነጥነው በነገረ ክርሰቶስ ለተነሱ ምንፍቅናዎች ምላሽ መስጠት ላይ ነው።
መልስ ከተሰጣቸው የምንፍቅና አይነቶች ውስጥ አርዮሳዊነት  እና አቡሊናርዮሳዊነት ሰፊውን ቦታ ሲወስዱ መንፈቀ{ተረፈ} አርዮሳዊነት[፯] አውጣኪያዊነት እና ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል።

በቅዱሱ ዘመን አርዮሳዊነት እና መንፈቀ{ተረፈ} አርዮሳዊነት ያየለበት እና ቤተክርስቲያንን የፈተነበት ስለነበር አብዛኞቹ የቅዱሱ የዶግማ ጽሑፎቹ ለእነርሱ ምላሽ የሚሰጡ ናቸው።
በመጽሐፉ ውስጥ የተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እግረ መንገዳቸውን አብረው ተተርጉመዋል።
የቅዱሱ የአመላለስ ዘዴም በመጀመሪያ የመናፍቃኑን ሀሳብ ካነሳ በኋላ ምላሹን ከመጽሐፍ ቅዱስ በማምጣት በአመክንዮ አስደግፎ ማስቀመጥ ነው።

ሊቁ የግሪክ ቋንቋ የተማረ ላቲናዊ ቢሆንም በዚህ መጽሐፍ በግሪክ ቃላት ያሉ የነገረ መለኮት መግለጫ ቃላትን {Theological terminologies} ያብራራል ይተነትናል።

፪.የመጽሐፉ የውስጥ ክፍል በጥቂቱ ሲተነተን
መጽሐፉ አስር ምዕራፍ ያለው ሲሆን የእያንዳንዱን ምዕራፍ ሀሳብ በስሱ ለማየት እንሞክራለን።

                      ምዕራፍ ፩
ይህን የመጽሐፉን ክፍል መግቢያ {introduction} ማለት ይቻላል።
በዚህ ክፍል ቅዱሱ የአቤል እና የቃየንን መሥዋዕት መሠዋት የሚናገረውን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ኅብረ አምሳላዊ ትርጓሜን ይተረጉማል።
የቃየንንም መሥዋዕት ከመናፍቃን ጋር ያገናኘዋል የቃየን መሥዋዕት እግዚአብሔርን አላስደሰተውምና ነው ይህንንም ሊቁ እንዲህ ያብራራዋል "ቃየን መሥዋዕቱ እግዚአብሔርን እንዳላስደሰተ አወቀ እግዚአብሔርም “መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች — ዘፍጥረት 4፥7 አለው ግን የቱ ጋር ነው ወንጀሉ? ጥፋቱ የቱ ነው? በመሥዋዕቱ አይደለም ነገርግን የመሥዋዕቱ መባእ የቀረበበት የእዕምሮ ሁናቴ ነው።" ይላል [፰]

ማለትም እግዚአብሔር መሥዋዕቱን ያልተቀበለለት መሥዋዕቱን ንቆት አልነበረም ነገርግን መሥዋዕቱ የቀረበበትን መንገድ ነው ማለቱ ነው።
የቃየን መሥዋዕት በእግዚአብሔር ፊት ሞገሥን እንዳላገኘ እንዳላስደሰተ ከቤተክርስቲያን ኅብረት የተለዩ የመናፍቃንም ሃይማኖት እግዚአብሔርን አያስደስተውምና።
የመናፍቃን አገልግሎት እምነት በቤተክርስቲያን ውስጥ አይደለምና ነው።

                         ምዕራፍ ፪
በዚህ ክፍል እግዚአብሔር ለቃየን የተናገረው የግሳጼ ቃል ማለትም {“መልካም ብታደርግ ፊትህ የሚበራ አይደለምን? መልካም ባታደርግ ግን ኃጢአት በደጅ ታደባለች
  — ዘፍጥረት 4፥7} አስተምህሮአቸውን ከተለያዩ የፍልስፍና ትውፊቶች ለቃረሙት በግብር ቃየንን ለመሰሉት ለአውናምዮሳውያን {መንፈቀ{ተረፈ}አርዮሳውያን} ለሰባልዮሳውያን፣ለጸረ-መንፈስቅዱስ{Pneumatomachi {ለመቅደንዮሳውያን}}፣የክርስቶስን አካል ቤተክርስቲያንን ለከፈሉ ለብናጥስ{ኖቫትያን} እና ዶናተስ [፱] እንዲሁም ለአቡሊናርዮሳውያን እና መሰል መናፍቃን እንደሚገባ ይናገራል።

መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ፫፡፬{3፡4}ን ዋቢ በማድረግም  እንዲህ ይላል "ስለዚህ ማንም ከዘላለማዊ ንጉሥ መኖሪያ ከእናት ቤተክርስቲያን እቅፍ እንዳይለየን እንጠንቀቅ ልክ በመኃልየ መሓልይ እንዳለችው ነፍስ"[፲]

                       ምዕራፍ ፫
በዚህ ክፍል ላይ የዮሐንስ ወንጌል ፩፡፩{1፡1}ን የሚያብራራበት {የሚተረጉምበት} ክፍል ነው።
ወንጌላዊው እንደ አሳ አጥማጅነት ሳይሆን እንደ ሰው አጥማጅነት {ሐዋርያት አሳ ማጥመድ ትተው ሰው ያጠምዱ{ነፍሳትን ወደ ክርስቶስ ያቀርቡ ዘንድ}በጌታ እንደተሾሙ ልብ ይላል} በመንፈስቅዱስ ተቃኝቶ መናገሩን ይህን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል መናፍቃን የልብ ጆሯቸውን ዘግተው እንደሚሰሙት እና ተጨማሪ ጉዳዮችን ይዘረዝራል።
878 views20:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-12-04 09:16:49

520 views06:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-29 20:17:09

678 views17:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-24 14:15:37
940 views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-11-24 14:15:37
968 views11:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ