2023-03-20 22:54:12
“መኖሪያችን የሆነው ምድራዊ ድንኳን ቢፈርስም፣ በሰው እጅ ያልተሠራ ነገር ግን ከእግዚአብሔር የሆነ ዘላለማዊ ቤት በሰማይ እንዳለን እናውቃለን።”
2ኛ ቆሮንቶስ 5፥1
የህያው ተስፋ የታምራት አገልግሎት መስራችና መሪ የሆኑት የሐዋርያ ዳንኤል ጌታቸው እና
የተልዕኮ ለትውልድ አለም አቀፍ አገልግሎት መስራችና መሪ የሆኑት የሐዋርያ ዘላለም ጌታቸው (ዶ/ር) ወላጅ እናት የሆኑት ወ/ሮ #_የሺወርቅ_በቀለ መጋቢት 11, 2015 ዓ.ም ወደ አገለገሉትና ወደሚወዱት ጌታ ሄደዋል።
ወ/ሮ የሺዬ በቤተክርስቲያን በጸሎትና በተለያዩ ክፍሎች ሲያገለግሉ የቆዩና ሁለት ሐዋርያ (ሐዋርያ ዳንኤል ጌታቸው እና ሐዋርያ ዶ/ር ዘላለም ጌታቸው) ሁለት ሴት መጋቢዎችን (መጋቢ ዜና ጌታቸው እና መጋቢ ሐና ጌታቸው) አንድ ሴት አገልጋይ (አሚ ጌታቸው) በጥቅሉ አምስት አገልጋዮችን ያፈሩ ታላቅ ሴት ነበሩ።
ለቤተሰቦቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው በሙሉ የመጽናናት ሁሉ አምላክ እግዚአብሔር መጽናናትን ይስጣቸው እያልን የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን ለመግለጽ እንወዳለን።
ማውንት ጽዮን ዘሲቲ ኦፍ ዘሊቪንግ ጋድ ኢንተርናሽናል ቸርች
ቮይስ ኦፍ ጋድ ቲቪ ቻናል
የወ/ሮ የሺወርቅ በቀለ የአስከሬን ሽኝት እና የቀብር ስነ-ስርዓት በተመለከተ
...................................................................
መጋቢት 12/2015 ዓ.ም ከረፋዱ 5:00 ሰዓት - በህያው ተስፉ የታምራት አገልግሎት ቤ/ክርስቲያን የአስከሬን ሽኝት ሲሆን
ከቀኑ 8:00 ሰዓት ላይ ዊንጌት ጴጥሮስ ወጳውሎስ የወንጌላዊያን መካነ መቃብር ስፍራ የቀብር ስነ-ስርዓት የሚካሄድ መሆኑን እንገልጻለን።
7 views19:54