Get Mystery Box with random crypto!

Amba Digital - አምባ ዲጂታል

የቴሌግራም ቻናል አርማ ambadigmedia — Amba Digital - አምባ ዲጂታል A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ambadigmedia — Amba Digital - አምባ ዲጂታል
የሰርጥ አድራሻ: @ambadigmedia
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.42K
የሰርጥ መግለጫ

አምባ ዲጂታል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መረጃ፣ ዘገባዎችና አተያዮችን የሚያቀርብ ዲጂታል የሚዲያ መድረክ ነው፡፡

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-08-25 15:02:10
ሕወሓት ጥቃት በማቆም ወደ ምክክር እንዲመጣ ሲል መንግሥት አሳሰበ

አምባ ዲጂታል፤ ሐሙስ ነሐሴ 19፣ 2014 ― ሕወሓት እየፈፀመ የሚገኘውን ጥቃት በማቆም ወደ ምክክር እንዲመጣ ሲል መንግሥት ያሳሰበው በዛሬው እለት ማለትም ነሐሴ 19፣ 2014 ባወጣው መግለጫ ነው።

በመንግሥት ኮሚኒኬሽን በኩል በወጣው መግለጫ፤ ሕወሓት ይህን ጥሪ የማይቀበል ከሆነ መንግሥት ሀገራዊ ሉአላዊነትንና የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ አስፈላጊውን ርምጃ እወስዳለሁ ብሏል።

ለአምስት ወራት ያህል ጋብ ብሎ የቆየው የፌዴራል መንግስት እና ሕወሓት ጦርነት ትላንት ዳግም መጀመሩ ይታወቃል።

ጦርነቱን ማን ጀመረው በሚለው ላይ ሁለቱም አካላት አንዳቸው ሌላኛውን እየወነጀሉ ይገኛል።

የፌዴራል መንግስት እና ሕወሓት ጦርነት ዳግም ያገረሸው ለድርድር ይቀመጣሉ ተብሎ በተጠበቀበት ሰዐት ነው።

https://ambadigital.net/2022/13845/
1.1K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 12:30:33
የአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ጦርነት ማገርሸቱን ተከትሎ ትላንት ረቡዕ ነሐሴ 18፣ 2014 የተናገሩት
971 views09:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 11:53:40
ትላንት ረቡዕ ነሐሴ 18፣ 2014 የሕወሓት ኃይሎች መቐለ ከተማ ከሚገኘው የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን በ12 ተሽከርካሪ የተጫነ ነዳጅ ዘርፈዋል መባሉን ተከትሎ የተናገሩት
986 views08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 11:07:05

967 views08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 09:41:43 የፌዴራል መንግሥት እና የሕወሓት ባለሥልጣናት በምሥጢር በአካል በመገናኘት ተነጋግረው እንደነበር ተገለጸ

አምባ ዲጂታል፤ ሐሙስ ነሐሴ 19፣ 2014 ― የፌዴራል መንግሥት እና የሕወሓት ባለሥልጣናት በምሥጢር በአካል ተገናኝተው እንደነበር የገለጹት ትግራይ ክልልን የሚያስተዳድረው ሕወሓት ሊቀመንበር ዶክተር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ናቸው፡፡ ሊቀመንበሩ ይህን የገለጹት ለተለያዩ አካላት በጻፉት ደብዳቤ ነው፡፡

ዶክተር ደብረጽዮን ማክሰኞ ነሐሴ 17፣ 2014 ለ12 አካላት በጻፉት ደብዳቤ ለሁለት ጊዜያት በተደረገው የምሥጢር ግንኙነት ከፌዴራል መንግሥት ጋር ተኩስ ለማቆም እና በትግራይ የተቋረጡ መሠረታዊ አገልግሎቶችን ለመቀጠል መግባባት ላይ ደርሰው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ የዶክተር ደብረጽዮን ደብዳቤ የፌዴራል መንግሥት እና የሚመሩት ሕወሓት ባለሥልጣናት የት እና መቼ እንደተገናኙ የጠቀሰው ነገር የለም፡፡

የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ከባለፈው ዓመት ጥቅምት ወር አንስቶ ጦርነት ውስጥ መግባታቸው ይታወቃል፡፡ ሁለቱ አካላት ያለፉትን አምስት ወራት ጦርነቱን ጋብ አድርገው ለመደራደር ዝግጁ እንደሆኑ ሲገልጹ ቆይተዋል፡፡ በዚህ ሒደት ውስጥ ባለሥልጣኖቻቸው በተለያዩ አገራት መገናኘታቸውን የሚያመለክቱ ይፋዊ ያልሆኑ መረጃዎች ቢወጡም የፌዴራል መንግሥቱ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በኩል አስተባብሏል፡፡

ሁለቱ አካላት ጦርነቱን ጋብ ባደረጉበት በተለይ ባለፉት ሳምንታት የሰላም ንግግሩ ፍሬ እያሳየ መሆኑን ኦሊሴጉን ኦባሳንጆን በአሸማጋይነት የመደበው የአፍሪካ ኅብረት ገልጾ ነበር፡፡ ሌላኛዋ አደራዳሪ አሜሪካም በባለስልጣናት በኩል ድርድሩ ከአስር ቀናት በፊት ከተካሄደው የኬንያ ምርጫ በኋላ ይደረጋል የሚል ተስፋ እንዳላት ገልጻ ነበር፡፡

ይህ በእንዲህ ባለበት ትላንት ረቡዕ ነሐሴ 18፣ 2014 ንጋት ላይ ዳግም ጦርነቱ ተጀምሯል፡፡ ጦርነቱን ማን ጀመረው በሚለው ላይ መረጃውን ቀድሞ ያወጣው ሕወሓት፤ የፌዴራል መንግሥቱ ኃይሎች ጥቃት ከፍተውብኛል ቢልም፤ እኩለ ቀን አካባቢ መግለጫ ያወጣው መንግሥት ሕወሓት ለተኩስ ቀዳሚ ነው ሲል ወንጅሏል፡፡

ከጦርነቱ ዳግም መጀመር በኋላ ዋንኛው አደራዳሪ የአፍሪካ ህብረትን ጨምሮ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ የአሜሪካ እና ብሪታንያ ባለሥልጣናት ውጊያው ቆሞ ንግግር እንዲጀመር ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳ ፋኪ ማህመት ትላንት ምሽት ባወጡት መግለጫ፤ በፌደራል መንግስት እና ህወሓት መካከል ዳግም ውጊያ መቀስቀሱ በጥልቅ እንዳሳሰባቸው ገልጸዋል። የቀድሞው የናይጄሪያ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ሁለቱን ኃይሎች እንዲያሸማግሉ የሾሙት ሊቀመንበሩ፤ ተኩስ ቆሞ ሁለቱ ወገኖች ሰላማዊ መፍትሔ ለማፈላለግ ንግግር እንዲጀምሩ ጥሪ አስተላልፈዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝም እንዲሁ በኢትዮጵያ ዳግም ውጊያ በመጀመሩ መደናገጣቸውን እና ማዘናቸውን ገልጸዋል። ውጊያ ቆሞ ሁለቱ አካላት የሰላም ንግግር እንዲጀምሩ ጥሪ ያቀረቡት ጉቴሬዝ፤ ‹‹ኢትዮጵያውያን በበቂ ተሰቃይተዋል›› ብለዋል፡፡

በጦርነቱ ማገርሸት በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል መግከጫ ያወጣችው አሜሪካ ደግሞ እንደ አዲስ ያገረሸው ግጭት እና በአዲስ አበባ እና በመቐለ መካከል የሚታየው የቃላት መወራወር፤ በአገሪቱ አካታች የፖለቲካ ሂደት ለመመስረት የሚደረገውን ጥረት እንደሚያዘገይ አስታውቃለች፡፡ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሚኒስትሩ አንቶንዮ ብሊንክን የሁለቱ ተፈላሚ ወገኖች ወደ ውጊያ መመለስ፤ የኢትዮጵያን ዜጎች ለመጠነ ሰፊ ስቃይ፣ ለሰብዓዊ መብቶች ጥሰት፣ እና ለተጨማሪ የኢኮኖሚ ፈተና እንደሚዳርግ አስጠንቅቀዋል።
1.0K views06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 17:10:57

1.1K views14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 14:33:00

1.1K views11:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 13:02:36 መንግሥት ሕወሓት ጥቃት ሰንዝሮ የተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሷል አለ

አምባ ዲጂታል፤ ረቡዕ ነሐሴ 18፣ 2014 ― የፌዴራሉ መንግሥት ሕወሓት ጥቃት ሰንዝሮ የተኩስ ማቆሙን በይፋ አፍርሶታል ያለው ዛሬ በኮሚኒኬሽን አገልግሎት በኩል ባወጣው መግለጫ ነው፡፡ እንደ መንግሥት ኮሚኒኬሽን መግለጫ ከሆነ ሕወሃት ሰሞኑን ሲፈጽም የነበረውን ‹‹ትንኮሳ ገፍቶበት›› ዛሬ ንጋት ላይ በምሥራቅ ግንባር በቢሶበር፣ በዞብል እና በተኩለሽ አቅጣጫዎች ከሌሊቱ 11 ሰአት ጀምሮ ጥቃት ፈጽሟል።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ይህን መግለጫ ከማውጣቱ አስቀድሞ ዛሬ ረቡዕ ነሐሴ 18 ማለዳ ላይ ሕወሓት የ‹‹ትግራይ ሠራዊት ወታደራዊ ኮማንድ›› ባለው አካል በኩል በሰጠው መግለጫ፤ ዛሬ ንጋት 11 ሰዓት ላይ መጠነ ሰፊ ጥቃት በፌዴራል መንግሥት ተከፍቶብኛል ብሏል። የ‹‹ትግራይ ሠራዊት ወታደራዊ ኮማንድ›› ጥቃቱ ተከፍቷል ያለው ‹‹በጩቤ በር፣ ጃኖራ፣ ጉባጋላ እና በያሎው ኣቅጣጫ ወደ አላማጣ፣ ባላና ብሶበር›› ነው፡፡

የሕወሓት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ በተመሳሳይ በትዊተር ገጻቸው ‹‹ከሳምንት ትንኮሳ በኋላ የአማራ ልዩ ኃይል፣ የአማራ ሚሊሻ እና የወሎ ፋኖ እንዲሁም [የመከላከያ] 6ኛ ኮማንድ ጥቃት ከፍተዋል›› ብለዋል።

ሆኖም የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ባወጣው መግለጫ ሕወሓት ‹‹የፈጸመው ጥቃትም ሆነ እሱን ተከትሎ ያወጣው መግለጫ አስቀድሞ ለትንኮሳው ሲዘጋጅ እንደነበር ግልጽ ማሳያ ነው›› ብሎታል፡፡

የሕወሓት ኃይሎች በአንጻሩ መንግስት ጀምሮታል ያሉትን ጥቃት ዋንኛ አላማው ‹‹ከምዕራብ ትግራይና ምዕራብ ጎንደር ወደ ኣድያቦ፣ ኣስገደ እና ፀለምቲ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ሃቅ ነው›› ብለዋል፡፡ አክለውም ጠላት ያሉት የፌዴራል ኃይል ‹‹የጀመረውን ጥቃት ካላቆመ በአስተማማኝ ደረጃ ጥቃቱን በመመከትና በመስበር ወደ ፀረ ማጥቃት በመሸጋገር የተወረረውን ሉኣላዊ የትግራይ መሬትና የተፈናቀለው ህዝባችን ወደ ቀድሞው ይዞታው ለመመለስ የሚያስችል ሙሉ ዝግጅት›› አለን ነው ያሉት፡፡

በተመሳሳይ መንግሥት ባወጣው መግለጫ፤ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ጥያቄ መፍትሄ ማግኘት የሚችለው ‹‹በሰላማዊ መንገድ ብቻ መሆኑን በመገንዘብ ዛሬም ነገም የሰላም አማራጭ የመጀመሪያ መፍትሔ እንደሆነ›› መንግሥት ፅኑ እምነት እንዳለው የገለጸ ቢሆንም፤ ሕወሓት ‹‹በትንኮሳው ከገፋበት›› መንግስት ‹‹ሀገር የማዳን ሕጋዊ፣ ታሪካዊና ሞራላዊ ግዴታ ስላለበት እንዲሁም የሽብር ቡድኑ ወደደም ጠላም ወደ ሰላም አማራጭ እንዲመጣ ለማድረግ አስፈላጊውን እርምጃ ሁሉ›› እወስዳለሁ ብሏል፡፡ ይህን ለማስፈፀም ደግሞ መንግስትና መላው የፀጥታ ኃይላችን ከነሙሉ ብቃትና ቁመናቸው በተጠንቀቅ ላይ ናቸው ሲል አክሏል፡፡

ሁለት ዓመት ሊደፍን ጥቂት የቀረው የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ጦርነት ባለፉት ወራት ሁለቱም አካላት በወሰዱት የተኩስ አቁም አቋም ጋብ ብሎ ቆይቶ ስለ ድርድር ሲነገር ቆይቷል፡፡ ለድርድሩ ሁለቱም ተደራዳሪዎችን መሠየማቸውን ገልጸው የነበረ ቢሆንም፤ ባለፉት ቀናት ግን ወሬው ወደ ጦርነት ተቀይሯል፡፡
1.0K views10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ