Get Mystery Box with random crypto!

Amba Digital - አምባ ዲጂታል

የቴሌግራም ቻናል አርማ ambadigmedia — Amba Digital - አምባ ዲጂታል A
የቴሌግራም ቻናል አርማ ambadigmedia — Amba Digital - አምባ ዲጂታል
የሰርጥ አድራሻ: @ambadigmedia
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.42K
የሰርጥ መግለጫ

አምባ ዲጂታል በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ መረጃ፣ ዘገባዎችና አተያዮችን የሚያቀርብ ዲጂታል የሚዲያ መድረክ ነው፡፡

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-27 13:20:43 የአማራ ክልል የጫት ተጠቃሚነትን ለመቀነስ የቀረጥ ጭማሪ አደረገ

አምባ ዲጂታል፤ ቅዳሜ ነሐሴ 21፣ 2014 ― የአማራ ክልላዊ መንግሥት በክልሉ የጫት ተጠቃሚነትን ለመቀነስ የቀረጥ ጭማሪ አድርጓል፡፡ የክልሉ መንግሥት አዲስ ባደረገው የቀረጥ ጭማሪ መሠረት ነጋዴዎች በአንድ ኪሎ ግራም ጫት 30 ብር እንዲከፍሉ ይደረጋል፡፡

ከነሐሴ 12፣ 2014 ጀምሮ መተግበር የጀመረው አዲሱ ታክስ፤ በክልሉ እየጨመረ የመጣውን ይህን አነቃቂ ቅጠል ተጠቃሚነት ለመቀነስ የተደረገ መሆኑን መመሪያው አመልክቷል፡፡ አዲሱ መመሪያ ከአንድ ከተማ ወደ ሌላ ለሚደረገው የጫት ዝውውር የቀረጥ ክፍያ የሚጥል ነው፡፡

አነቃቂ የሆነው የጫት ቅጠል የጤናና ማኅበራዊ ቀውሶች በማስከተል፤ የዜጎች ምርታማነት እንደሚቀንስ እና ቤተሰባዊ መስተጋብርን እንደሚያዛባ በጉዳዩ ላይ ጥናት ያደረጉ ይናገራሉ፡፡

የአማራ ክልል አስተዳደር መቀመጫ ባህር ዳር ከተማ በገቢዎች ጽሕፈት ቤት በኩል 2010 ሚያዝያ ወር ላይ በተመሳሳይ በአንድ ኪሎ ግራም 30 በመቶ ወይም 30 ብር ቀረጥ በጫት ላይ ጥሎ ነበር፡፡

በአንጻሩ በተለያዩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ገበሬዎች አገሪቱ በስፋት ትታወቅ የነበረውን የቡና መሬታቸውን ወደ ጫት ማሳነት በመቀየር ጫት ማብቀልን መምረጣቸው ይነገራል፡፡

እንደ መረጃዎች ከሆነ ባለፈው የምርት ጊዜ በአማራ ክልል በዘርፉ የተሰማሩ ከ235 ሺሕ በላይ ገበሬዎች በ10 ሺሕ 886 ሔክታር መሬት ላይ ከ68 ሺሕ ኩንታል በላይ ጫት አብቅለዋል፡፡

ሪፖርተር ጋዜጣ ይዞት በወጣው ዘገባ፤ የጫት ተጠቃሚነት በጨመረበት የአማራ ክልል ገበሬዎች የጫት ምርታቸውን በሌሎች ሰብሎች እንዲተኩ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛል፡፡

ጫት በቅርብ ዓመታት ኢትዮጵያ ወደ ውጭ ከምትልካቸው ቀዳሚ አምስት ምርቶች መካከል የሚጠቀስ ሲሆን፣ ባለፈው የፈረንጆች ዓመት 392 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አስገኝቷል፡፡

በኢትዮጵያ ከሚገኙ ክልሎች በጫት ምርት የኦሮሚያ ክልል ቀዳሚን ደረጃ ሲይዝ፤ በክልሉ የሚገኙ ገበሬዎች 1.3 ሚሊዮን ኩንታል ጫት ያበቅላሉ፡፡ የክልሉ መንግሥት ከአንድ ኪሎ ጫት ሦስት ብር ይሰበስባል፡፡
880 views10:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 11:50:59
ልዩ መረጃ፡ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለደራርቱ የክብር ዶክትሬት ሰጥቷል፡፡ ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ለደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬት የሰጠው ዛሬ ቅዳሜ ነሐሴ 21፣ 2014 ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲው ለደራርቱ ቱሉ የክብር ዶክትሬቱን የሰጠው በአትሌቲክስ ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ በማበርከት ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ ፋና ወጊ አትሌት እና ለህብረሰተብ ፍቅርና አንድነት መጎልበት ላሳየችው ትጋት መሆኑን ገልጧል፡፡ በኦሊምፒክ መድረክ የወርቅ ሜዳሊያ በማግኘት የመጀመሪያዋ ሴት አፍሪካዊት የሆነችው ደራርቱ ቱሉ፤ በውድድር ዘመኗ በታላላቅ መድረኮች ላይ በአሸናፊነት የኢትዮጵያን ባንዲራ ያውለበለበች ታላቅ አትሌት ናት፡፡ ደራርቱ በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዝዳንትነት እያመራች እንደምትገኝ ይታወቃል፡፡
870 views08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 10:12:11 የቅዳሜ ረፋድ ዜናዎች

889 views07:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 18:09:17

967 views15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:32:11
ተጨማሪ መረጃ፡ መንግሥት ለሕወሓት ፀረ ሰላም እብሪት ናቸው ያላቸውን ወታደራዊ ዐቅሞች ኢላማ ያደረገ ርምጃ እወስዳለሁ ብሏል። በመሆኑም በትግራይ የሚገኙ ዜጎች የሕወሓት ወታደራዊ መሣሪያዎች እና ማሠልጠኛዎች ካሉባቸው አካባቢዎች እንዲያርቁ አሳስቧል። ይህ የመንግሥት ማሳሰቢያ የመጣው ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሕወሓትን ወደ ሰላም ያምጣው ካለ ከደቂቃዎች በኋላ ነው።
1.0K views11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 14:00:36
ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሕወሓትን ወደ ሰላም እንዲያመጣው መንግሥት ጠየቀ

አምባ ዲጂታል፤ ዐርብ ነሐሴ 20፣ 2014 ― መንግሥት ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሕወሓትን ወደ ሰላም እንዲያመጣው የጠየቀው ዛሬ ዐርብ ነሐሴ 20፣ 2014 ባወጣው መግለጫ ነው።

በኮሚኒኬሽን አገልግሎት በኩል በወጣው መግለጫ መንግሥት "ያለ ጦርነት መኖር የማይችለው" ሕወሓት ለሰላም የተከፈቱ በሮችን ሁሉ እየዘጋቸው መሆኑን ገልጿል።

መግለጫው አክሎም የመከላከያ ኃይሉ የመንግሥትን የሰላም አማራጭ በመያዝ በጥንቃቄ በመከላከል ላይ እንደሚገኝ ጠቁሟል።

የፌዴራል መንግሥት እና ሕወሓት ለአምስት ወራት ጋብ አድርገውት የቆዩትን ጦርነት ከሁለት ቀናት በፊት ዳግም መጀመራቸው ይታወቃል።

ጦርነቱን ማን ጀመረው በሚለው ሁለቱም አካላት አንዳቸ ው ሌላቸውን እወነጀሉ ይገኛሉ። መንግሥት ሕወሓት ጦርነቱን አቁሞ ወደ ሰላም አማራጭ እንዲመጣ ሲጠይቅ ይህ ለተከታታይ ሁለተኛ ጊዜ ነው።

ለመንግሥት የሰላም ጥሪ ሕወሓት የሰጠው ምላሽ የለም።

https://ambadigital.net/2022/13857/
961 views11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 12:44:20

869 views09:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 10:27:39 የተመድ ዋና ጸሐፊ አንቶንዮ ጉቴሬዝ ቃል አቀባይ የሕወሓት ኃይሎች በመቐለ ከተማ የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን ገብተው ከግማሽ ሚሊዮን ሊትር በላይ ነዳጅ ዘርፈዋል ካሉ በኋላ ጉዳዩ እያነጋገረ ቀጥሏል። በዝርፊያ የተወነጀለው ሕወሓት ያበደርኩትን ነው የወሰድኩት ሲል፣ ነዳጁን ወደ ከተማዋ ላኪው የፌዴራል መንግሥት ነዳጁ ይመለስ ብሏል። አሁን ደግሞ በዚሁ ነዳጅ ዙርያ በመንግሥት ሰዎች ዘንድ መራራ ሥም አላቸው የሚባሉት የአሜሪካ የተራድኦ ድርጅት አስተዳዳሪ ሰማንታ ፓወር አስተያየት ሰንዝረዋል። የረፋድ መረጃችን ይህን ጨምሮ ትላንት ሐሙስ አድመው የዋሉ የጉራጌ ዞን ከተሞች ዛሬ እንዴት እየሆኑ ነው ይላል። ያድምጡ

954 viewsedited  07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 09:27:40
እግረ መንገድ፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሥመ ጥሩ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ‹‹ግሎባል ትራቭል›› የተሰኘ መጽሔት ከመንገደኞች ባሰባሰበው ድምጽ መሠረት የፈረንጆቹ የ2022 ‹‹ምርጥ የአፍሪካ አየር መንገድ›› ሽልማትን አግኝቷል፡፡ አየር መንገዱ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ሽልማቶችን በማግኘት ኢትዮጵያ በዓለም የሚያስጠራ መሆኑ ይታወቃል፡፡
937 views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 16:09:02

1.0K views13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ