Get Mystery Box with random crypto!

ቅኔ እና ዜማ / QINE ENA ZEMA official

የቴሌግራም ቻናል አርማ qineenazema — ቅኔ እና ዜማ / QINE ENA ZEMA official
የቴሌግራም ቻናል አርማ qineenazema — ቅኔ እና ዜማ / QINE ENA ZEMA official
የሰርጥ አድራሻ: @qineenazema
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 262
የሰርጥ መግለጫ

This is an official channel of QINE ENA ZEMA
PLEAS FOLLOW US
https://fb.com/QineEnaZema
https://www.youtube.com/channel/UCxFBvvBoNVtSyTEQbp4MScQ
Like,follow&subscribe

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-10 08:18:45 የእንባ ጸሎት
(Prayer of Tears)

በጌታ ፊት ተግተው የሚማልዱ ስለ ራሳቸውም ሆነ ስለ ሌሎች የሚያነቡ ሰዎች ያስቀኑኛል። ታድለው እላለሁ! እውነተኛ እንባ በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ እንዳለው በጥቂቱም ቢሆን ይገባኛልና!

Gregory of Nassa “እንባ በነፍስ ላይ ላለ ቁስል እንደ ደም ነጠብጣብ ነው።" ብለዋል። አባ አንቶኒ የሚባሉ ቄስ ደግሞ “whoever wishes to advance in building up virtue will do so thru weeping and tears.” ብለዋል!

እንባ የእኛና የዓለሙ ሕዝብ በደል በመንፈሳችን በጥልቀት ሲታወቀን የምንሰጠው መንፈሳዊ ምላሽ ነው። መዝሙረኛው "በልቅሶ የሚዘሩ በደስታ ይለቅማሉ።" (መዝ.126፥5) ያለውም የእንባን ዋጋ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ነው!

Baslea Schlink የሚባሉ ጸሐፊ ስለ እንባ ጸሎት እንዲህ ብለዋል:- "The first characteristic of the kingdom of heaven is the overflowing joy that comes from contrition and repentance….Tears of contrition softens even the hardest hearts."!

እግዚአብሔር ልቡ የተሰበረውን ትሑት አይንቅም (መዝ.51:17)። እንባ ደግሞ ያንን የማሳያ አንዱ መንገድ ነው። በዚህ ረገድ ሪቻርድ ፎስተር እንዲህ መክረዋል:-

➣“When you cannot weep outwardly, shed tears before God in your intention. Have a weeping heart. Keep your soul in tears. Even if the eyes are dry , the mind and the spirit can be broken before God.”

➣"The fire of sin is intense but it is put out by a small amount of tears for the tears put out a furnace of faults, and cleans out wounds of sin."

(Richard Foster, Prayer, 37-46)

☞"አምላክ ሆይ፥ ሕይወቴን ነገርሁህ፤ እንባዬን እንደ ትእዛዝህ በፊትህ አኖርህ።" (መዝ.56፥8)

☞"እናንተ አሁን የምታለቅሱ ብፁዓን ናችሁ፥ ትስቃላችሁና።" (ሉቃ.6፥21)

☞"እናንተ ታለቅሳለችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ፥ ዓለም ግን ደስ ይለዋል፤ እናንተም ታዝናላችሁ፥ ነገር ግን ኀዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል።" (ዮሐ.16፥20)

እግዚአብሔር ሆይ እባክህ
ልባችንን በጸጋህ አለስልስልን!
___
Dr. Bekele birhanu
@nazrawi_tube
186 views05:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-06 13:11:00
. ❝አሁን ሰላም ነው
ዘማሪ ሙሴ አለሙ
C o m i n g S o o n

@nazrawi_tube
644 views10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-28 20:34:08 የሚሹህን አትተዋቸውም

ዛሬ ጧት በማለዳ ከማር ወለላ ይልቅ የሚጣፍጠውን የእግዚአብሔር ቃል አንድ አራት ምዕራፎች አነበብኩ፡፡ መርጬ ካነበብኳቸው ምዕራፎች መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ 9 ይገኝበታል፡፡ ይህንን ምዕራፍ አንዴ አነበብኩና ደገምኩት፡፡ “የውዴ ቃል በተራሮች ላይ ሲዘልል በኮረብቶችም ላይ ሲወረወር ይመጣል፡፡” (መኃ.2፥8) እንደሚል፣ ዓይኔ ከተተከለበት ፊት ለፊት ገጽ ላይ አንዲት ክፍል ተወርውራ ልቤን በሐሤት ሞላችው፡፡ እጅግ ደስ አለኝ፡፡ ወዲያው አምላኬንም ስለ ላከልኝ ቃል በኃይል አመሰገንሁት፡፡ ለእናንተም ይህንኑ ላካፍላችሁ ወደድሁ፡፡ ብትችሉ ሙሉውን ምዕራፍ አንቡት፤ ልቤን የነካው መልእክት ግን የሚከተለው ነው፡-

“ስምህን የሚያውቁ ሁሉ በአንተ ይታመናሉ፤
አቤቱ፣ አንተ የሚሹህን አትተዋቸውምና፡፡” (ቁ.10)

በተለይ በተለይ፣ እጅግ የነካኝ “የሚሹህን አትተዋቸውምና” የሚለው አገላለጽ ነው፡፡ ይህ ሃሳብ መንፈሳዊ መሻት ያለው ሰው የሚያገኘውን በረከት ነው የሚጠቁመው፡፡ ቃሉ “እኔ የሚወድዱኝን እወድዳለሁ፤ ተግተው የሚሹኝ ያገኙኛል” (ምሳ.8፥17) ይላልና!

በመንፈሳዊው ዓለም መሻት፣ መፈለግ፣ ቅናት፣ ግለት(passion)፣ ማሰስ(craving)፣ ጥማት፣ ራብ፣ ጉጉት፣ ናፍቆት ወዘተ እጅግ የሚያስፈልጉ ነገሮች ናቸው፡፡ እነዚህ ነገሮች ወደ ፊት እንድንዘረጋና በጨመረ ሁኔታ ጌታን እንድንፈልገው እንደ ሞተር ነው የሚሆኑልን፡፡ በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት እነዚህ ነገሮች በውስጡ የሚንተከተኩበት ሰው ትጉነት መገለጫው ነው፡፡ ያንን የሚወድደውን ነገር በሚገባ እስኪያገኘው ድረስ አይተኛም፡፡ እረፍት አይኖረውም፡፡ ያነባል፣ ይጸልያል፣ ይመሰክራል፣ ይጽፋል፣ ሃሳቡን ለሰዎች ያካፍላል፣ ወይ ከሰዎች ጋር ስለ ውዱ ያወራል እንጂ ሥራ ፈትቶ መቀመጥ የሚባል ነገር አይታሰብም፡፡

የእግዚአብሔር ቃል “እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው” (መዝ.105፥3) ይል የለ? እንዲህ ዓይነት ሰው የሚፈልገውን ነገር ገና በቅጡ ሳያገኘው ተባርኳል፡፡ እንዴት? “ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው” (ማቴ.5፥6) ከተባሉት ውስጥ ይመደባልና፡፡ ታዲያ ይህ ምስጉን ሳያሰልስ ትኩረቱን አምላኩ ላይ አድርጐ፣ ፊቱን እየፈለገ ሲተጋ፣ የእግዚአብሔርን ክብር ናፍቆ እየተጠባበቀ፣ በጸጋው ዙፋን ፊት ሲያሳልፍ ምንድነው ነው የሚሆንለት? ይጠግባላ! ምክንያቱም ከሚለውምነውና ከሚያስበው በላይ ሊያደርግ የሚቻለው አምላኩ በሕይወቱ ይገለጣል ፡፡

ለእርሱ በቤተ ክርስቲያን በክርስቶስ ኢየሱስ እስከ ትውልዶች ሁሉ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን ፤ አሜን(ኤፌ.3፥ 20)፡፡

@nazrawi_tube
200 views17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-10 20:04:11
ለዘፈን እጅ የማይሰጥ ትውልድ ይሄ ነው።
"በመንፈሳዊ ቅኔ የሰከረ ለክርስቶስ የሸፈተ መልካም ወጣት ነው።"

የማንን አዲስ መዝሙር ማዳመጥ ትፈልጋላችሁ???
ከታች ያለውን መስፈንጠሪያ በመጫን የተወዳዶቹን ዘማሪያንን መዝሙር ማግኘት ትችላላችሁ።
223 views17:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-21 17:33:02 ምንድነው ውስጣዊ መሻታችን?

R.T.Kendall የሚባሉ ግሩም የሆኑ መንፈሳዊ መጻሕፍትን ለንባብ ያበቁ ጸሐፊ ጌታ ኢየሱስን ያገኙት ገና በለጋ ዕድሜያቸው ሲሆን፣ ቤተ ክርስቲያንን በትጋት እያገለገሉ ይገኛሉ። ጌታን ስለማወቅ እንዲህ ይላሉ፡-“Knowing more about God and knowing more of God is the difference between head knowledge and heart knowledge.” አዎ፣ ስለ እግዚአብሔር ማወቅ እና እርሱን በግል ደረጃ (relationally) ማወቅ ይለያያሉ!

የሙሴ ውስጣዊ ፍላጎትና መሻቱ የአምላኩን ክብር ማየት ነበር፡፡ ሊጠይቃቸው የሚችላቸው ስንት ነገሮች ሞልተው ሳሉ፣ እርሱ ግን አንድ ነገር ላይ ብቻ አተኩሮ፣ “እባክህ ክብርህን አሳየኝ።” (ዘጸ.33፥18) ብሎ ተማጸነ። ጠቢቡ ሰሎሞን ብዙ ነገሮችን መጠየቅ እየቻለ፣ “በሕዝብህ ላይ መፍረድ ይችል ዘንድ፥ መልካሙንና ክፉውንም ይለይ ዘንድ ለባሪያህ አስተዋይ ልቡና ስጠው፤ አለዚያማ በዚህ በታላቅ ሕዝብህ ላይ ይፈድ ዘንድ ማን ይችላል?” (1ገ.3፥9) ብሎ ነበር የጠየቀው፡፡ He asked for a spiritual insight and wisdom!

እኛስ እንዲህ ዓይነት ምርጫዎች ቢሰጡን ምን እንል ይሆን? ረጅም ዕድሜ፣ ሀብት፣ ክብር፣ ዝና ወዘተ፡፡ የሐዋርያው ጳውሎስ ጥልቅ ናፍቆት (deepest longing) ጌታ ኢየሱስን ካወቀው በላይ በጥልቀት ማወቅ ነበር፡፡ ያንንም እንዲህ ብሎ ገልጾታል፡ “እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።” (ፊል.3፥10-11)።

እግዚአብሔር አምላክ ከሰው ልጆች የሚሻው ምንድነው? መርምረው እንዲያገኙት ይሻል (የሐዋ.17፥26)፡፡ እርሱን ለማወቅ በሚተጉ ሰዎች ደስ ይሰኛል (ዮሐ.17፥2)፡፡ እኛስ ለመሆኑ ምንድነው ውስጣዊ መሻታችን? የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል፡-

➤ “ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው፥ ይጠግባሉና።” (ማቴ.5፥6)፤

➤ “በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ፥ የልብህንም መሻት ይሰጥሃል።” (መዝ.37፥4)፤

➤ “እግዚአብሔርን አንዲት ነገር ለመንሁት እርስዋንም እሻለሁ፤ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ በእግዚአብሔር ቤት እኖር ዘንድ፥ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውንም አይ ዘንድ፥ መቅደሱንም እመለከት ዘንድ።” (መዝ.27፥4)፤

➤ “እኔ ግን በጽድቅ ፊትህን አያለሁ፤ ክብርህን ሳይ እጠግባለሁ።” (መዝ.17፥15)፡፡

እናም እግዚአብሔር እርሱን በመሻት፣ በመፈለግ፣ በማወቅና በመከተል ይባርከን!
---
Dr. Bekele Brihanu
@nazrawi_tube
@nazrawi_tube
221 views14:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-16 17:17:06
እጸልያለሁ ∞ ቃሉን አነባለሁ።
እጸልያለሁ ∞ ቃሉን አጠናለሁ።

አንድ ክርስቲያን በመንፈሳዊ ሕይወቱ እንዲያድግ (እድገት የሚለውን ቃል እያስተዋልን "እድገት ማለት ከአንድ ዝቅተኛ ደረጃ ወደ ሌላ ከፍተኛ ደረጃ ለማደግ የሚደረግ ግስጋሴ ነው።") መጸለይና ቃሉን ማንበብ መሠረታዊ ነገር ነው።

መንፈሳዊ እድገት ክርስቶስን ወደ መምሰል ማደግ ነው። ልክ አንድ ሰው ሌላውን ወዳጁን ለመምሰል እለት እለት ከእርሱ ጋር መዋል እና ወዳጁ ምን እንደሚያደርግ ፣ ምን እንደሚያስብ፣ አነጋገሩን እና ሁሉ ነገሩን ማጥናት እንዳለበት እለት እለትም እርሱን ለመምሰል መለማመድ እንዳለበት ሁሉ ክርስቶስንም ለመምሰል እለት እለት ድምጹን ለመሰማት ከእርሱ ጋር መነጋገር (መፀለይ) ስለ እርሱ በድንብ ለማወቅ ቃሉን ማንበብ ግዴታ ነው።
በዚህ ላይ መዘንጋት የሌለብን ኢየሱስን ሙሉ ለሙሉ መስለን ወይንም አውቀን ስለማንጨርስ እርሱን መምሰልም ሆነ እርሱን ማወቅ የዘወትር ስራችን ሊሆን ይገባል፤ እርሱን ለመምሰል የምናደርገው የእድገት ግስጋሴ የሁል ጊዜ ነው።

ስለዚህ “ጌታ ቸር መሆኑን ቀምሳችሁ እንደ ሆነ፥ ለመዳን በእርሱ እንድታድጉ አሁን እንደ ተወለዱ ሕፃናት ተንኰል የሌለበትን የቃልን ወተት ተመኙ።”
(1ኛ ጴጥሮስ 2፥2-3)

አስተውሉ “ሰውነትን ለሥጋዊ ነገር ማስለመድ ለጥቂት ይጠቅማልና፤ እግዚአብሔርን መምሰል ግን የአሁንና የሚመጣው ሕይወት ተስፋ ስላለው፥ ለነገር ሁሉ ይጠቅማል።”
— 1ኛ ጢሞቴዎስ 4፥8

ስለሆነም በመንፈሳዊ ህይወቴ ለማደግ፦ #እጸልያለሁ_ቃሉን_አጠናለሁ
#እጸልያለሁ_ቃሉን_አነባለሁ_Challenge!!
---
ይሄን ቻሌንጅ በመቀላቀል ሁሉም ሰው እንዲጸልይ እና ቃሉን እንዲያነብ ቻሌንጅ ያድርጉ

---
nazrawi_tube
Pleas share
194 views14:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-10 15:55:52
#ቆይ_ግን_ላሚቷ_የፈለግነውን_ባትወልድስ?

“ድል ድል ይሸተኛል ኦሆሆ አሃሃ”
ባይሸተንስ ግን?

“ተራራዬን ናደው”
ባይንደውስ ግን?

“በዚህ ስል በረኩቱ በዚያ ስል በረከቱ ከበበኝ”
ቆይ ባይከበንስ?

“ተራው የኔ ነው የኔ”
ቆይ ግን ባይሆንስ?

“የለመንኩትን በሙሉ ሰጠኝ”
ባይሰጠንስ ግን?

ባንጠረምሥስ ግን?
ባንሰባብርስ ግን?
ባናፈራርሥስ ግን?
ባንበዘብዝስ ግን?

በእኛና በፈጣሪ መካከል ያለውን ግንኙነት ፈጽሞ በ “አምጣና እንካ” ቀመር ላይ መመስረት የለብንም፡ እርሱ የሕይወት ቃል አለው ስለዚህ ከምንምና ከማንም በላይ ተመራጭ ነው።
ጠረመስንም አልጠረምስንም NO WHERE TO GO.

ቆይ ቆይ ግን ላሚቷ የምንፈልገውን ባትወልድስ?
ግድ የለም ላሚቷስ ለምትወልደው ሲባል ትፈለግ ፈጣሪ ግን ለምንድር ነው የሚፈለገው?
ለሚሰጠን ወይም ለሚያደርግልን ነገር ነው ወይስ በራሱ ተፈላጊና ተመራጭ ስለሆነ ነው?
#እነዚህ_ሁሉ_አምነው_ሞቱ
___
yilu danu
@nazrawi_tube
173 views12:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-07 19:26:19 ሐዋርያው ጳውሎስ እርግማን / Anathema / ανάθεμα የሚለውን ቃል በተለያየ መልኩ የተጠቀመበት ሲሆን ከእነዚህም ውስጥ ሦስቱ ልብ ሊባሉ የሚገባቸው ይመስሉኛል - በተለይ በወንጌል አገልጋዮች ዘንድ።

#አንድ

ገላትያ 1 ፡ 8
ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፣ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን።

ይሄ “እርግማን” የሚያሳየን ሐዋርያው ጳውሎስ ለሚያገለግለው ወንጌል ምን ያህል እርግጠኛና አይበገሬ እንደሆነ ነው፡ ሌሎች ሰዎች ቢሆኑ ወይም እኛው ራሳችን ተመልሰን ሌላ ወንጌል ብንሰብካችሁ፣ ካስፈለገም ከሰማይ መልአክ አንዱ እኛ አስቀድመን ከነገርናችሁ ወንጌል ያፈነገጠ ቢነግራችሁ “የተረገመ” ይሁን ይላል።
የሚሰብከው ወንጌል ከሌሎች፣ ከራሱም፣ እንዲሁም ከሰማይ መልአክት ሁሉ የሚበልጥ ነው።

ወንጌል ዛሬ በመድረኮቻችን ላይ እንዴት ነው?

#ሁለት

ሮሜ 9 ፡ 3
በሥጋ ዘመዶቼ ስለ ሆኑ ስለ ወንድሞቼ ከክርስቶስ ተለይቼ እኔ ራሴ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበርና።

ይሄኛው “እርግማን” የራሱን የጳውሎስን በስጋ ዘመዶቹ ስለ ሆኑት ስለ እስራኤላውያን ያለውን ጥልቅ ፍቅር የሚገልጽ ነው፡ እነርሱ ይድኑ ዘንድ እኔ ከክርስቶስ ተለይቼ የተረገምሁ እንድሆን እጸልይ ነበር ነው የሚለው፡ This was not his wishful thinking. He literally prayed that he may be accursed.
የሚያገለግለው ወንጌል ከተለመደውና ከምናውቀው የተለየ ፍቅር ውስጥ የሚወጣ ነበር፡ የሚያገለግለው ሰሞነኛ ስለሆነ ሳይሆን ከፍቅር በመነጨ ልብ ነበር፣ ለዛውም የሌሎችን እርግማን ለመሸከም እስኪመርጥ ድረስ።

የወንጌል አገልግሎታችንና ቅናታችን ዘንድሮ ከየት ነው የሚመነጨው?
What is our driving force today to proclaim the gospel?

#ሦስት

1ኛ ቆሮ 16 ፡ 22
ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን የማይወድ ቢኖር የተረገመ ይሁን።

ለጳውሎስ እንደ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደድ የለም፣ ይህን ጌታ የማይወድ ሁሉ “የተረገመ” ይሁን ነው የሚለው፡ ለዚህ ጌታ ያላደረና ያልተገዛ ከእርግማን በታች ይውደቅ ነው የሚለው፡ ኢየሱስን ከማንምና ከምንም በላይ አድርጎት ነበር ያገለገለው፡ ሰዎች እርሱን እንዲወዱት ሳይሆን የሚያበረታታቸው ሁሉም ጌታ ኢየሱስን እንዲወዱ ነበር የሚጋብዘው።

በመድረኮቻችን ላይ የምናገለግላቸው ሰዎች ማንን እንዲያስቡ፣ እንዲከተሉና እንዲወዱ ነው የምናደርገው?

#ማጠቃለያ፡-
ጳውሎስ ግድ የሚሰኝበትን ወንጌል ሰዎችን በመውደድና ሰዎችም ሁሉ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲወዱ በመጋበዝ ነበር ያገለገለው።

እውነት ለመናገር ያስፈራል፣ ምክንያቱም እንዲህ ለማለት ማናችንም አቅም ያለን አይመስለኝም።
የወንጌል አገልጋይ ሆኖ ይህን ለማስተማር ወይም ለመተንተን
ሳይሆን በእውነት ከልቡ ለማለት አቅም ያለው ሰው ብጹዕ ነው።

መድረኮቻችን በዚህ እውነት ሲፈተሹ እንዴት ይሆኑ?

#እንጸልይ፦
አቤቱ ለአንተና ለሰዎች ካለን ፍቅር ያልሰረጸ አገልግሎት
ቤተክርስቲያንን ታደጋት
አቤቱ ለታይታና የራስን ስም ለመትከል ከሚደረግ ሩጫ
ቤተክርስቲያንን ሰውራት
አቤቱ በንግግር ችሎታ እንጂ በፍቅር ካልታጀበ የመድረክ ትወና ቤተክርስቲያንን አድን
___
yilu danu
| @nAZRAWI_tUBE || @nAZRAWI_tUBE |
| @nAZRAWI_tUBE || @nAZRAWI_tUBE |
192 views16:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-19 16:19:24
ለዘፈን እጅ የማይሰጥ ትውልድ ይሄ ነው።
"በመንፈሳዊ ቅኔ የሰከረ ለክርስቶስ የሸፈተ መልካም ወጣት ነው።"

የማንን አዲስ መዝሙር ማዳመጥ ትፈልጋላችሁ???
ከታች ያለውን መስፈንጠሪያ በመጫን የተወዳዶቹን ዘማሪያንን መዝሙር ማግኘት ትችላላችሁ።
3.0K views13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 07:22:41












































ን።
#መልካም_የክርስቶስ_ልደት።


ይሄን ለሚወዱት ሁሉ Forward ያድርጉ
╔══❖•◈•❖══╗
( @nazrawi_tube )
( @nazrawi_tube )
╚══❖•◈•❖══╝
ለበለጠ ቤተሰብ ይሁኑ
[ተ ላ ሉን]
215 views04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ