Get Mystery Box with random crypto!

KIRAMI

የቴሌግራም ቻናል አርማ kiramtube — KIRAMI K
የቴሌግራም ቻናል አርማ kiramtube — KIRAMI
የሰርጥ አድራሻ: @kiramtube
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 384
የሰርጥ መግለጫ

کل قدر من رب الله
کرام😍محمد
(صلوات الله عليك وسلم)
አስተያየት እና ጥያቄዎችን በዚህ አድርሱን👌✔
@seluybot 👈 cross
#leave ከማለታችሁ በፊት ስህተት ካለ በ @seluybot ያናግሩኝ
ባረከላሁ ፊኩም ዉዶች🙏

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-10-20 20:40:32 እብዱ ደራሲ ክፍል ስድስት
በመغፊራ ቢንት ፉላን
............
አረማመዳችንን ላየ ቶሎ ብለህ ና ተብሎ በማስፈራርያ የተላከ ህፃን ነው ምንመስለው ከእርምጃ በጣም በፈጠነ ከእሩጫ ባልተናነሰ እርምጃ ታክሲ መያዣው ጋር ደረስን ታክሲ ሰልፉ እንደዛሬ ረዝሞብኝ አያውቅም ደሞ ለእልሁ ታክሲውም የለም የምንሰራበት ድርጅት መሀል መርካቶ እንደመሆኑ መጠን በስራ መውጫ ሰአት በጣም ብዙ ህዝብ ነው የሚኖረው ያንን ሁላ ሀልቅ ደሞ ሲኖ ካልጫነው በስተቀር አያልቅም። ደሞ ሚጋፋው ህዝብ ብዛቱ ደና ሰልፍ ይይዙ እና ልክ ታክሲ ሲመጣ ሰልፍ የለ መጋፋት ና መራገጥ! አንዳንዱማ እርግጫው አህያ ያስቀናል!የመገናኛ ታክሲ ብዙ ቢመጣም ህዝቡ ሁላ እዛ ሚሄድ ይመስል ታክሲው አይበቃም ግማሹ በቅጥቅጥ፤ግማሹ በሀይገር ቢሄድም ህዝቡ ግን ምንም ያህል ሊቀንስ አልቻለም እንደውም የጫናቸውን በጀርባ እያመጣ ሚገለብጣቸው ነበር የሚመስለው። ብቻ አሰልቺ ነው እኔ ና ሰሙ ሌላ ጊዜ አደለም ልንራገጥ እና ልንጋፋ ይቅርና ብንገፋ ራሱ ይቅርታ እንጠይቅ ነበር፡ዛሬ ግን መቆም ሁላ ሰልችቶናል ተጋፍተን እንደማይሆንልን እያወቅን መጋፋትን መርጠናል ግን ምንም ሊሳካልን አልቻለም እንደውም አንድ አህያ የሚያስንቅ ሰውዬ እግሬን ረገጠኝ በጥፊ ብለው ሁላ በጣም ደስተኛ ነበርኩ! ደሞ ከሱም ብሶ እያየሽ አትጋፊም?አለኝ ሰሙ ሳቅ መቆጣጠር የሚባል ነገር አልፈጠረባትም ሳታስበው በሰማችው የሰውየው ንግግር ሳቋን ለቀቀችው ና እኔን ከመሀል ጎትታ አወጣችኝ እኔ ለራሴ እግሬን አሞኛል አንቺ ትገለፍጫለሽ አ።?ብዬ ግልምጥ አደረኳት!እሷ ግን አደለም አይዞሽ ልትለኝ ማውራት እስኪያቅታት ትንተከተካለች አሁን ከሰውየው እርግጫ እና ግልምጫ የባሰ የሷ ሳቅ አበሸቀኝ።ችግር አለብሽ ወላሂ አንዴ መሳቅ ከጀመርሽ አታቆሚም አ?ደሞ ምን አለ ሚሳቅበትን ቦታ እንኳን በስርዐት ብታውቂ?ኡሚ እንደዛ ሆና እየጠበቀችን አንቺ እዚ ታሽካኪያለሽ? ገደል ጊቢ ስፈልጊ !ብዬ ሰሙን ጥያት ወደ ታክሲው ሰልፍ ሄድኩ የተናገርኳት ሁሉ በንዴት እና በጭንቀት ብዛት ቢሆንም ጥፋተኛ ነች ብዬ ደምድሜያለው። እሺ በቃ ይቅርታ!ነይ ራይድ እንጥራ? እኔጋ ብር ስላለ እኔ ከፍላለው አለችኝ በተሰበረ ድምፅ ምንም መልስ አልሰጠውኋትም! ሰሙን አስከፍቻታለው ግን አሁን ከሷ በላይ የማሂር ነገር ነው ሚያሳስበኝ ስለዚ መለማመጥም ይቅርታም መጠየቅም አልፈለኩም። ራይዱ በ5 ደቂቃ ውስጥ ያለንበት መጣ እቤት እስክንደርስ በጣም ቸኩያለው የኔ ፍጥነት ደሞ የተለየ ነበር ሹፌሩን ቀይሬው ብነዳ ሁላ ደስተኛ ነኝ ይህን ያህል ያንገበገበኝ ግን ምንድነው? መመለስ ያልቻልኩት ጥያቄ!የትራፊክ መብራቱ 2 ደቂቃ ሳይሆን 2ሰዐት ሆነብኝ፧ ልጅ ጥላ እንደመጣች እናት ነበር ያደረገኝ ሰሙ ግን ተረጋግታለች ፊቷ ቢረበሽም ልቧ በጭንቀት ቢወጠርም የኔን ያህል አልቸኮለችም ግን የረበሻት የኔ ንግግር ይሁን የማሂር ነገር አላወኩም ዝም እንደተባባልን ሰፈር ደረስን ለምን እንደሆነ ባላውቅም ወደሰፈር መግቢያ ጋር ስንደርስ ሰሙ እዚጋ አውርደን አለችው ሌላ ቀን በራይድ ስንመጣ ቤት ያድርሰን የምትል ልጅ ዛሬ ጭራሽ ሰፈር መግቢያው ላይ በቃ ተናዳለች ወደ ቤቷ ልትሄድ ነው ብዬ ስላሰብኩ ምንም ሳልል ወረድኩ እሷም ሂሳቧን ከፍላ ተከተለችኝ። ወደነሱ ሰፈር መግቢያ ቅያስ ጋር ስንሄድ ትሄዳለች ብዬ ነበር ግን እንደፈራሁት አላደረገችም ትንሽ ቅልል አለኝ።ወደ እኛ ሰፈር ስንቃረብ ሰሙ እጄን ይዛ አስቆመችኝ እና እህቴ በጣም እንደጨነቀሽ የማሂርን ነገር ለማየት እንደቸኮልሽ አውቃለው ግን መጀመርያ እራስሽን አሳምኚው ሁሉንም የሚያደርገው አላህ ነው እናም ተረጋጊ ተረብሸሽ ኡሚን እንዳትረብሻት አለችኝ ከኡሚ ጋር በስልክ ያወሩት ነገር ሰሙ ፊቷ ሲቀያየር ኡሚ የኔን ድምፅ ስትሰማ የደነገጠችው ድንጋጤ የሆነ ነገር እንደተፈጠረ አሳመነኝ ሳላስበው ማሂር ሞቷል አይደል ሰሙ ብያት እንባዬ ያለ ገልጋይ መፍሰስ ጀመረ ሰሙ በጣም ደነገጠች ወላሂ ውዴ እንደዛ አደለም እኔ ምንም ማውቀው ነገር የለም የተፈጠረውን ነገር ስለማናውቅ እንጠንክር ብዬ ነው ብላ እሷም እንባዋን ያለ ከልካይ አፈሰሰችው።አሁን ስድቡም ሳቁም ተረስቶ ሁለታችንም በማሂር ሀሳብ ገብተናል ሰሙ ሁሉንም እንዳልተፈጠረ አድርጋ ትታዋለች። እንባችንን ጠራርገን ወደ ሰፈር ገባን ሰፈር ውስጥ ምንም አዲስ ነገር አላየሁም ምን አልባት ዘመድ ስለሌለው ይሆን? እቤት ስንገባ ኡሚ እቤቱን አጫጭሳ ቡና አፍልታ እየጠበቀችን ነበር ሱፍራ ላይ ሰሙ ምትወደውን የክትፎ ጥብስ በአንድ ሰሀን እኔ የምወደውን እሩዝ በአንድ ሰሀን ሻይ አድርጋ እየጠበቀችን ነው የማየውን ነገር ማመን አልቻልኩም ኡሚን የጠበኳት እያለቀሰች አዝና ምናምን ነበር ግን ከጠበኳት በተቃራኒ ነበር ያገኘውሀት እኔና ሰሙ ተያየን ብቻ የኡሚ እንደዚ መሆን ሁለታችንንም አረጋግቶናል ግቡ እንጂ ምን ይገትራቹሀል፤ እናንተን ስጠብቅ ቡናውን እኮ ቀቀልኩት አለችን ሁላታችንም ሰላም ብለናት ቦርሳችንን ጥለን እጃችንን ልንታጠብ ወደ ውስጥ ገባን ሰሙም እኔም ግራ ቢገባንም ኡሚ ስላቻኮለችን ምንም ሳንል ወደ ሳሎኑ ተመለስን በሱፍራው ዙርያ ተቀምጠን ምግብ መብላት ጀመርን ኡሚ ማሂርን ከነመፈጠሩ የረሳችው ትመስላለች እኔ እና ሰሙ ግን ማሂርን ማሰብ አላቆምንም ኡሚን መጠየቅም ፈርተናል ምን አልባት ማሂር እኛ እንደገመትነው ሆኖ ቢሆን እና ኡሚ እሱን ለመርሳት ቢሆንስ እንደዚ እያደረገች ያለችው? ኡሚ ቀኑን ሙሉ የሰራችውን ሁሉ እያወራችህን ነበር ግን አንዴም ቢሆን ስለ ማሂር አላነሳችም በጣም ግራ ገብቶኛል አሁን ግን ልጠይቃት ወስኛለው እኔ ምልሽ ኡሚ ወዬ አለችኝ በጣም እየፈራው ቢሆንም ማሂር እንዴት ሆነ? አልኳት የፈራሁት አልቀረም ኡሚ እንባዋን ያለከልካይ አወረደችው ሰሙ እና እኔ ድንጋጤ አደነዘዘን በተቀመጥንበት ደርቀን ቀረን ተነስተን እንኳ ኡሚን ለማማበል አልደፈርንም .......
ክፍል ሰባት ይቀጥላል....
519 viewsÏküti ‿ , 17:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-20 06:34:53 ከመዉሊድ በኋላ ተመልሻለዉ።እብዱ ደራሲም ድርሰቱን ይቀጥላል
377 viewsÏküti ‿ , 03:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-20 06:33:20 እብዱ ደራሲ ክፍል አምስት
በመغፊራ ቢንት ፉላን
.........
እኔና ሰሙ የደወለችው ኡሚ መሆኗን ስናውቅ በድንጋጤ ቆመን ቀረን መንገድ ላይ ስለሆነ ያለነው ስልኩን ማንሳት አልፈለኩም ኡሚ ስለ ማሂር ምንም አለችኝ ምን መንገድ ላይ ማውራቱን አልፈለኩትም ሰሙም ሀሳቤን ተገራታኛለች ኡሚ ደጋግማ ብትደውልም ቢሮ እስክንገባ ላለማንሳት ወስነናል ሌላ ቀን እያዘገመን ሚያጥርብን መንገድ ዛሬ ግን ረዝሞብናል ሁለታችንም ውስጣችን በፍርሀት ተሞልቷል እንዴትም ብለን ቢሮ ስንደርስ የቢሮውን በር ክፍት አገኘነው ሁለታችንም በድንጋጤ እና በመሰላቸት አይነት አስተያየት ተያየን በቃ ሰውዬሽ መቷል ማለት ነው አለችኝ በሹክሹክታ ይሆናል በቃ ኤጭ ካልጠፋ ቀን በዚ ሰዐት ይመጣል ምኑ ብሽቅ ነው በአላህ አልኳት ስንገባ የሚከተለንን የስራ ብዛት እያሰብኩኝ፤ አለቃችን ከእድሜ ብዙም ከኛ አይበልጥም ነገር ግን ነገረ ስራው ሁላ እንደሽማግሌ ነው መነጫነጭ በጣም ይወዳል ሰሞኑን እቃ ሊያመጣ ወደ ዱባይ ሄዶ ስለነበር ደህና ተገላግለነው ነበር ደሞ ሳይናገር ነው የሚመጣው እሱ እዚ ቢሮ አለ ማለት ማውራት የለ መሳቅ የለ ስልክ ማውራት የለ በፈለጉ ሰዐት መውጣት መግባት የለ ከእኔ ጋር ማ የሆነ ጂኒ አያይዞታል ሲሀም እንዲ ሆነ ሲሀም እንደዛ ሆነ ሲሀም በዚ ገባ ሲሀም በዚ ወጣ በደቂቃዎች ውስጥ 50ጊዜ ነው ስሜን ሚጠራው በሱ የተነሳ ስሜን ራሱ ጠልቼዋለው አንዳንዴማ እዛ ቢሮ ውስጥ ካለእኔ ሰራተኛ ያለ አይመስለውም ሰሙን ከነመፈጠሯ ረስቷቷል ሌላ ቅርንጫፍ ቢኖረውም እሱ ግን ካለዚ ቢሮ ያለው አይመስለውም አሁንማ ጭራሽ ከአጠገባችን ያለውን ቢሮ የራሱ ሊያደርገው እያሳደሰው ነው እሱ እዚ ቢሮ የገባ ቀን እኔ ወደ ሌላ ቢሮ ቀይሩኝ እላለው ወይም ከስራው እለቃለው ስላት ከትከት ብላ እየሳቀች ስለሚወድሽ ነው ኮ ትለኛለች ለዛም ነው ሰውዬሽ ምትለኝ ።እኔ ግን አሁን ከስራው እና ከአለቃችን በላይ የማሂር ነገር በጣም አሳስቦኛል ቢሮ ከገባን በውሀላ ለኡሚ መደወል እንደማልችል ብደውልም በስነስርዐት እንደማላወራት ስላወኩኝ ሰሙን ከመግባታችን በፊት እንደውልላት አልኳት ሰሙ ምንም እንኳን የማሂር ነገር ቢያስጨንቃትም ኡሚን በተጣደፈ አነጋገር ማናገሩን አልመረጠችም እሱ ለምሳ መውጣቱ ስለማይቀር በዛ ሰዐት እንደውላለን ባይሆን እንዳትጨነቅ አለቃችን እንደመጣ ንገሪያት ስራ እንደበዛብን ይገባታል ብላኝ ለኡሚ ደወልኩላት ግን ለማናገር ድፍረቱን ስላጣው ለሰሙ ሰጠውኋት ሰሙ የኡሚን ድምፅ ስትሰማ ፊቷ ተቀያየረ ግን እኔ እንድነቃባት ስላልፈለገች በግድ ለመሳቅ እየሞከረች ነበር ነገሩ ግራ ስለገባኝ ስልኩን ተቀብዬ ኡሚ ደና ነሽ አልኳት ኡሚ ድምፄን ስትሰማ እንደደነገጠች ድምጿ ያሳብቅባታል ከኡሚ ድምፅ ጀርባ ለቅሶም አይሉት ሳቅ የሚመስል ድምፅ ይሰማኛል አሁን ከቅድሙ የበለጠ ልቤ በፍርሀት ልፈነዳ ደርሳለች ደና ነኝ ሲሁ እንዴት ዋልሽልኝ እህትሽ እኮ አለቃቹ እንደመጣ ነገረችኝ ስራ ይበዛባቹሀል በቃ ጠንክሩልኝ ልጆቼ ደና ዋሉ በተመቻቹ ሰዐት ደውሉልኝ በቃ ካልሆነም ቤት ኑ አብራቹ ምትወዱትን ምሳ ሰርቼ ጠብቃቹሀለው ብላ ምንም መልስ እንዳልሰጣት በሚመስል መልኩ ስልኩን ጆሮዬ ላይ ጠረቀመችብኝ። ይሄ የኡሚ የሁልጊዜ ንግግር እንደሆነ ባውቅም የዛሬው ግን የሀዘን እና የስስት ነገር አለበት። አሁን የበለጠ ልቤ ፈርቷል ቦርሳዬ ውስጥ ባይሆን እና ይ የተመታ ሰውዬ ባይመጣ ኖሮ ወደቤት እሄድ ነበር አሁን ግን ግዴታ ነው መግባት እና ከሰሙ ጋር ወደ ውስጥ ገባን ገና ከመግባታችን እሺ ማጂላኖች በስራ ሰዐት እንኳን አትቀመጡም ብሎ በነገር ለኮሰን ምን አለ አሁን የመጣው ከዱባይ ነው ሰላምታው አይቀልም የተረገመ ሼባ ብዬ በውስጤ ተሳድቤ ወደ ቦታዬ ሄጄ ተቀመጥኩኝ ገና ከመቀመጣችን ይህን የስራ order ጀመረ በቃ እኔና ሰሙ የማሂርን ነገር ባንረሳውም ግን አሁን 75% የሚሆነው ሀሳባችን ስራው ላይ ሆኗል ሳናውቀው ሰዐቱ 9 ሆኗል ለካ አረ ዙሁር እንስገድ አለች ሰሙ በዛውም ምሳ እንብላ አይነት መልእክት በቃ በተራተራ ስገዱ ምሳ ደግሞ እኔ ነኝ ምጋብዛቹ እዚው አብረን እንብለላን ብሎ የኛን ፍቃድ እንኳ ሳይጠይቅ ደውዬ ልዘዝ ብሎ ወጣ ምሳ ሰዐት ላይ ኡሚ ጋር እንደውላለን ብለን የነበረ ቢሆንም ይሄ ሰውዬ ግን ምንም እረፍት ሊሰጠን አልቻለም ሁለታችንም በሰጨት ብለን የየራሳችንን ስድብ አወረድንበት እና በቃ ውዴ ተረጋጊ አላህ ያለው ነው ሚሆነው ብላ ግንባሬን ሳመችኝ እና ለኡዱ ወጣች በተራ በተራ ሰገድን እና ምሳችንን መቶ በልተን ወደ ስራችን ገባን አሁንም እንደቅድሙ በስራ ተወጥረን ሳናውቀው 12 ሰዐት ሆኗል ለካ ኡሚ ደወለች በድንጋጤ ቀና ብዬ ሰሙን አየውሀት አለቃችን ፊትለፊት ስለነበር ማውራት አልቻልንም ዝም ብዬ ስልኩን አንስቼ ወዬ ኡሚ አልኳት አሁን ከቅድሙ ድምጿ መረጋጋት አለው እናንተ ልጆች ቡናው ኮ ቀዘቀዘ አለችኝ መጣን መጣን ኡሚ ልንወጣ ነው አልኳት በዛውም ለሰሙ እንውጣ ለአዩብ ደግሞ ልንወጣ ነው የሚል መልእክት እያስተላለፍኩ ነው። ስልኩን ስዘጋው በቃ ሂዱ ጠዋት በጠዋት ኑ እና ትጨርሱታላቹ አለን ማስጠንቀቂያ መሆኑ ነው እሺ ደና እደር ብለን ተያይዘን ውልቅ ብለን ወጣን ሁለታችንም እቤት እስክንደርስ ቸኩለናል ኡሚ ስለማሂር ምን ትለን ይሆን ማሂር ምን ሆኖ ይሆን.......?
ክፍል ስድስት ይቀጥላል ......
416 viewsÏküti ‿ , 03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-02 20:11:30
10 ሺዎች እሚታደሙበት ታላቅ ሀገር አቀፍ መውሊድ በጣት እሚቆጠሩ ቀናት ብቻ ቀረው!!!!!!!!
@madihmohammed
519 viewsMadih ibnu ahamed , 17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-28 19:56:16 እብዱ ደራሲ ክፍል አራት
በመغፊራ ቢንት ፉላን
........
እንደገመትኩት ነበር የሆነው ከድርጅቱ ደውለው ፈተናውን እንዳለፍኩ እና ስራ መጀመር እንዳለበኝ ተነገረኝ። የሀዘን እና የደስታ ስሜት ነበር የተሰማኝ፤ቀስ ብዬ ኡሚ ጋር ሄድኩ እና ነገርኳት ኡሚ በጣም ትጨነቅላታለች "በቃ አትንገርያት ይከፋታል ለሷ ካልተደወለላት ስራው ይቀራል ከፈለገ! እኔ እናታቹ እንድትለያዩብኝ አልፈልግም አሁን ሂጂ እና ቀስቅሻት ቁርስ ደርሷል"አለችኝ።ኡሚ እንደዛ ስትለኝ ቅልል አለኝ ወደ ክፍሌ ስገባ ሰሙ ነቅታለች "ሴትዬ ተነስተሻል እንዴ?ነይ በይ ቁርስ ቀርቧል" አልኳት እና ወጣው ሰሙ ፊቷ ልክ አደለም የተረበሸ ከተማ መስላለች ቁርሱንም በስነስርዐት እየበላች አደለም የሰሙን እንደዛ መሆን ስናይ የኔም የኡሚም ግምት አንድአይነት ነበር "ምነው ሰሙ ደና አይደለሽም እንዴ ፊትሽ ልክ አደለም?" አለቻት ኡሚ "አረ ምንም አልሆንኩም ኡሚ ስቃዥ ነበር ያደርኩት" አለቻት እየዋሸች እንደሆነ ሁለታችንም አውቀናል "አብሽሪ እህቴ ብዬ ሳብ አድርጌ አቀፍኳት" አንገቴ ውስጥ ተወሽቃ "ወድሻለው እሺ ምንም ይሁን ምን ካንቺ አይበልጥብኝም" ስትለኝ ሳላስበው እንባዬ ወረደ ኡሚ ብቸኛ ልጇ ስለሆንኩ እንደዚች አይነት እህት በማግኘቴ በጣም ደስ ብሏታል "አብሽሩልኝ እኔ እናታቹ እያለው ማንም አይለያቹም!"ብላ ሁለታችንንም ሳመችን እና የበላንበትን እቃ አንስታ ወደ ኩሽና ገባች ሰሙም ሱፍራውን ጥቅልል አድርጋ ኡሚን ተከተለቻት ኡሚና ሰሙ በሹክሹክታ ሲያወሩ ይሰማኛል፤ ኡሚ ለሰሙ እየነገረቻት ይሁን? ብዬ በጣም ፈርቻለው። ወሬያቸውን ጨርሰው ከኩሽና ሲወጡ ኡሚ ያለመደባትን "ሂዱ በሉ የሰሙን ቤት ፏ ፏ አድርጋቹ ኑ" ብላ ላከችን "ሰሙም አይ እኔ ብቻዬን እሄዳለው" አለች? "ከመች ጀምሮ? አለች" ኡሚ በመቆጣት ድምፅ እኔም ግራበመጋባት ቀና ብዬ አየውሀት እንደከፋት በጣም ታስታውቃለች ኡሚን በቁጣ አይነት አስተያየት ሳያት"ምን ታፈጪብኛለሽ?ተነሺ ደርሳቹ ኑ" አለችኝ አሀ ሌላ ቀን የሰሙን ቤት አፅድተን እንኳን እንመለስ ስንላት የምን ቤት ነው? የሷ ቤት እዚ ነው! እንደውም እቃውን ጭናቹ ኑ! ነበር የምትለን ዛሬ ምን ተገኘና ነው? በቃ ሰሙ ፈተናውን አላለፈችም!ኡሚም ነግራታለች ለዛ ነው ሰሙም ብቻዬን እሄዳለው ያለችው።ኡፍ ኡሚ ደሞ ምን አጣደፋት ደሞ ከፈለገ ይቀራል ብላኝ አልነበር እንዴ? ብቻ በፍርሀት ስሜት ውስጥ ሆኜ ከሰሙ ጋር ተያይዘን ወጣን። የሰሙ ቤት ከኛ ብዙም አይርቅም፤ሌላ ቀን በእግራችን ነበር ወደሷ ቤት የምንሄደው፤ ዛሬ ግን ሁለታችንም አይደለም እየተጓተትን በእግራችን የመሄድ ታክሲውም ቀርቶብን እቤት ብንቀመጥ ሁላ ደስተኞች ነበረን። ከኡሚ ጋር ላለመነታረክ ነው የወጣነው፤ምንም አላወራንም። አንዴ ብቻ ሰሙ "ሲሁ ከድርጅቱ ደወሉልሽ እንዴ? አለችኝ። በጣም ነው የደነገጥኩት "አይ አረ አልደወሉም ላንቺ ደወሉልሽ እንዴ?" አልኳት "አይ" አለችኝ ብቻ እንደዛ እንደደባበረን የሰሙን ሁለት ክፍል ቤት እንደነገሩ አፀዳድተን ያልታጠበውን እቃ አጥበን ወደቤት ተመለስን።
..........
እቤት ስንገባ ኡሚ ጓረቤት ሰብስባ ዳቦ ደፍታ ቤቱን በዐል አስመስላ ነበር የጠበቀችን።ገና ከበር ስንገባ በእልልታ ጊቢውን አቀለጠችው እኔም ሰሙም ተያየን ሁለታችንንም አቅፋን አለቀሰች ለካስ ሁለታችንም ፈተናውን አልፈን ኖሯል ደስታችን ልክ አልነበረውም ከሳምንት በውሀላ ሁለታችንም ስራችንን ጀመርን አንድ ድርጅት አንድ ቢሮ ላይ ሰሙ አንዳንዴ ቤቷ ብዙውን ጊዜ እኛ ቤት መኖር ጀምራለች።
..................
"ነይ በቃ ምግብ አልበላሁም እየሄድን እነግርሻለው" አልኳት እና የቢሮውን በር ዘግተን ወጣን። ወደ ምግብ ቤቱ ስንሄድ ጠዋት የሆነውን ከሀ እስከ ፖ ነገርኳት ሰሙ ማሂርን እኛ ቤት ስትመላለስ ታውቀዋለች የመጀመርያ ሰሞን ትፈራው ነበር አረ!ጭራሽ ወደሰፈሩ መምጣት አቁማ ነበር ከጊዜ ቡሀላ ግን ማሂር እብድ አደለም! ብላ ትሞግት ጀምራለች። በነገርኳት ነገር አዝናለች፤ የኔ ስሜት ተጋብቷባታል ፤ተፅናንታ ልታፅናናኝ ፈልጋለች:ግን ሁለታችንም ውስጣችን ፈርቷል ማሂር ሞቶ ይሆን? የሁለታችንም ጥያቄ ነው! ግን ማን ይመልስልን? ምግቡን አዘን እንደነገሩ ቀማምሰን ተውነው፤ "ምነው?ምግቡ አልጠፈጣቹም እንዴ?" የሚለው የእማማ ጥያቄ ነበር ከሀሳባችን ያባነነን፡ልክ እንደተመካከረ ሰው እኩል "አረ ይጣፍጣልእማማ!"አልን ንግግራችን ለራሳችን ፈገግ አደረገን እና ሂሳብ ከፍለን ወጣን የሁለታችንም ሀሳብ ማሂር ጋር ነበር ምንም ማውራት አልፈለግንም እናውራ ብንልስ ውስጣችን እየተረበሸ እንዴት ብለን ብቻ በሀሳብ ተጠምደን ወደ ቢሮ በዝግታ እየሄድን የኔ ስልክ ጠራ ኡሚ ነበረች.......
ክፍል አምስት ይቀጥላል.........
552 viewsÏküti ‿ , 16:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-26 19:55:43 እብዱ ደራሲ ክፍል ሶስት
በመغፊራ ቢንት ፉላን
.......
ሰዐቱ አምስት ሰዐት ሆኗል ሰሙ ጠዋት ስላረፈድኩባት እንደተኮፈሰች ኮምፒውተሯ ላይ አፍጥጣለች። እኔም የማሂር ነገር በጣም ስላሳሰበኝ ቢሮ ከገባው ጀምሮ ከማንም ጋር አላወራሁም እሷንም ቢሆን እንደ ሌላ ቀኑ አልተለማመጥኳትም። ሰሙ ልምምጥ ትወዳለች እኔ ደሞ ይህን ፀባዮን ስለማውቅ እለማመጣታለ፤ ዛሬ ግን ምንም አላልኳትም ቁርስ አለመብላቴን እንኳን ረስቼዋለው። ሰሙም እንደደበረኝ ገብቷቷል፤አስር ጊዜ ስልክ ስደውል በቆረጣ ታየኛለች አጠገቤ መታ ልታወራኝ ፈልጋለች፤ሄጄ አንዴ እንኳን ሰሙ በቃ Sorry ብላት እንደምትመለስ አውቃለው፤ግን በቃ ዛሬ ሙዴ አደለም! የማሂር ነገር አስጨንቆኛል፤ምን አለ ባልመጣው? እቤቴ ሆኜ ምን እንደተፈጠረ እንኳን አውቄ ነፍሴ ትረጋጋ ነበር!
"የኡሚ ስልክ አለማንሳት ደግሞ የባሰ ጭንቀቴን ጨመረው ""ማሂር ምን ሆኖ ይሆን መኪና ገጭቶት ነው? ሰዎች ደብድበውት ነው? ወይስ ሞቶ ነው?"ይህንን ሳስብ ሳላስበው እንባዬ ፈሰሰ።ሰሙ እያየችኝ እንደሆነ እንኳን አላስተዋልኩም "አሀ ሲሁ እያለቀሽ እኮ ነው" ብላ ከወንበሯ ላይ ተስፈንጥራ መታ አጠገቤ ተቀመጠች:እንባዬን ጠራርጌ"sorry ሰሙ" አልኳት "አሁን እሱን ተይው እና ምን ሆነሽ ነው? ኡሚዬ ደና አደለችም እንዴ?ከገባን ጀምሮ ኮ ልክ አደለሽም!" አለችኝ "ምንም ሰሙ ዝም ብዬ ነው" "ኡፍፍ አንቺ ደሞ ችግር አለብሽ ወይስ ሰውዬሽ ናፍቆሽ ነው?" ስትለኝ ሳቄን ለቀቅኩት።
..................................
ሰሙ የሳቄ ምንጭ፤ የጭንቀቴ ማቅለያ ነች። ትውውቃችን የቅርብ ጊዜ ቢሆንም ለሚያያየን የልጅነት ጓደኛሞች እንጂ የአመት ከ6 ወር ትውውቅ አይመስልም። ያወኳት እዚው መስሪያ ቤት ልቀጠር ሲቪ ላስገባ ስመጣ ነው እሷም እንደኔ ልትቀጠር መሆኑ ነው። ድርጅቱ የሚፈልገው ሁለት ሴት ብቻ ነው። እንደኛ ሊቀጠሩ የመጡት ግን ከ50 ይበልጣሉ፤ድርጅቱ የሙስሊም ስለሆነ ግማሽ ያህሉ ሙስሊሞች ናቸው።እኔና ሰሙ ወረፋችን ከፊት እና ከውሀላ ስለነበር ለመግባባት አልተቸገርን፤ የትት ማስረጃችንን የሚቀበለን ሰው አራት ሰዐት ቢሆንም ሚገባው እኛ ግን ወረፋ ለመያዝ ስንል ጠዋት አንድ ሰዐት በቦታው ተገኝተናል። ከሰሙ ጋር ብዙ አወራን፤ እዛ ቦታ ላይ የተገናኘን ሳይሆን አብረን የመጣን ነበር የምንመስለው፤ሰሙን ስላገኘውሀት ደስ ብሎኛል፤ የሚገርመው ደሞ ሁለታችንም የ Accounting ተመራቂ መሆናችን እና የተማርንበት ትት ቤት መገጣጠሙ ነው። ያልተዋወቅነው ሰሙ የማታ ተማሪ ስለሆነች እኔ ደሞ የቀን ተማሪ ስለሆንኩ ነበር።"እራሴ እየከፈልኩ ስለሆነ የማታ ነበር የምማረው"አለችኝ "ዋናው መማርሽ ነው ባክሽ!" አልኳት። እንደዛ እንደዛ እያልን ብዙ ብዙ ነገር አወራ፤ ሲበዛ ግልፅ መሆኗ አስገረመኝ፤ብዙ ጓደኞች ቢኖሩኝም ሁሌም አብሬያት መሆንን ተመኘው፡ አሁን ወረፋችን ደርሷል፤ ሁለታችንም ገብተን ወረቀታችንን አስገባን እና ተያይዘን ወጣን "ሁለታችንም አልፈን አብረን ብንሰራ ደስ ይለኛል" አለችኝ የኔም ፍላጓት ነበርና "ኢንሻአላህ" አልኳት ስልክ ተለዋወጥን እና ተለያየን። ከሰሙ ጋር ቅርርባችን በጣም ጠብቋል እቤት ትመጣለች ኡሚም ወዳታለች የትት ማስረጃ ያስገባንበት መስሪያቤት ስለፈተና ስንጠራ አብረን ነበር የሄድነው ውጤቱ ግን በጣም ዘግይቷል ሁለታችንም ተስፋ ቆርጠናል፤ ቢሆንም ግን አልደበረንም፤ አብረን እንውላለን፤አንዳንዴ ሁላ ሰሙ እኛ ቤት ታድራለች የምትኖረው ብቻዋን ስለሆነ ወደቤቷ ምትሄደው ለአዳር ነው። ቤተሰቧቿ እንደሞቱ እና ከአያቷ ጋር ክፍለ ሀገር እንደኖረች፤የ10ኛ ክፍል ውጤት ሲመጣላት በአጓቷ ልጅ እገዛ አ.አ እንደመጣች እና ከሱ ጋር እንደነበር የምትኖረው፤ ነገር ግን ሚስቱ ክፉ ስለነበረች የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እንደመጣላት ስታውቅ ከሱ ጋር አጣልታ ከቤት እንዳባረረቻት እና እሱም ከሚስቱ ተደብቆ እንደሚረዳት፤ ስራ እንዳስጀመራት፤የቤት ኪራይ ይከፍልላት እንደነበር፤የማታ ትት ያስመዘገባት እሱ እንደሆነ፤ ከአመት በውሀላ ግን በልብ ህመም እንደሞተ ሁላ በመጀመርያው ቀን ነበር የነገረችኝ። ይህንን ሁላ ስቃይ በልጅነቷ ስለተሸከመች ታሳዝነኛለች ጥንካሬዋ ብርታቷ በጣም ይገርመኛል።አንድቀን እንዲ ሆነ ሰሙ እኛ ቤት ነበር ያደረችው በጠዋት ስልኬ ጠራ ና ተነሳው ሳየው ባለፈው የተፈተንበት ድርጅት ቁጥር ነው ምን አልባት ሰሙ ካላለፈች ሳወራ እንዳትሰማ ብዬ ኔቶርክ እንደተቆራረጠበት ሰው ሄለው እያልኩ ከክፍሌ ወጣው.....
ክፍል አራት ይቀጥላል....
428 viewsÏküti ‿ , 16:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-26 19:55:43 ሰዎች እራሳቸውን ካሉበት ስሜት ለመፈወስ ብቻ የሚያደርጉት የተለያዩ መንገዶች አሉ:-አንዳንዶች ለተወሰነ ጊዜ ስለ እውነታው እስኪረሱ ድረስ በአልኮል መጠጥ እራሳቸውን ይደብቃሉ፣አንዳንዶች በሲጋራ ጭስ ውስጥ ተሸሽገው ችግራቸውን እና ጭንቀታቸውን ከጭሱ ጋር በማውጣት ህመሙ አብሮ እንደሚሄድ ያስባሉ ፣ አንዳንዶች ሥቃያቸውን ለመራቅ ወደ ጥበብ ሥራ ይሸጋገራሉ - ታሪኮችን ልብወለዶችን እና ግጥሞችን ያነባሉ አልያ ይጽፋሉ ፣ሙዚቃ እና የሙዚቃ መሣሪያዎችን ይጫወታሉ ፣ አንዳንዶ ፊታቸውን ሙሉ ለሙሉ ወደ ፈጣሪያቸው አዙረው ሁሉን የዚህችን ዓለም ነገር እርግፍ አድርገው ይተዋሉ፡፡ አንዳንዶቹ በሥራ የተጠመዱ ይሆናሉ ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ ቀኑን ሙሉ በአልጋ ላይ በመተኛት እረፍት ማድረግን ይመርጣሉ ፣ አንዳንዶቹ ከራሳቸው የትውልድ ከተማ አምልጠው እራሳቸውን በተለያዩ ስፍራዎች ይሸሽጋሉ like-በባህር አጠገብ ባሉ ቦታዎች ፣ በተራሮች አናት ላይ ወይም ደግሞ የተፈጥሮን ልዩ መስዕብ ያለበት ጫካ ወይንም ገጠራማ ቦታ ላይ ሄደው ከችግሩም ችግሩንም ካስከተሉባቸው ሰዎች ይርቃሉ፡፡ ሰዎች እራሳቸውን ለማሻሻል ወይንም ለማደስ ብቻ ብዙ ነገሮችን ወይንም ዘዴዎችን ይጠቀማሉ ፡፡ እራሳቹን ለመፈወስ ማናቸውንም መንገዶች ልትጠቀሙ ትችላላችሁ የተጠቀማችሁት መንገድ ግን የውስጥን ብቻ ሳይሆን የላይኛውንም ገፅታችሁን እንደማይጎዳው እርግጠኛ ሁኑ፣የተጠቀማችሁት መንገድ ወደፊታችሁን እንዳያጠፋ፣ፈጣሪያችሁን እንዳያስከፋ እና የቅርብ ሰዎቻችሁን እንዳይጎዳ ተጠንቀቁ፣ በምትወስኑት ውሳኔ አንተን ወይንም አንቺን ሳይሆን በውስጣቹ ያለውን ችግር አድክሞ ሰቃያቹን እንደሚያጠፋላቹ ተስፋ አደርጋለሁ እናም የውስጥ ቁስላቹን ለማድረቅ፣የተሰበረውን ልባቹን ለመጠገንና ከህመሙ ለማገገም የወሰናችሁት ውሳኔ መፍትሄን የሚያመጣ እና በመጨረሻም ከችግሩ የሚገላግላቹን ነገር መርጣቹ ከእራሳቹ እስር ቤት መውጫውን እንደምታገኙ እና በስተመጨረሻ የእውነተኛ ደስታን ስሜት እንደምታጣጥሙት ተስፋ አደርጋለሁ፡፡
ኹሉድ
357 viewsÏküti ‿ , 16:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-25 20:44:32 እብዱ ደራሲ ክፍል ሁለት
በመغፊራ ቢንት ፉላን
....................
"ሲሁ ሲሀም ተነሺ እንጂ ስራ ረፍዷል፡ እንደ ቀልድ ሱብሂ በሰዐቱ መስገድ ተውሽ አይደል? እሺ አሁን ብድግ በይ ውሀ ሳልገለብጥብሽ"ብላኝ ወደ ኩሽናዋ ሄደች በጠዋት እንቅልፍ ማልደራደረው እኔ ስልኬን ከአጠገቤ ሳብ አድርጌ ሰዐቱን አየሁት ምክንያቱም ኡሚ ሁሌ ሱብሂ ልትቀሰቅቀኝ ስትፈልግ ስራ ረፍዷል ነው ምትለኝ እንዴት እንደምበሳጭባት! አንዴ ከተነሳው እንቅልፍ ስለማይወስደኝ በተነሳው ሰዐት ነው መስገድ ምፈልገው: እሷ ግን አትሰማኝም "ሱብሂ መስገድ ቀንሽን ሙሉ ደስተኛ እንድትሆኚ ያደርግሻል" ትለኛለች ለኔ ደስታ ሚሰጠኝ የጠዋት እንቅልፍ መሆኑ አይገባትም ግን ላለመጨቃጨቅ ስል"እሺ"እላታለው ኡሚ ግን እሺ ማለቴ የባሰ ያናድዳታል። "ሁሌ እሺ ብቻ እስኪ አንድ ቀን እንኳን ተግብረሽ አሳይኝ" ትለኛለች አሁን አሁንማ ሰለቻት መሰለኝ በስራ ሰዐት ነው ምትቀሰቅሰኝ ግን ምንም ቢሆን ከ12:40 አታሳልፈኝም ነበር፤ዛሬ ግን ረፍዷል ስልኬን ሳየው 1:05 ይላል ውሀ እንደተረጨ ሰው ብርድልብሴን ወርውሬ "ኡሚ ግን ምን ሆና ነው?እስካሁን ያልቀሰቀሰችኝ" እያልኩ እየተነጫነጭኩ ሻወር ለመውሰድ ወጣው።ትላንት ስዞር ስለዋልኩ እና አምሽቼ ስለተኛው ሰውነቴ ዛል ብሏል ሻወር ስወስድ ከለቀቀኝ ብዬ ቀዝቀዝ ባለ ውሀ ሻወር ወሰድኩ ግን ምንምን ስራ የመሄድ ሙዱ ሊመጣልኝ አልቻለም ግን ደሞ ግዴታ ነው!ለሰሙ አልነገርኳትም፤ ይህን እያሰብኩ ስልኬ ጠራ ሰሙ ነበረች
"እ አንቺ ጨራረሽ" አለችኝ "ምን አለ ደና አደርሽ ቢቀድም?" አልኳት "ትላንት አብረን መስሎኝ ያመሸነው በይ ነይ ውጪ እየደረስኩ ነው" ብላ ስልኩን ዘጋችብኝ "ምን አለ እንዳወራ እንኳን እድሉን ብትሰጠኝ ኡፍ ሰሙ ደሞ አሁን ደውዬ አልሄድም ብላት ራሱ ቤት መታ ለኡሚ አቃጥራ ታስወጣኛለች ከነሱጋር ከምንዛዛ ደሞ ብሄድ ይሻለኛል"ብዬ ልብሴን መልበስ ጀመርኩ "አንቺ ልጅ አረ ባክሽ ነይ ውጪ! ሻዩ ቀዘቀዘ እኮ አረ ምን ይሻልሻል በአላህ? ሰው አንድ ቀን እንኳን አያልፍለትም? ጓደኛዬ ትታዘበኛለች እንኳን አትይም እንዴ? አረ ተይ ሲሁ ቀልብ ግዢ ተይ"ኡሚ ምክሯን ልጀምር ነው። "ጨርሻለው ኮ ኡሚ ደሞ ቁርስ አልበላም፤አራበኝም" አልኳት ከክፍሌ ውስጥ ሆኜ፤ "አራበኝም ማለት ምን ማለት ነው? ከእንቅልፍሽ አደል እንዴ የተነሳሽው? ነይ ውጪ እና ቢ!"ቁጣ እና ትእዛዝ የተቀላቀለበት ድምፅ!መልስ ልሰጣት ስል የውጪው በር ተንኳኳ "ይሀው ጓደኛሽ መጣችልሽ ስትንከራፈፊ"ብላኝ በሩን ልትከፍት ወጣች "ኡፈይ አልሃምዱሊላህ ገላገልችኝ"ብዬ ቦርሳዬን አንጠልጥዬ ከክፍሌ ወጣው። ጫማዬን እየፈለኩ እንዳለ ኡሚ መጣች ከውሀላዋ ጓረቤታችን ወይዘሮ አኢሻ ተከትለዋት ገቡ። ፊታቸው ልክ አደለም መርዶ ነጋሪ ነበር ሚመስሉት፤ ኡሚም ተረብሻለች፤አጠገቧ እንደቆምኩ እንኳን አላስተዋለችም፤ "ደሞ ማን ሞተ አይ እኛ ሰፈር አዝራኤል አንዴ ከገባ ካልጠራረገን አይወጣም አደል?"እያልኩ እያሰብኩ ጫማዬን ለብሼ እንደጨረስኩ ሰሙ ደወለች "አረ አንቺ ሴትዬ ነይ ውጪ ያምሻል አ ሰዐት ኮ ረፍዶል ወላሂ ጥዬሽ ነው ምሄደው" ብላ ስልኩን ዘጋችው። እንደተበሳጨች ስለገባኝ ኡሚን "ደና ዋይ ብያት"ልወጣ ወደ ሳሎን ስገባ እሷም ከሳሎኑ ስትወጣ በር ላይ ተጋጨን ግን ትዝም አላልኳት! "ኡሚ ደና ዋይ በቃ ልሄድ ነው" ብዬ እንደለመድኩት ግንባሯን ልስማት ጠጋ ስል አይኖቿ እንደ ጉድ እንባን ያዘንባሉ፤በጣም ነበር የደነገጥኩት "ኡሚ ምንድነው የሆንሽው?ማነው የሞተው!ማን ምን ሆኖ ነው?" መልሷን አልጠበኩም ነበር "ምንም ምንም አደለም ልጄ ሂጂ በይ ወደ ስራሽ በጊዜ ተመለሺ የጊቢውን በር ቆልፈሽ ሱቅ አስቀምጪልኝ።" ብላ ጉንጪን ሳም አድርጋኝ ከቤት ወጣች ጨራርሼ ስለነበር ተከትያት ወጣው።"አይ የኔ ልጅ፣ የኔ የዋህ፣አይ ማሂርዬ" የሚሉ ከአንደበቷ የሚወጣ የለቅሶ ድምፅ ይሰማኛል። ጓረቤታችን እትዬ አይሻም "በልጅነቱ እንደዛ መሆኑ ሳያንስ አይይይ የሰው ልጅ መከራ እናቱ ምን ትል ይሁን አይይ ማሂር" እያሉ ከኡሚ ጋር ተከታትለው ከጊቢ ወጡ.....
ክፍል ሶስት ይቀጥላል .......
351 viewsÏküti ‿ , 17:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-24 20:54:50
367 viewsMadih ibnu ahamed , 17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-23 19:50:52 እብዱ ደራሲ ክፍል አንድ
በመغፊራ ቢንት ፉላን
...........
ለመኖርም ለመሞትም አልታደለም በመኖር ውስጥ የሞተ፣ ሞተ እየተባለ የኖረ፣ ምስኪን ፍጡር ነው።የማያውቁት ሰዎች ከሩቅ ሲያዩት በፍርሀት ልባቸው ጥለው ይሮጣሉ ከፊሉ መንገድ ይቀይራል፣ከፊሉ በፍርሀት ይጨማደዳል፣ የሚያውቁት ደሞ ከፊሉ እያዘነለት፣ ከፊሉ እያዘነበት፣ በአጠገቡ ማለፍ ሳይሳቀቅ፣ እንዳላወቁት ሳይደነግጥ በአጠገቡ ያልፋሉ።ሁሌ ከእጁ ላይ የማትለየዋ ቡኒ ተስቢህ የማሂር መታወቂያ ነች ሲቀመጥ ሲነሳ ሲተኛ ሲበላ ሁሌም እጁ ላይ አለች። ሲዞር ሳንቲም ሲለቅም ይውል እና የሰፈሩ ወጣቶች በሸራ እና በማዳበሪያ የሰሩለት ቤት ውስጥ ሄዶ ይተኛል። የተቦጫጨቀ ልብሱ እላዩ ላይ ሊያልቅ ትንሽ ቀርቶታል ከማይታየው የሰውነት ክፍሉ የሚታየው ይበዛል ያለፈ ያገደመውን ሳንቲም ይጠይቃል። ግማሹ በሀዘኔታ,ግማሹ ብከለክለው ይመታኝ ይሁን በሚል ፍራቻ, ይሰጡታል። አንድአንድም አለ ሂድ ከዚ! ብሎ ቀልቡን ገፎ የሚያባርረው፧ ለነገሩ ማሂር ቀልብ የለውም! ቀልብ ቢኖረውማ የተቦጫጨቀ ልብሱን በቀየረ፤መንገድ ማደሩን ትቶ ወደቤቱ በገባ፤ ግን የት ነው ቤቱ? ከየትስ ነው የመጣው? ለምንድነው አብዛኛውን ጊዜ እዚህ ሰፈር የሚኖረው? እንደዚ ሲሆን ጠያቂ የለውም? ና ልጄ ብላ የምትሰበስብ እናት ወይ የሚሰበስብ አባት የለውም? ቤተሰቦቹስ? ዘመዶቹስ? የማን ልጅ ነው? ወደ ሰፈሩ የመጣ አዲስ ነዋሪ ፤ለእንግድነት የመጣ ሳይቀር የሚጠይቀው ጥያቄ ነው፤ግን መልስ የለም። ማሂር እዚ መንደር መቶ መዋል ማደር ከጀመረ አምስት አመታትን አስቆጥሯል አንዳንዴ ለተወሰኑ ቀናት ከመንደሩ ይጠፋል ግን እሰይ ተገላገልን የሚለው የለም፡፡ሁሌም አንድሳምንት ቆይቶ ይመጣል የት ይሂድ?ለምን ይሂድ? የሚያውቅ የለም! የመንደሩ ሰው እንደጎረቤቱ ለምዶታል፧ከአይናቸው ሲጠፋ ባይፈልጉትም ይጠይቃሉ የት ሄዶ ይሆን?ብለው ይጨነቃሉ! መኪና ገጭቶት ይሆን? እብድ ነው ብለው ቀጥቅጠውት ይሆን? ማሂር እኮ ግን እብድ አደለም! ሰው አይናካም የጫት ሱስ የለበትም ሰው አያሰቸግርም አይጮህም እንደ እብድ አይለፈልፍም! ትልቅ ሰው ይወዳል እቃ ተሸክመው ካየ ተቀብሏቸው የሚፈልጉበት ቦታ ያደርስላቸዋል። አሁን አሁንማ እነሱም ና እስቲ የኔ ልጅ ይሄን እቃ አድርስ!እያሉ ይልኩት ጀምረዋል። እንቢ አያውቅም አንገቱን እንዳቀረቀረ የተባለበት ቦታ ያደርሳል። የሰፈሩ ጎረምሶች እብዱ ደራሲ ይሉታል ያገኘው ነገር ላይ ይፅፋል ለሰው የማይገባ ለሱ እረፍት የሚሰጠው አይነት ፁሁፍ ወጣቶቹ ይወዱታል እሱም ሳንቲም እንዲሰጡት ስለሚፈልግ ሲያዙት ይታዘዛል እነሱም እጃቸው ለሱ ይዘረጋል ደሞ ብር አይቀበልም ሳንቲም ብቻ፤ ለሊት በሱ አጠገብ ያለፈ ሰው ሳንቲም ሲቆጥር ማየት የተለመደ ነገር ሆኗል፡ምን እንደሚያደርግበት ባያውቁም ይሰጡታል እሱም ይሰበስባል። ህፃናት የሚጫወቱበት ቦታ ላይ አይጠፋም አንድሰሞን ሲመጣ እየፈሩ ይሮጡ ነበር አሁን ይቀርቡት ጀምረዋል አንዳንዴ አብሯቸው ይጫወታል ያጫውታቸዋል አብሯቸው ይስቃል በሳቁ ውስጥ ግን ሁሌም እንባ አለ ቶሎ የማይደርቅ እንባ ሀዘን ስብራት እንዳዘለች የምታስታውቅ እንባ ያነባል ተስፋ የቆረጠ ናፍቆት ያጠቃው ብቸኝነት ያጎሳቆለው ሰው የሚያፈሰውን እንባ እንደጎረፍ ያዘንበዋል ማልቀስ ከጀመረ አያቆምም ግን እሱ እየሳቀ ነው ሚያለቅሰው! ሳቁ ደሞ ከጣራ በላይ ይሰማል፤ ሰዎች ሲያለቅሱ ደሞ ይስቃል፤ ሰፈር ውስጥ ለቅሶ ካለ እዛ ከአካባቢ አይጠፋም ሰዎች በሀዘን እንባቸውን ሲያወርዱ እሱ ግን በደስታ በሚመስል መልኩ ይስቃል በደስታ እንደሚቦርቅ ህፃን ይፈነድቃል እንግድነት ለመጣው ሰው አዲስ ነገር ቢሆንም መንደሩ ግን ይሄን ለምዶታል እና ተውት እብድ ነው ይባላል ።ሰዎች እብድ ነው የሚሉት እቤታቸው አስገብተው ሊያኖሩት የሚፈሩት ዋናው ምክንያታቸው ይሄ ነው። ዛሬ ግን ማሂር የለም እናቶች እንደህፃን የሚልኩት ህፃናቶች የጨዋታ ማድመቂያቸው ወጣቶቹን ሳንቲም እያለ የሚለምናቸው የፈለጉት ቦታ የሚልኩት ማሂር ዛሬ ቦታው የለም። እንደለመደው አንድ ሳምንት ቆይቶ ይመጣል ብሎ ሁሉም እየጠበቀ ነው። እሱ ግን የለም እናት ልጇ ወቶ እንደቀረባት ልጅ ከስራ ሲመጣ ብስኩት ገዝቶ እንደሚያመጣለት አባት ደጅ ደጁን እያዩ ነው አረ ባካቹ እብዱ ደራሲ እኮ ከጠፋ ሳምንት አለፈው እያሉ የወንድማቸውን ያህል የሚጨነቁለት ጎረምሶቹ ፍለጋቸውን ቀጥለዋል።ማሂር ግን የለም ........
ክፍል ሁለት ይቀጥላል.....
392 viewsÏküti ‿ , 16:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ