Get Mystery Box with random crypto!

የአህዛብና የመናፍቃን ጥያቄዎችና መልሶቻቸው!!

የቴሌግራም ቻናል አርማ kidestaresema — የአህዛብና የመናፍቃን ጥያቄዎችና መልሶቻቸው!!
የቴሌግራም ቻናል አርማ kidestaresema — የአህዛብና የመናፍቃን ጥያቄዎችና መልሶቻቸው!!
የሰርጥ አድራሻ: @kidestaresema
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.52K
የሰርጥ መግለጫ

☞ በዚህ ቻናላችን የተለያዩ መንፈሳዊ ትምህርቶችን በቤተክርስቲያናችን የሚነሱ ጥያቄዎች በመናፍቃን በአህዛብ የሚጠየቁትን በአጠቃላይ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ላይ የሚነሱትን ጥያቄዎች የማያዳግም መልስ መልሰን ለኦርቶዶክሳውያንና ለህዝቡ መልስ የምንሰጥ ይሆናል! #join & #share
ለግሩፕ 👉 @kidestaresema6
ለቻናል 👉 @kidestaresema
ለማንኛውም ጥያቄ 👉 @tiotokos_bot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-04-30 10:54:52 ሮ አዳምን እንዳሳተው ሁሉ ክርስቶስም ደካማውን የአዳምን ሥጋ ለብሶ በደካማነቱ ቢጠጋው ድል እንደነሳው ለማስተማር ነው።

፪. “አባ ሥረይ ሎሙ እስመ በዘኢየአምሩ ይገብሩ” (አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው) ሉቃ ፳፫፡፳፬ ጌታችን ይህንን ማለቱ የበደሉንን ይቅር ማለትን ሲያስተምር እና ከስቅለቱ ሳያውቁ የተሳተፉም ስለነበሩ እና አሉና እነሱን ከስቅለቱ ሲለይ ይህንን ተናገረ።

፫. “ዮም ትሄሉ ምስሌየ ወስተ ገነት” (ዛሬ በገነት ከእኔ ጋር ትኖራለህ) ሉቃ ፳፫፡፴፫ ይህንንም የተናገረው በቀኙ የተሰቀለው ወንበዴ የጌታችንን የባህርይ አምላክነት አምኖ “በመንግስትህ አስበኝ” ቢለው እሱም ከሁሉ ቀድሞ ገነት የመግባት እድልን ሲያጎናጽፈው ነው።

፬. “አባ አመሐፅን ነፍስየ ውስተ እዴከ” (አባት ሆይ ነፍሴን በ እጅህ አደራ እሰጣለሁ) ሉቃ ፳፫፡፵፮

፭. “ነዋ ወልድኪ ነያ እምከ” (እነሆ ልጅሽ እነኋት እናትህ) ዮሐ ፲፱፡፳፮-፳፯ በዚህም ጌታችን ለደቀ መዝሙሩ እመቤታችንን እናት አድርጎ ሲሰጠው ለሁላችንም እናት እንድትሆነን መስጠቱን ሲያጠይቅ ነው።

፮. “ከመ ይብጻሕ ቃለ መጽሐፍ ዘይቤ ጻማዕኩ” (መጽሐፍ በመብሌ ውስጥ ሐሞት ጨመሩበት) መዝ ፷፰፡፳፩ ይህም የመጽሐፉ ቃል ይፈጸም ዘንድ ተጠማሁ አለ። የሰቀሉትም መራራ ሀሞትን እና ኮምጣጤን ይጠጣ ዘንድ ሰጡት ዮሐ ፲፱፡፳፰።

፯. “ወይቤ ተፈጸመ ኩሉ” የተነገረው ተስፋ የመሰለው ምሳሌ የተተነበየው ትንቢት ደረሰ ተፈጸመ ሲል ተፈጸመ አለ። ዮሐ ፲፱፡፴።
ከዚህ በኋላ ቅድስት ነፍሱ ከቅዱስ ሥጋው ስትለይ አምላክነቱን ለመግለጽ በምድር አራት በሰማይ ሦስት ተአምራት ታይተዋል ፡፡
እነርሱም የሚከተሉት ናቸው፦

በምድር
፩-የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ተቀደደ፣
፪-ምድር ተናወጠች፣
፫-አለቶች ተሰነጣጠቁ፣
፬-መቃብሮች ተከፈቱ ፣ ሙታን ተነሱ። ማቴ27፤51-53
በሰማይ
፩- ፀሐይ ጨለመች፣
፪-ጨረቃም ደም ሆነች፣
፫-ከዋክብት እረገፉ። ማቴ ፳፯፡፴፭
አስራ አንድ ሰዓት ጌታ ወደ መቃብር ወረደ ተቀበረ ጌታን የሰቀሉት አይሁድ የፋሲካ በዓላቸው ቀርቦ ነበር እና ሥጋቸው በመስቀል እንዳይውል የሰቀሏቸውን ሰዎች ጭናቸው ተሰብሮ እንዲሞቱ ጲላጦስን ለመኑት እርሱም ፈቀደላቸው። ጌታን ሊሰብሩት ሲመጡ ሞቶ አገኙት በዚህ ጊዜ ሌንጊኖስ የሚባል ወታደር መሞቱን ሊያጣራ ጎኑን በጦር ቢወጋው ከጎኑ ደምና ውሃ ፈሰሰ ይህም የምንጠመቅበት ማየ ገቦ ነው። በሥውር የጌታ ተማሪ የሆኑት የአርማትያሱ ዮሴፍና የአይሁድ አለቃ ኒቆዲሞስ ጲላጦስን ለምነው በማስፈቀድ እንደ አይሁድ የአገናነዝ ሥርዓት የጌታን ሥጋ በሽቶ ጋር በተልባ እግር አልብሰው “ቅዱስ እግዚአብሔር ቅዱስ ኃያል ቅዱስ ሕያው ዘኢይመውት” እያሉ ገንዘው ማንም ባልተቀበረበት አዲስ መቃበር ቀበሩት። ምነው ቅዱሳን ነቢያት ባረፉበት መቃበር ያልተቀበረ ቢባል ኋላ በትንሳኤው ሲነሳ የነቢያት አጽም አስነሳው (ለምሳሌ ያህል የነቢዩ ኤልሳዕ አጥንት ሙት አስነስቷል ፪ ነገሥ ፲፫፡፳፩) እንጂ መቼ በሥልጣኑ ተነሳ ብለው አይሁድ ይሞግቱ ነበር እና እንዲያ እንዳይሉ በአዲስ መቃበር ተቀበረ። ማቴ ፳፯፡፶፯-፷፩ ፤ ማር ፲፭፡፵፪-፵፯ ፤ ሉቃ ፳፫፡፶-፶፮ ፤ ዮሐ ፲፱፡፴፪-፵።
በዕለተ ስቅለት በጸሎታችን ወቅት ሲባል እንደሰማችሁት “ኦ ዘጥዕመ ሞተ በሥጋ” ሞትን በሥጋው ቀመሰ። የማይሞተው ሞተ። በቀራንዮ የተከፈለልንን ዋጋ እያሰብን እንደቃሉ እንኖር ዘንድ፣ ከበደል እና ከኃጢአት ተጠብቀን በንስሐ ነጽተን፣ በቅዱስ ሥጋው እና ክቡር ደሙ ዘለዓለማዊ ሕይወትን እናገኝ ዘንድ ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን።
4.6K viewstheotokos (የአምላክ እናት), 07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-30 10:54:52 ዕለተ አርብ

ዓርብ ነግህ(ከጠዋቱ አስራ ሁለት ሰዓት)ጌታ ለፍርድ ቀረበ

የዓለሙ ሁሉ ፈጣሪ የዓለሙ ፈራጅ እውነተኛው ዳኛ ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ በሐሰት ተከሶ ለፍርድ በጲላጦስ አደባባይ ችሎት ቆመ። ጲላጦስም ጌታን መርምሮ ለሞት የሚያበቃ አንዳች ጥፋት ቢያጣበት ሊፈታው ፈለገ። ከሳሾቹ ግን ጌታን ስቀለው ወንጀለኛውን በርባንን ፍታልን ብለው ጮሁ። የጲላጦስ ሚስት የነበረችው አብሮቅላ ግን በህልም ብዙ መከራ እና ስትቀበል ስታይ አድራለችና ለባሏ በዚህ ሰው ላይ አንዳች ክፉ ነገር እንዳታደርግ ብላ መልዕክት ለባሏ ላከችበት። በፈራጅነት የተቀመጠው ጲላጦስም ክርስቶስ የገሊላ ሰው መሆኑን ሲረዳ ጌታችንን በጊዜው የገሊላ ገዥ ወደ ሆነው ሄሮድስ እንዲሄድ አደረገው። ጲላጦስና ሄሮድስ በሥልጣን ዘመናቸው እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ፣ እኔ ልግዛ እኔ ልግዛ እያሉ በዳኝነት ይጣሉ ነበር አሁን ግን በጌታ ሞት የተነሳ ሁለቱ የሥልጣን ጥመኛ ጠላቶች ታረቁ። ሄሮድስም ጌታን ወደ ጲላጦስ መልሶ ሰደደው። ለእስራኤላውያን የፋሲካ በዓል ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበት መታሰቢያ ነውና በየዓመቱ የሚፈልጉትን እስረኛ ሊፈታላቸው ልማድ ስለነበራቸው በርባን የተባለውን ወንበዴ እንዲፈታላቸው ጠየቁት እርሱ ግን ኢየሱስን ልፍታላችሁ ወይስ በርባንን ቢላቸው ወንበዴዎን በርባንን መረጡ። ወንበዴው በርባን ከእስር ተፈትቶ ንፁሁ ጌታ ታስሮ ለሞት መዳረጉ ጌታ ስለበደለኞች ስለኃጢአተኞች ሊሞት እና የነሱ እጣ የሆነውን ቅጣት እና መከራ ሊቀበል የመጣ መሆኑን የሚያጠይቅ ነው። (ማቴ ፳፯፡ ፩-፲ ማር ፲፭፡፩-፭ ፤ ሉቃ ፳፫፡ ፩-፶፮ ዮሐ ፲፰፡ ፳፰-፴፰)

ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጌታ ተገረፈ

ጲላጦስም ጌታን መርምሮ አንዳችም ለሞት የሚያበቃ በደል አላገኘበትም። እሱም ሊፈታው ፈለገ ህዝቡ ግን “ስቀለው ስቀለው” እያሉ አብዝተው ጮሁ። ጲላጦስም ምናልባት ቢገረፍ እሱ ይበቃዋል ብለው ይገደል የሚለውን ጥያቄያቸው ይተዋሉ ብሎ በማሰብ ለመገረፍ አሳልፎ ሰጠው። በልማዳቸው የተገረፈ አይሰቀልም እና። እነርሱ ግን ልባቸው በጭካኔ የደነደነ ነበር እና እየተፈራረቁ ክንዳቸው እስኪዝል ድረስ አርባ ብቻ ሊገረፍ የተፈረደበትን ቁጥር ያሳሳቱ በማስመሰል ሥጋው አልቆ አጥንቱ እስኪታይ ድረስ ስድስት ሺህ ስድሥት መቶ ስልሳ ስድስት (፮፼፮፻፷፮) ጊዜ ገረፉት። ጌታ እንዲሰቀል የህዝቡ ጩኸት በበረታ ጊዜም ጲላጦስ ከዘመኑ ንጉስ ከቄሳር ጋር እንዳያጣሉት ለሥልጣኑ በመስጋት እኔ ከደሙ ንጹህ ነኝ ብሎ በውሃ እጁን ታጠበና ጌታን እንዲሰቅሉት አሳልፎ ሰጣቸው።(ማቴ ፳፯፡፳፬-፳፮ ፤ ማር ፲፭፡፮-፲፭ ፤ ሉቃ ፳፫፡፩-፳፮ ፤ ዮሐ ፲፰፡፳፰-፴፰)።

እኩለ ቀን - ከቀኑ ስድስት ሰዓት ጌታ ተሰቀለ

ለዝንተ ዓለም መላእክት፣ ሊቃነ መላእክት፣ ሱራፌል እና ኪሩቤል ሳያቋርጡ ምስጋና የሚያቀርቡለት ንጉሥ የክፉዎች አይሁድ መዘበቻ ሆነ። ቅዱሳን መላእክት በፍርሐት የሚሰግዱለትን ጌታ በመቃን ራሱን መቱት። መጀመሪያ ለመዘባበት ሲሉ ያለበሱትን ቀይ ግምጃ ገፈው አውልቀው ወደሚሰቅሉበት ቀራንዮ ተራራ ከባድ እጸ መስቀል አሸክመው እያዳፉ ወሰዱት። ከባዱን ዕፀ መስቀል መሸከሙ ከባዱን ኃጢአታችንን እንደተሸከመልን የሚያጠይቅ ነው ቅዱስ ጴጥሮስ “ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ” እንዳለ ፩ኛ ጴጥ ፪፡፳፪።
ስምዖን የተባለውን የቀሬና ሰው በመንገድ አገኙትና የጌታን መስቀል ይሸከም ዘንድ አስገደዱት (ማቴ ፳፯፡፴፪)። የስምዖን መሸከም ግን ጌታ ከመስቀሉ በረከት እንዲሳተፍ ስለፈለገ ነው።
ጌታን ወንበዴ ነው ብለው ስሙን ለማጥፋት እንዲመቻቸው በሰው አመለካከትም ወንበዴውን ነው የሰቀሉት እንዲባል ስለፈለጉ ንፁሁን ሥጋን የተዋሐደ አምላክ በሁለት ወንጀለኛ ወንበዴዎች መካከል እንዲሰቀል አደረጉት። ነቢዩ ኢሳይያስ በትንቢቱ “ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፤ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥” (ኢሳ ፶፫፡፲፬) ያለው ይፈጸም ዘንድም ጌታ በፈያታዊ ዘየማን እና በፈያታዊ ዘጸጋም መካከል ተሰቀለ።
ጌታችን በፍጹም ያፈቀረውን የሰውን ልጅ ከመራራው የኃጢአት ሞት ሊያድነው ፍቅር አስገድዶት መጥቷልና ዕጸ በለስ ለመብላት የተዘረጉ የአዳም እጆችን ወደ እጸበለስ የገሰገሱ የአዳም እግሮችን ለመቤዠት ሲል እጆቹን እና እግሮቹን በችንካር ተቸነከረ። የበለስ ፍሬን በመብላት አዳም የተጎነጨውን መራር ሞት ለማጠየቅ ጌታ ውሃ ጠማኝ ብሎ ቢጠይቅ የሰጡትን መራር ሆምጣጤ እና ሀሞት ቀመሰ።
ጲላጦስም አይሁድ በቅንዓት ለሞት አሳልፈው ጌታን እንደሰጡት ያውቅ ነበር እና “ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው” የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ በሦስት ቋንቋ በጽርዕ (ግሪክ) ፣ በዕብራይስጥ ፣ በሮማይስጥ በመጻፍ እንዲቀመጥ አስደረገ። ማቴ ፳፮፡፴፯ ፤ ማር ፲፭፡፳፯ ፤ ሉቃ ፳፫፡፴፰ ፤ ዮሐ ፲፱፡፲፱-፳፪።

ዘጠኝ ሰዓት ጌታ በፈቃዱ ነፍሱን ከሥጋው ለየ - ሞተ

ጌታችን አምላካችን እና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አስራ ሦስት ሕማማተ መስቀልን ከተቀበለ በኋላ የሰው ልጅ ባለመታዘዝ ያጣውን ሕይወት በሞቱ ለመካስ መራራ ሞትን በፈቃዱ ተቀበለ። ነቢዩ በኢሳይያስ “የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል? በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም። የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም። በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ። ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም። በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገኘበትም ነበር።” የተባለው ይፈጸም ዘንድ (ኢሳ ፶፫፡፩-፱) ይህ ሆነ። ጌታም “መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።” (ዮሐ ፲፡፲፬-፲፭) ያለው ፈጸም ዘንድ ስለበጎቹ መልካም እረኛ ነፍሱን ሰጠ በሞቱ ሞታችንን ለወጠ። ጌታም ነፍሱን ከሥጋው በፈቃዱ ሲለይ “አባት ሆይ፥ ነፍሴን በእጅህ አደራ እሰጣለሁ አለ።”” ይህንንም ብሎ ጌታ በፈቃዱ የሞት ጽዋን ጠጣ።
ጌታችንም ነፍሱ አሳልፎ ከመስጠቱ አስቀድሞ ሰባቱን አጽርሐ መስቀል ተናግሯል። ሰባቱ አጽርሐ መስቀል ወይንም ሰባቱ በመስቀል ላይ የተናገራቸው ከዚህ የተከተሉት ናቸው፡

፩. “ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ” (አምላኬ ለምን ተውኸኝ) ማቴ ፳፯፡፴፮ ጌታችን እንዲህ ማለቱ እርሱ ደካማ ስለሆነ ወይንም በደካማነት ወይም መለኮት ስለተለየው ሳይሆን ለኛ አብነት ይሆነን ዘንድ መከራ ሲገጥመን ምን ብለን መለመን፣ መማጸን፣ መጸለይ እንዳለብን ለማስተማር ነው። አንድም ጠላት ዲያብሎስ በአካለ ከይሲ ተሰው
4.5K viewstheotokos (የአምላክ እናት), edited  07:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-29 11:16:06
3.2K viewsMicky, 08:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-29 11:10:09
3.9K viewsMicky, 08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-29 11:10:00
3.0K viewsMicky, 08:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-29 11:09:51
3.0K viewsMicky, 08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-29 11:09:42
2.9K viewsMicky, 08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-29 11:09:41 #ሐሙስ

#በግዝት_በዓል_መስገድ_ይችላል??

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዕለት ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ መሆኑን ለመግለጥ እና ለአርአያነት ጸሐፍት ፈሪሳውያን የአይሁድ ካህናት መጥተው እስኪይዙት ድረስ ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ጸሎተ ሐሙስ በመባል ይታወቃል፡፡

ትሕትና ፍቅር መታዘዝ እንዲሁም የአገልግሎትን ትርጉም ለማስረዳትና ለማስገንዘብ የደቀ መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ሕጽበተ ሐሙስ በመባልም እንደሚጠራ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይናገራሉ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስም «ወሶበ ኀፀቦሙ እገሪሆሙ ነሥአ አልባሲሁ ወረፈቀ ካዕበ ወይቤሎሙ አእመርክሙኑ ዘገበርኩ ለክሙ … ወሶበ አነ እንከ ሊቅክሙ ወእግዚእክሙ ኀፀብኩክሙ እገሪክሙ ከማሁኬ አንትሙኒ ይደልወክሙ ትኅፅቡ እግረ ቢጽክሙ፡፡»፤ «እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ እንዲህም አላቸው ያደረግሁላችሁን ታስተውሉታላችሁን?… እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ እናንተ ደግሞ እርስ በእርሳችሁ ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል ሲል ተናግሯል፡፡ /ዮሐ.13-12-20/፡፡

ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ሥጋዬ ነው እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚፈስ ደሜ ነው ከእርሱ ጠጡ በማለት ምሥጢረ ቁርባንን የመሠረተበት ወይም ራሱ ምስጢረ ቁርባንን የጀመረበት ቀን በመሆኑ የምስጢር ቀን ተብሎ ይጠራል፡፡

ይኸውም የሰው ልጆች ሥጋውንና ደሙን ተቀብለን ከእርሱ ጋር አንድነትና ኅብረት እንዲኖረን ጥንተ ጠላት ዲለብሎስንም ፍጹም ድል ነሥተን ሰማያዊት ርስት መንግሥተ ሰማያትን እንድንወርስ ለማስቻል ነው፡፡ /ማቴ.26-26-29/፡፡ አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ በእነርሱ ጥበብና ፍላጐት ቀስ ብለው መጥተው የያዙበት ቀን ስለሆነ በዚህ ዕለት በለሆሳስ /ብዙ የድምጽ ጩኸት ሳይሰማ/ የቅዳሴ ሥርዓት ይፈጸማል፡፡

ሆኖም በአንዳንድ ሰዎች የሚነሳ ጥያቄ አለ። በግዝት በዓላት ላይ ሕማማት ቢውል ይሰገዳል ወይንስ አይሰገድም ተብሎ ይጠየቃል። በተለይ አሁን በሐሙስ እለት የእመቤታችን በዓል ይውላል። ከዚህም ጋር ተያይዞ የግዝት በዓል ስለሆነ አይሰገድም የሚሉ አሉ።

ይህ ፈጽሞ ስህተት ነው። የበዓሉን ዓላማ ካለማወቅ በዓሉ ምን እንደሆነ ካለማወቅ የመጣ ስለሆነ አይሰገድም ተብሎ መወራቱ ስህተት ነው።

እንደማጣቀሻ ይሁነን ዘንድ የግዝት በዓላት የምንላቸው እለተ እሁድ እለተ ቅዳሜ የሚካኤል በዓል(12) የእመቤታችን በዓል(21) በዓለ እግዚአብሔር(29) እነዚህ የግዝት በዓላት ተብለው በቤተክርስቲያናችን ይጠራሉ።

በእሁድና በቅዳሜ አይሰገድም ነገር ግን የሚሰገድበትም ጊዜ አለ። በፍትሐ ነገስት አንቀጽ 19 ላይ አይሰገድም ካለ ቡኋላ ይህ ያልተወገዘበት አንቀጽ ነው ብሎ ይናገራል። ይህ ማለት የሚሰግድበት እሁድ አለ ማለት ነው የሚሰገድበት እሁድ መቼ ነው ከተባለ ሀጢያት በሰለጠነበት ሰዓት ዕለተ ሰንበት ቢሆን ይሰገዳል ማለት ነው።


ወደ ሕማማቱ ስንመለስ በመጀመሪያ ልናውቅ የሚገባን ነገር በዓሉ የስግደት በዓል መሆኑን መርሳት የለብንም። ዕለቱ ራሱ የስግደት በዓል ነው ከዐበይት በዓላት አንዱ ስቅለት ነው በዓበይት በዓላት ደግሞ መስገድ ወይንም ማዘን አይፈቀድም ይቺ ዕለተ ስቅለቷ ግን ትሰገድበታለች ምክንያቱም ዕለቱ የስግደት በዓል ስለሆነ ማለት ነው።

በሁለተኛ ደረጃነት ደግሞ በዚህ በሰሙነ ሕማማት የምንፈጽመው ስግደት የአምልኮ ስግደት ነው። የአምልኮ ስግደት በቤተክርስቲያናችን በ365 ቀን ውስጥ ይሰገዳል። ግዝት በዓል አያግደውም ስለዚህ የአምልኮ ስግደት ስለሚፈቀድ በሕማማቱም ያንኑ ነው የምንሰግደው ማለት ነው።

የሶስተኛ ደረጃ በዚህ በሰሙነ ሕማማት የእመቤታችን በዓል ራሱ መዋሉ በዚህ ሳምንት የደረሰባትን መከራና ስቃይ እንግልት አስበን አንዴ እየተነሳች እንዴ እየፈረጠች አምርራ ያለቀሰችበትን አስበን ይበልጥ የምንሰግድበት ነው።

ስለዚህ በሰሙነ ሕማማት ከጌታ ሕማም የበለጠ ሕማሙን የሚያሽር ምንም የግዝት በዓል የለም!!!!!!!!!!!

እንበለ ደዌ ወህማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሃነ ያብጽህክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ በፍስሃ ወበሰላም አሜን።

#ሼር_በማድረግ_ለሌሎች_ያካፍሉ!!!

@kidestaresema
@kidestaresema
@kidestaresema
4.5K viewsMicky, 08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-28 17:10:23
2.8K viewstheotokos (የአምላክ እናት), 14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-04-28 17:10:23 ክፉ ምክር

#ዕለተ #ረቡዕ

እንበለ ደዌ ወህማም እንበለ ፃማ ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሃነ ያብጽህክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ በፍስሃ ወበሰላም አሜን።

አይሁድ በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ የሞት ፍርድ ለመፍረድ የመጨረሻውን ምክር ያደረጉት ረቡዕ እንደ ሆነ በቅዱስ መጽሐፍ ተጽፏል። ይሁን እንጅ ከዚያም በፊት በተለያዩ ጊዜያት በእርሱ ላይ ምን እንደሚያደርጉ ሲማከሩ ነበር።

በህዝቡ ፊት ያደርገው የነበረው መልካም ነገር ምክንያት አሳጥቷቸው እንጅ ሊይዙት ሲፈልጉ ቆይተዋል። የአይሁድ ክፉ ምክርና ጥላቻ ከቅንዓት የመጣ እንደሆነ እስከ ሀገረ ገዥው ጲላጦስ ድረስ የታወቀ ነበር።በዚህም ምክንያት ለሞት አሳልፎ ላለመስጠት ብዙ ሞክሯል። ይሁን እንጅ የእነሱን ፈቃድ ለመፈጸም ሲል እያወቀ አሳልፎ ሰጥቷቸዋል። ትልቁ በደል እንኳን ለሞት የሚያበቃ ለክስ የሚሆን መረጃ እንደሌላቸው እያወቀ ሁከት ስላበዙ እራሱን ነጻ ለማድረግ እጁን ታጥቦ ጌታን ግን አሳልፎ ሰጥቷቸዋል።


እሥራኤላውያን በዘመኑ በሮም ቅኝ ግዛት ስር የነበሩ ቢሆንም ነገር ግን የኦሪትን ህግ ምክንያት በማድረግ እንደ ህጋቸው ይፈርዱ ነበር። ለዚያ ነው ጲላጦስ መርምሮ ምንም ወንጀል ስላላገኘበት እንደ ህጋችሁ ፍረዱበት ብሎ የሰጣቸው። እስራኤል ዘሥጋ ከቀድሞ ጀምሮ ያላቸውን ታሪክ ስንመለከት ወንድማቸው ዮሴፍን በቅንአት ተነሳስተው ሊገድሉት ተማክረው ነበር።


ነገር ግን የእግዚአብሔር ቸርነት ጠብቆት ከእነሱ አንዱ ሮቤል የተባለው ትልቁ ወንድማቸው ከምንገድለው እንሽጠው የሚል ሃሳብ በማቅረቡ ለግብጻውያን ነጋዴዎች ሸጠውታል። ለመግደል ምክንያታቸው ዮሴፍ ቅንና የዋህ ሰው በመሆኑ እግዚአብሔር ወደፊት የሚሆነውን በህልም አሳይቶት ነበር። አባቱም የዋህነቱንና ቅንነቱን አይቶ መክሮት ነበር። ወንድሞቹ በምድረ በዳ እንስሶችን ሲጠብቁ ሳሉ የሚበሉትና የሚጠጡት ይዞ በብዙ ድካም ወደ እነሱ ሲቀርብ ያለ ርህራሄ ከጉድጓድ ውስጥ ነበር የጨመሩት ለአባታቸውም አውሬ በላው ብለው በደም የተለወሰ ልብሱን አምጥተው ሰጥተውታል። "እነርሱም በሩቅ ሳለ አዩት፥ ወደ እነርሱም ገና ሳይቀርብ ይገድሉት ዘንድ በእርሱ ላይ ተማከሩ። አንዱም ለአንዱ እንዲህ አለው። ያ ባለ ሕልም ይኸው መጣ። አሁንም ኑ፥ እንግደለውና በአንድ ጕድጓድ ውስጥ እንጣለው። ክፉ አውሬም በላው እንላለን፤ ከሕልሞቹም የሚሆነውን እናያለን። ዘፍ 37፥18"


ዮሴፍ ገና በልጅነቱ ወደማያውቀው ሀገር በመሸጡ የሚወደውን አባቱን እንዲሁም ወገኖቹን ለመፈለግ አልቻለም። ነገር ግን እግዚአብሔር ሁልጊዜም ከቅኖች ጋር ነውና ከብዙ ችግር ጠብቆት የንጉሥ ታማኝ አገልጋይና በኋላም ባለሟል ለመሆን ችሏል። ወንድሞቹም በሀገራቸው ረሀብ ስለጸና ወደ ምድረ ግብጽ እህል ፍለጋ ሄደዋል። እነሱ ባያውቁትም እሱ ግን አወቃቸው። ያለፈውን በደላቸውን ይቅር ብሎ የሚያስፈልጋቸውን ሁሉ አድርጎላቸዋል። ከዮሴፍ ሞት በኋላም የዮሴፍን መልካምነት የማያውቅ ፈርዖን በግብጽ በመነሳቱ መከራቸው እጅግ በመብዛቱ ምክንያት ሁልጊዜም የአባቶቻቸውን ቃል ኪዳን የማይረሳው አምላክ ሙሴን አስነስቶ ከግብጽ ባርነት ነፃ አውጥቷቸዋል።


አስቀድሞ ለአብርሃም በገባው ቃልኪዳን መሰረትም ከነዓን ወደተባለችው ምድር ገብተዋል። ይሁን እንጅ በመንገድ እያገለገሉ ይመሩዋቸው የነበሩትን ሙሴና አሮንን ሊገድሏቸው የተነሱበት ጊዜም ነበር። "፤ ማኅበሩ ሁሉ ግን በድንጋይ ይወግሩአቸው ዘንድ ተማከሩ" (ኦሪት ዘኍልቍ 14: 10)


ነቢየ እግዚአብሔር ኢሳይያስ "፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው። " (ኢሳ 53: 4) ብሎ እንደተናገረው በጌታ ላይ የደረሰውን መከራና ስቃይ ስናስብ አይሁድ ባይሆኑ ማን ሊፈጽመው ይችላል? ለምን ወደ እነሱ መጣ? ስንልም አስቀድሞ ያወቃቸው በመሆኑ እራሱን አሳልፎ ለእነሱ ሰጠ ብንል አይፈረድብንም።
ጌታ አምላክነቱን ገልጦ ልዩ ልዩ ተአምራት ማድረግ ከጀመረ አንስቶ አይሁድ ጤናማ መንፈስ አልነበራቸውም። በተለይ ዘመኑ ምድረ እሥራኤል በቅኝ ግዛት የነበረችበትና ህዝቡም በካህናቱና በመሪዎቹ ተስፋ የቆረጠበት ወቅት በመሆኑ ብዙዎች ተመልካች አጥተው በየስፍራው ሰቆቃ ላይ ነበሩ።


በተለይ ድሆችና ህሙማን አስታዋሽ አጥተው በከፋ ችግር ውስጥ የወደቁበት ዘመን ነበር። ቅኝ ገዢዎቻቸው የራሳቸው ጥቅም እንዳይነካ ይጠብቃሉ እንጅ በህዝቡ ላይ ስለሚደርሰው መከራ አይገዳቸውም ነበር። በዚህም ምክንያት አይሁድ በተለያየ ጎራ ተሰልፈው ህዝቡን ያወናብዱት ነበር። ጌታ ይህን ሁሉ አይቶ ከክፉ ስራችሁ ተመለሱ፣ ህዝቡን አትበድሉ፣ እናንተ የማታደርጉትን በህዝቡ ላይ አትጫኑ፣ ለድሆች ራሩላቸው፣ ሰንበትን መልካም በመስራት አክብሩ እያለ ይገስጻቸው ነበር። እነሱ ግን እንዲህ ይሉ ነበር። "፤ ወደ መቅደስም ገብቶ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሽማግሎች ወደ እርሱ ቀረቡና። በምን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት። " (ማቴ 21: 23) እንዲረዱትም በምሳሌ እያደረገ ይነግራቸው ነበር ። ትምህርቱን ቢረዱትም " የካህናት አለቆችና ፈሪሳውያንም ምሳሌዎቹን ሰምተው ስለ እነርሱ እንደ ተናገረ አስተዋሉ፤ ሊይዙትም ሲፈልጉት ሳሉ ሕዝቡ እንደ ነቢይ ስላዩት ፈሩአቸው። " ማቴ 21፥45


ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተራራው ስብከቱ ላይ "፤ እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር የመጣሁ አይምሰላችሁ፤ ልፈጽም እንጂ ለመሻር አልመጣሁም። " (ማቴ 5: 17) እያለ ይናገር ነበር ነገር ግን አይሁድ በቅንአት አይናቸው ታውሮ ሰለነበር የሚላቸውን አይሰሙም ነበር። ህዝቡ እሱን ከተክተለ ክብራችን ይቀርብናል በማለት ተጨንቀዋልና በእለተ ረቡዕ የመጨረሻውን ምክር አድርገው ከሐዋርያት መካከል ይሁዳን በገንዘብ አሳልፎ እንዲሰጣቸው ከተዋዋሉ በኋላ በ30 ብር የምስመው እሱ ነው ያዙት ብሎ አሲዞታል። ምክራቸው ፍጻሜ በማግኘቱ በጌታ ላይ እየተሳለቁ መከራ አጽንተው በመስቀል ላይ ሰቅለውታል።
ልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት "፤ አንድ ሆነው በአንተ ላይ ተማከሩ፤ በአንተ ላይ ቃል ኪዳን አደረጉ፤ "(መዝ 83: 5) ብሎ እንደተናገረው ከመስቀል ላይ አውጥተው እስኪሰቅሉት ድረስ እህል ላይቀምሱ ቃል ተገባብተው ተለያይተዋል።

ክፉ ሰዎች ከመከሩት ክፉ ምክር አምላካችን እግዚአብሔር በቸርነቱ ይጠብቀ

እንበለ ደዌ ወህማም እንበለ ፃር ወድካም አመ ከመ ዮም ያብጽሃነ ያብጽህክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ በፍስሃ ወበሰላም አሜን።

@kidestaresema
@kidestaresema
@kidestaresema
3.0K viewstheotokos (የአምላክ እናት), 14:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ