Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Universities Muslim Association /Ethio-UMA/

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioumachannel — Ethiopian Universities Muslim Association /Ethio-UMA/ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethioumachannel — Ethiopian Universities Muslim Association /Ethio-UMA/
የሰርጥ አድራሻ: @ethioumachannel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 322
የሰርጥ መግለጫ

ሙስሊም ተማሪዎች በያሉበት ትስስር ማድረግ: ተውሒድና ሱናን መሰረት ያደረገ ኢስላማዊ እውቀትን መገብየት: ብሎም እርስ በርሳቸው መተዋወቅና መወዳጀት!
"ቁርአን እና ሱናን በሰለፎች አረዳድ"

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-11-20 14:31:37 كل صفة مدح الله بها العبد في القرآن فهي ثمرة العلم ونتيجته، وكل ذمّ ذمّه فهو ثمرة الجهل ونتيجته.

ابن القيم |
#مفتاح_دار_السعادة ومنشور ولاية العلم والإرادة (١/ ١١٥).

እያንዳንዱ አላህ በቁርአን ባሪያውን ያወደሰበት ባህሪ የእውቀት ፍሬው እና ውጤቱ ሲሆን፤ሁሉም የውቀሰበት ነገር ደግሞ የአለማወቅ ፍሬው እና ውጤቱ ነው።

ኢብኑል ቀይም

      ‏•••═══ ༻✿༺═══•••
https://t.me/amhakfelagijemaa
142 viewsحيدر مزمل, 11:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-15 08:58:31
ዛሬ ሰዎች ወደ አላህ ለመቃረብ ብለው ለሰዎች ሱጁድ ሲያደርጉ አጂብ
ይኸው እነዚ ናቸው ሱፊይዎች

ሽርክ
❶ኛ
يَا أَيُّهَا النَّاسُ ضُرِبَ مَثَلٌ فَاسْتَمِعُوا لَهُ ۚ إِنَّ الَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِ اللَّهِ لَن يَخْلُقُوا ذُبَابًا وَلَوِ اجْتَمَعُوا لَهُ ۖ وَإِن يَسْلُبْهُمُ الذُّبَابُ شَيْئًا لَّا يَسْتَنقِذُوهُ مِنْهُ ۚ ضَعُفَ الطَّالِبُ وَالْمَطْلُوبُ

እናንተ ሰዎች ሆይ! አስደናቂ ምሳሌ ተገለጸላችሁ፡፡ ለእርሱም አድምጡት፡፡ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምትግገዟቸው (ጣዖታት) ዝንብን ፈጽሞ አይፈጥሩም፡፡ እርሱን (ለመፍጠር) ቢሰበሰቡም እንኳን (አይችሉም)፡፡ አንዳችንም ነገር ዝንቡ ቢነጥቃቸው ከእርሱ አያስጥሉትም፡፡ ፈላጊውም ተፈላጊውም ደከሙ፡፡
[ሱረቱ አል-ሐጅ - 73]

ሱብሃነ-ረቢ ምንኛ ያማረ ምሳሌ ነው! ከአላህ ውጭ የሚመለኩት ተሰባስበው እንኳን ቢሆን ዝንብ አይፈጥሩም። ሲቀጥልም ዝንብ ራሱ የሆነ ነገር ቢወስድባቸው አይቀሙትም። ኧረ እንደውም እንደወሰደባቸው አያውቁም። ምን ያክል ደካሞች መሆናቸውን እንገንዘብ እንደትስ ይመለኩ በፍፁም ከአላህ ወጭ ሊመለኩ አይገባም።

2ኛ ይቀጥላል
144 viewsحيدر مزمل, 05:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-06 14:50:59 #ማምሻም_እድሜ_ነው
  
#ከተረት_ወደ_እውነት

ወንድሜ ባለፈው እድሜህ መልካም ሰርተህ ከሆነ አላህን አመስግን ካልሆነ ግን ዛሬውኑ ወደ አላህ ተመለስና ማንነትህን አድስ። ማምሻ እድሜ የሚሆነው ወደ አላህ የሚያስጠጉ መልካም ተግባራት ሲተገበርበት እንጂ ዱንያ ላይ በስተ እርጅና ስለተመቻቸ ብቻ አይደለም። ተውሂድ የሌለው እርጅና ሻማ ያልበራበት ምሽት ነው፣ሱና የሌለውና ቢዳዓ የወረሰው ሽምግልና ዝናብ እንዳንዣበበበት አመሻሽ ነው። በወንጀል የታጀበ እርጅና በእሾህ እንደታጠረ መኖሪያ ነው።
#ስለዚህ_ጀግናዬ_ማምሻችንን_እናሳምር። አላህ የተውበት በር እስኪዘጋ ተውበትን ተቀባይ ነውና ወደ አላህ እንመለስ፤ካለንበት ሽርክ፣ቢዳዓ፣ወንጀል ወስነን እንውጣ። #ማምሻም_እድሜ_ነውና_አመሻሻችንን_እናሳምር

አስተያየት በ


@Dsiaunivbot
 
https://t.me/amhakfelagijemaa
140 viewsحيدر مزمل, 11:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-22 21:42:39 አሰላሙዐለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ

ለሁላችንም የምትሆን ማስታዎሻ



እንደሚታወቀው የሀዋሳ ሪፈራል ሰርክል ተማሪዎች መስጅድን ለመታደግ ብዙ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል!

አሁንም የቀረንን የገንዘብ መጠን ለመጨረስ የተሰጠን የጊዜ ገደብ ከመጠናቀቁ በፊት......
ሁላችንንም አሳታፊ በሆነ መልኩ በአላህ ፈቃድ የፊታችን ጁሙዓ ጥቅምት 12/02/2014 ዓ.ል ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ጀምሮ #የኦን_ላይን የኒያ ዘመቻ ተዘጋጅቷል!!

ውድ ወንድምና እህቶች!! ሁላችንም ይህን የአላህን ቤት አላህ ከሰጠን ሲሳይ ላይ በቻልነው መጠን በማውጣት እንታደገው።

ለዛም በተዘጋጀው #የonline ፕሮግራም ላይ ለመሳተፍ ከአሁኑ እንዘጋጅ። ሌሎች ዘመድ ወዳጆቻችን በዚህ ዘመቻ እንዲሳተፋ አሁኑኑ መልዕክቱን እናጋራቸው!!
በአላህ ፈቃድ በቀጠሮው ለመገኘት እንሞክር!!
ኸይር ስራ በቃ አይባልምና ከአሁን በፊት የተሳተፋችሁ አሁንም በመሳተፍና ሌሎችንም በማመላከት በቀጠሮው ይገኙ!!
መልዕክቱን በሚገባ ያስተላልፋ!!

Share

@refferaltemariwochmesjid
399 viewsHilal Yimer, 18:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-17 13:59:10
የትርጉም ስራዎች ቁጥር:

ህፃን የሆነች ሴትን ልጅ ፀጉር መላጨት እንደት ይታያል ሱና ነው ወይስ አይደለም ልክ ወንድ ልጅ እንደሚላጨው ትላጫለችን?

ፀጉሯ ተመዘኖ በግራሙ ልክ ሶደቃ ማውጣትስ እንደት ይታያል ለወንድም ልጅ ጭምር?

አል ዐላማ ዶክተር ሷሊህ አል ፈውዛን ኢብኑ ዐብዲላህ አል ፈውዛን (ሃፊዞሁሏህ
)።

መጠን 2·6 ሜጋ ባይት ብቻ
#share
•••━════✿ ✿════━•••
ለሃሳብ አስተያየቶ:

@Dsiaunivbot

https://telegram.me/amhakfelagijemaa
136 viewsحيدر مزمل, 10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-16 20:56:00 ውዱ ነብይﷺ በሞቱበት ቀን እየጨፈሩ፣ጫት እየበሉ፣አርደው በልተው ጠግበው የሚደሰቱ ሰዎችን
لا إله إلا الله
ሲሉ ባንሰማና መስጅድ ገብተው ሲሰግዱ ባናያቸው ኖሮ #ካፊር_ናቸው_ብለን_እንጠረጥር_ነበር።
https://t.me/amhakfelagijemaa
128 viewsحيدر مزمل, 17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-15 17:53:59 غدا السبت بعد الفجر إن شاء الله

لقاء مفتوح عبر الزوم لمناقشة شبهات حول المولد النبوي

د.عبدالعزيز بن ريس الريس

*6:00* فجرا بتوقيت السعودية

دخول ZOOM

https://us02web.zoom.us/j/85142689225?pwd=MWZzRWlYUzE5K1RIeWY5bHdxbFZ3UT09
116 viewsحيدر مزمل, 14:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-12 10:33:59 ስምንት ጠቃሚ ምክሮች
""""""""""""""""""""""""""""""""""
1,ከሰው ጋር አትፎካከር:— ምክንያቱም ሁሉም አላህ የፈቀደለት ነውና የሚያገኘው።ደግሞም መፎካከር ወደ ቅናት ይወስድሀል፤ቅናት ወደ ጥላቻናመጥመም ይጋብዛልና
2,ያለህን ተመልከት:—ያለህ ነገር ተመልክተህ ጌታህን አመስግን፤የሌለህን ምትመኝና ሁሉም የሚያምርህ ከሆነ በሀሳብ ዋልለህ ትጠፋለህ፣ያለህንም ታጣለህ።
3,እራስህን ምሰል:—ሰዎችን አትከተል የሆነ የራስህ የሆነ አላህ የሰጠህ ጥበብ አለህና እሱን ፈልገህ ለማዳበር ሞክር እንጂ ሰዎችን ለመምሰል አትሞክር መምሰልም አትችልምና።
4,ሁሉንም ለማስደሰት አትሞክር:—አንተ ለማንም ደስታ መስጠት አትችልም ደስታ ከአላህ ነው።ሰዎችን ለማስደሰት ሰበብ ብትሆንም ሁሉንም ማስደሰት አትችልም።ምክንያቱም አንተ አስደስታቸዋለሁኝ ስትል ሊያሳምማቸው ይችላልና።
5,የውሸት ደስታን አትፈልግ:—የእውነተኛ ደስታ ሚገኝበትን መንገድ አፈላልግ እንጂ ደስታን ፍለጋ የውሸት መንገድ አትጓዝ።ደስታ ሳይሆን ሀዘን ነው የሚሆነው ትርፉ።
6,ማንን እንደምታገኝ አታውቅምና ለሁሉም ቅን ሁን:—በህይወት አጋጣሚህ የምታገኛቸው ሰዎች የወደፊት የህይወት አጋርህም ሊሆኑ ይችላሉ፤ዳግም ባታገኛቸው እንኳን ጌታህ ዘንድ ቦታ ታገኝበታለህና ሁሌም ቅን አሳቢ፣ መልካም ሰሪ፣ለሰዎች የምታዝን ሁን።
7,መለወጥ ማትችላቸውን ነገራቶችን ተቀበላቸው:—ጌታህ ላንተ ያለው የሰጠህ ስጦታ አለ ያነገር ላንተ በቂ ባይሆን እንኳ መቀየር ማትችለው ነገር ከሆነ ለመቀየር አትሞክር አይቀየርምና።
8,የራስህን ትክክለኛ ወዳጅ ሁን:—ለራስህ አስብ፣ለራስህ መልካም ሁን፣እራስህን አትጣል ግን በጣም ሰዎችን የሚያስረሳ አይነት እራስ ወዳድ አትሁን።

ibnu muzemil
@amhakfelagijemaa
153 viewsحيدر مزمل, 07:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-10-03 08:32:59 ሁሌም ውብ ነሽ እማ

እናት ምን ብታረጅ ብትሆንም ጎስቋላ፣
ቤቷ ያልተዋበ ቢሆንም ሰቃላ፣
ምግቧም የታጨቀ ሆኖ ባይበላ፤
እናት ግን እናት ነች ፍቅሯ ብቻ በቂ፣
ጠረን፣መዓዛዋ ሁሌም ተናፋቂ።
እናት እናት የሚል ጠረን መዓዛዋ፣
ከአንገቷ ስር አለ ቢያረጅም ገላዋ።
ፊቷ ቢሸበሸብ፣ቢያጥር ፀጉሯ፣
እጇ ቢኮማተር፣ቢያነክስ እግሯ፣
እይታው ቢገደብ፣አይኗ ቢያነባ፣
መቀነት ቢያሻው፣ቢጎብጥም ወገቧ፣
መስማት ቢያዳግተው፣ጆሮዋ ቢደክም፣
ምላሷ ተሳስሮ፣ድምፇ ምን ቢያዘግምም።
ይሄ ሁሉ ሆኖ እርሷን ለታደለ፣
እናት እናት የሚል ጠረን መአዛዋ ከላዯ ላይ አለ፣
ክብሯን ለተረዳ፣በፍቅሯ ተለክፎ ሩ~ቅ ለዋለለ


ibnu muzemil
https://t.me/amhakfelagijemaa
160 viewsحيدر مزمل, 05:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-09-10 06:17:13 ይህ ነው እውነታው ክፍል 1

ካፊሮች(አይሁዶች እና ክርስቲያኖች) እስምልናን ለማጠልሸት እና የእነርሱን ሃይማኖት እውነት ለማስመሰል ሲጥሩ፣ ከመፅሃፎቻቸው ተወጣጥቶ ሃይማኖታቸው ውድቅ መሆኑ ሲነገራቸው፤ እስልምናም ክርስትናን እንደሚደግፍ፣እየሱስ ጌታ መሆኑን የሚገልፅ አንቀፅ በቁርአን ውስጥ አለ ብለው  ይቀጥፋሉ፣ ሙስሊሞችን ለማደናገር እና ክርስቲያኖችም የልብ ልብ እንዲሰማቸው ለማድረግ ይሞክራሉ። ከነዚህም መሀከል: በሱራ አንቢያእ 21:91 ላይ ያለውን ስለ ዒሳ (እየሱስ) የአላህ ሰላም በእርሱ ላይ ይሁንና የተጠቀሰው አንዱ ነው።
﴿وَالَّتي أَحصَنَت فَرجَها فَنَفَخنا فيها مِن روحِنا وَجَعَلناها وَابنَها آيَةً لِلعالَمينَ﴾
[Al-Anbiyâ': 91]

ትርጉም: <<ያቺንም ብልቷን ከዝሙት የጠበቀችውና በእርሷም ውስጥ ከነፍሳች የነፋንባት ከዛም እርሷንም ልጇንም ለአለማት ተአምር ያደረግናቸውን መርየምን አስታውስ>>
ይህን አንቀፅ ይዘው ከእራሱ ነፍስ ዘራበት ብርቅዬ ልጁ መሆኑን አላህ መስክሯል በቁርአኑ ብለው ይሞግታሉ።
ነገር ግን በሚገርም ሁኔታ እንዲህ የሚሉ ተመሳሳይ አንቀፆች አሉ። ለምሳሌ በሱረቱ ሷድ 38:72 ላይ ስለ አባታችን አደም ሲገልፅ እንዲህ ይላል:
﴿فَإِذا سَوَّيتُهُ وَنَفَختُ فيهِ مِن روحي فَقَعوا لَهُ ساجِدينَ﴾
[ص:72]
ትርጉም: <<አፈጣጠሩን አሳምሬ በፈጠርኩት እና ከመንፈሴም በነፋሁበት ጊዜ፣ለእርሱ ሰጋጆች ስትሆኑ ተዋደቁለት አልኩ>> ቁርአን 38:7
በሌላ ቦታም ለእየሱስ ብቻ ሳይሆን ለአደምም  ከመንፈሴ ነፋሁበት ይላል: ቁርአን 15/29፣ 32/9 ይመልከቱ።

ታድያ እየሱስም አዳምም የፈጣሪ ልጆች፣አንድ ሶስተኞች (ስላሴ ውስጥ የሚካተቱ)ናቸውን?  በጭራሽ! ታድያ ምንድ ነው የተፈለገበት?  ይህ የተፈለገበት እየሱስን ለማላቅ ጅብሪልን አዘን በእርሷ ላይ ዒሳ እንዲረገዝ አደረግን ማለት ነው የተፈለገነት(ተፍሲር በገዊን ይመልከቱ)። ደግሞ እኛ አለ እነ ማንን ነው እኛ ያለው አላህ? የሚል አይጠፋም። ይህ ከዚ በፊት ብዙ የተብራራበት ስለሆነ ልለፈው። ግራ የገባው ካለ ያሳውቀን።

ሌላው ማምቻቻው:
﴿إِذ قالَتِ المَلائِكَةُ يا مَريَمُ إِنَّ اللَّهَ يُبَشِّرُكِ بِكَلِمَةٍ مِنهُ اسمُهُ المَسيحُ عيسَى ابنُ مَريَمَ وَجيهًا فِي الدُّنيا وَالآخِرَةِ وَمِنَ المُقَرَّبينَ﴾ [الإمران: 45]
ትርጉም: መልአክቶችም መርየም ሆይ አላህ ከእርሱ በሆነ ቃል ስሙም አልመሲህ ዒሳ የመርየም ልጅ በሆነ በዚህ አለምና በመጨረሻውም አለም የተከበረና ከባለመዋሎችም በሆነ ልጅ ያበስርሻል ባሏት ጊዜ አስታውስ(ቁርአን 2/45)

ይህ አንቀፅ ግልፅ ቢሆንም ለማምታታት ይጠቀሙበታል። ግና ግልፅ ነበር የትኞችም ነብያት፣ደጋግ የአላህ ባሮች እንደየ ደረጃቸው በሁለቱም ሃገር የተከበሩ እና የላቁ ናቸውና በእየሱስ ብቻ የተገደበ አይደለም። ሙሳንም በዚሁ ቃል እንዲህ ሲል ገልፆታል:
﴿يا أَيُّهَا الَّذينَ آمَنوا لا تَكونوا كَالَّذينَ آذَوا موسى فَبَرَّأَهُ اللَّهُ مِمّا قالوا وَكانَ عِندَ اللَّهِ وَجيهًا﴾
[احزاب: 69]
ትርጉም: እናንተ ያመናችሁ ሆይ ሙሳን እንዳሰቃዩት ሰዎች አትሁኑ። አላህም ካሉት ነገር ሁሉ አጠራው። አላህም ዘንድ ባለ ሞገስ ነበር።  ሌሎችም በርካታ ማስረጃዎች አሉ።  (ቁርአን 4:98፣17:70 ይመልከቱ)


ሌላው አደራ የምለው ብዙ ጊዜ ሙስሊም ነበርን፣ክርስትያን ሆነን ነው እያሉ የሚያስተምሩ ሰዎች ዝም ብለው ጥቅስ እየጠቀሱ፣ ወይ ግማሹን ቆርጠው ይሰጧቹዋል። ብርቅ አይደለም እነ ቢኒያም ፍሬው ሌሎችም ቆራርጠው ሲያስተምሩ ያየነው ነገር ነው። ካምፓስ እያለሁ እንዲህ ያሉ ውሸቶች ፔንጤ ጓደኞቼ ያመጡልኝ ነበር።  ግን አንቀፁን ሳሳያቸውና ጭራሽ የማይገናኝ አንቀፅ ሲሆን ይገረሙም ነበር። ስለዚህ ቁርአንም ሆነ መፅሃፍ ቅዱስ ጥቅስ ሲነገረን ከመፅሃፎቹ እናረጋግጥ፣አንድ አንቀፅ ብቻ ይዘን ከፊት እና ከኋላው ያለውን ሳናረጋግጥ አንወስን። ያልገባን ነገር ከሆነ እንጠይቅ። በጭፍን አንከተል።

@amhakfelagijemaa

ለሃሳብ አስተያየቶ

@Dsiaunivbot
192 viewsحيدر مزمل, 03:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ