የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ስራ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
66.24K
የሰርጥ መግለጫ
በዚህ ቻናል
👉ትምህርታዊ መፅሐፎችን
👉ሪሰርቾችንና ፕሮፖዛሎችን
👉የሶሻልና የናቹራል መጽሐፎችን
👉የዩኒቨርስቲ እና የቴክኒክና ሙያ ሞጁሎችን
👉የጥያቄና መልስ ወርክ ሽቶችን እና
👉ልዩ ልዩ መጽሐፎችን በነፃ ያገኛሉ!
For any comments: @ethiodlbot
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
1
4 stars
0
3 stars
1
2 stars
1
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7
2024-06-05 14:00:35
ሰራተኞችን የሚቆጣጠሩ ካሜራዎች በየወረዳዎች ሊገጠሙ ነውአገልግሎት ሰጪ ሰራተኞችን የሚቆጣጠሩ ካሜራዎች ዛሬ በየክፍለ ከተሞች እንደሚሰራጩ የአዲስ አበባ ሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ አስታወቀ። ይህም ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ደንበኞች ላይ እንግልት የሚፈፅሙ ሰራተኞችን ለመቆጣጠር የሚያስችል መሆኑን ኤጀንሲው ገልጿል። ኤጀንሲው ለአራዳ እንደገለፀው በ11 ክፍለ ከተሞች ቁጥጥር ሲያደርግ እንደቆየና አሁን ደግሞ በ119 ወረዳዎች የካሜራ ቁጥጥር ስራ ሊጀምር መሆኑን አስታውቋል።
ኤጀንሲው እንደገለፀው የካሜራዎቹ ግዢ ተጠናቆ ዛሬ በየክፍለ ከተሞች ይሰራጫሉ። ይህም ግልፅነት እና ተጠያቂነትን ለመፍጠር እንዲሁም ክፍለ ከተሞች የየራሳቸውን ወረዳዎች መመልከት የሚችሉበት ስርዓት ለመዘርጋት እንደሚረዳ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ ተናግረዋል።
በአዲስ አበባ ከተማ የደንበኞችን እንግልት ይቀንሳሉ የተባሉና ምስልን እንዲሁም ንግግርን የሚቆጣጠሩት ካሜራዎች ገጠማ በሁለት ሳምንት ይጠናቀቃል ተብሏል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በክፍለ ከተማ ደረጃ ያለውን የደንበኛ መጉላላት ለመቀነስ ተቋሙ መታወቂያ ሲታተምና በክፍለ ከተማ ያለውን የፅህፈት ቤት አገልግሎቶች ሂደት በካሜራ ሲቆጣጠር መቆየቱ ይታወቃል።
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
7.7K viewsedited 11:00
2024-06-05 13:56:56
#Inbox #እንደወረደ
ለአንድ ድግሪ 9 ዓመትምን ዋጋ አለው እግዚአብሔር የሰጠኝ በቂ ዕውቀት እያለኝ እንደዕድል 10ኛ ክፍል በ1 ነጥብ በማይሞላ ቀርቼ ወደ ኮሌጅ ተወዳድሬ ገባሁና በከፍተኛ ውጤት ተመረቁኝ ። የእንግሊዝኛ መ/ር እጥረት ሰለጋጣማቸው 9ኛ ክፍል መደቡኝ ፤ እዛም በተማሪዎች ዘንድ ተወደድኩኝ፤በሚቀጥለው ዓመት ወደ 11ኛ ክፍል በተማሪዎች መርጫ ማስተማር ጀመርኩ ፥ የባስ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በእኔ መማር ፈለጉ ፥ ይህ እንደዚህ እያለ ከተቀጠርኩበት በሁለተኛው ዓመት መንግሥት የክረምት ትምህርት ዕድል ባመቻቸው መሠረት ተወዳድሬ ዕድሌን አግኝቼ ወደ ዩኒቨርስቲ ቀናው ።
ያውም በ2010 ዓ.ም ስሆን አንድ ዓመት በኮቭድ 19 ምክንያት ትምህርት ስቀር በጣም ቆዝሜ እያለሁ ሌላ ደግሞ ታምር ነገር ተከሰተ ያውም የትምህርት ካላንደር ለማስተካከል በሚል ነው።
ይሁን እንጂ አሁን የባስ ፀጥ አለ። ኤረ አብድኩኝ መኖር ጠላው ። አቤት ለአንድ ድግሪ 9 ዓመት ሙሉ ።
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
7.0K viewsedited 10:56
2024-06-05 13:20:30
በአንዱ ሊንክ ከ5 ሰው በላይ መግባት ሰለማይችል ፈጥናችሁ ለመቀላቀል ሞክሩ
t.me/BlumCryptoBot/app?startapp=ref_EG1STHlvrQ
Hamster Kombat
https://t.me/hamster_kOmbat_bot/start?startapp=kentId812359129
Tapswap
https://t.me/tapswap_mirror_bot?start=r_812359129 +2.5k Shares as a first-time gift
https://t.me/tapswap_mirror_1_bot?start=r_812359129 +2.5k Shares as a first-time gift
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
6.8K viewsedited 10:20
2024-06-05 11:31:40
በሰባት “አይቪ ሊግ” ትምህርት ቤቶች ተቀባይነት ያገኘው ኢትዮጵያዊ-አሜሪካዊ ታዳጊኢትዮጵያዊ አሜሪካዊው ታዳጊ ወጣት ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን በአስደናቂ ውጤት በማጠናቀቅ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ክብር በሚሰጣቸው ሰባት “አይቪ ሊግ” ትምህርት ቤቶች ተቀባይነት አግኝቷል።
በመጪው የትምህርት ዘመን፣ በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ የዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርቱን የሚጀምረው ኤታን ፍጹም ርስቱ፣ ‘ኤስኤቲ' በተሰኘው የተማሪዎች የቀለም ትምህርት የብቃት ፈተና፣ 1ሺሕ 600 በማምጣት የመጨረሻውን ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡ ይህንን የመጨረሻውን ከፍተኛ ውጤት ካገኙ እንደነ Facebook ባለቤት ማርክ ዙከንበርግ ያሉ ጥቂት ግለሰቦች መካከል አንዱ መሆንም ችሏል።
ከሁለት አስርት አመታት በፊት ወደ አሜሪካ ከመጡ ኢትዮጵያዊያን ወላጆቹ የተወለደው የ18 አመቱ ታዳጊ ኤታን ያገኘው ስኬት የልፋታቸውን ዋጋ መሆኑን አባቱ ፉፁም ዕርስቱ ተናግረዋል።
በዚህም፣ በዩናይትድ ስቴትስ በየዓመቱ ፈተናውን ከሚወስዱ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ተፈታኞች ውስጥ ከፍተኛውን ውጤት ከሚያስመዘግቡ አንድ ከመቶ(1%)ተማሪዎች ውስጥ ለመኾን ችሏል።
ወቅታዊ ጉዳዮችን በንቃት የሚከታተለው ኤታን በሃርቫርድ ቆይታው ዓለም አቀፍ ጉዳዮችን እና መንግስታዊ አስተዳድርን ያጠናል። አንድ ቀን ደግሞ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ሆኖ ሊመረጥ ይችላል የሚለው ሀሳብም ከብዙ ቦታ ይሰነዘርለታል።
Credit: adcaccess.org
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
6.7K viewsedited 08:31
2024-06-05 10:49:07
#Inbox #እንደወረደ
የክረምት ተማሪዎች ቅሬታየእውነት ትምህርት ሚንስቴር በቁም እየቀበረን ነው ያለው። ባለፈው አመት መጨረስ ሲገባን የትምህርት ካላንደር ለማስተካከል በሚል ሳንጨርስ ቆይተናል። ዘንድሮም አዝማሚያው እንደዛ ይመስላል። ምክንያቱም የ12ኛ ክፍል ሀገር አገር አቀፍ ፈተና ምክንያት እስከ ሀምሌ 11 ድረስ እንዲሰጥ ወስኗልና። ይህ ማለት ከሀምሌ 15 በፊት ዩንፈርስቲዎች የክረምት ተማሪዎችን ተቀብለው እንደማያስተምሩ ግልፅ ነው። በዚህ የተነሳ 1 ወር ከ15 ቀን በቂ አይደለም በሚል ምክንያት የዘንድሮውንም እንዳይሰርዘው እሰጋለሁ።
አንድ ክስተት ላንሳና ልጨርስ። በ2015 መጨረስ እያለበት የክረምት ትምህርት ባለመኖሩ ዋጋ ስለከፈለ አንድ ግለሰብ ላንሳ።
ግለሰቡ የሚሰራበት መስሪያ ቤት በ2016 መዋቅሩ ይሰፋና የውስጥ ማስታወቂያ በማውጣት ለደረጃው የሚመጥኑ ሰራተኞች አወዳድሮ ክፍት ቦታው ላይ ለመመደብ ለሰራተኞች ያሳውቃል። ማስታወቂያ የወጣባቸው ቦታዎች ባጋጣሚ የመጀመሪያ ዲግሪ የሚጠይቁ ነበሩ። ሆኖም ግን ሌሎች መረጃቸውን አስገብተው ሲወዳደሩ ይህ ግለሰብ ግን 2015 ላይ የክረምት ትምህርት ባለመኖሩ ሳይመረቅ በመቅረቱ ሳይወዳደር ይቀራል።
ባጋጣሚ ለመጠያየቅ ተደዋውለን በምናወራበት ጊዜ ይህን ጉዳይ እንዲህ በማለት አጫወተን "ዘንድሮ ብርሃኑ ነጋ ቀበረኝ" በሚል።
እኔም በትምህርት ሚንስትሩ በቁም ከተቀበሩ ሰዎች መካከል አንዱ ነኝ ብዬ አስባለሁ። ሌሎችም እንዲህ አይነት ነገር ያጋጠማችሁ ትኖራላችሁ።
"ሰማይ አይታረስ ንጉስ አይከሰስ" የሆነን አሰራር በጋራ ለማስወገድ ድምፅ እንሁን። (Ethiopian Digital Library) እናንተም ድምፅ ስለምትሆኑን እናመሰግናለን።
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
7.4K viewsedited 07:49
2024-06-04 16:25:02
ከሰኔ 1 ጀምሮ ተፈጻሚ ይሆናል - የቤት አከራዮች ተከራዮችን ለማስወጣት የ2 ወር ማስጠንቀቂያ ጊዜ እንዲሰጡ የሚያስገድደው አዋጅ
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 24 ቀን 2016 የጸደቀው 'የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1320/2016' ከሰኔ 1 ቀን 2016 ጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን ተገለጸ።
አዲስ ማለዳ ከከተማ አስተዳደሩ ኮምኒኬሽን ቢሮ ባገኘችው መረጃ የአዲስ አበባ ቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ቅድስት ወልደጊዮርጊስ እንደገለጹት አዋጁ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር የተረጋጋ ፣ ግልፅነት እና ተጠያቂነት ያለው እንዲሁም የአከራይ እና የተከራዮችን ጥቅም እና መሰረታዊ መብቶች ሚዛን በጠበቀ መልኩ ለመፈፀም የተደነገገ ነው።
የመኖሪያ ቤት ኪራይ ቁጥጥር እና አስተዳደር አዋጅን ለመተግበር የሚያስችል ውይይት ተካሄዷል።
አዋጁ በውስጡ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ውል እና ዋጋ፣ የአስፈጻሚ አካላት ስልጣን እና ሌሎች ድንጋጌዎች እንደተካተቱበት አዲስ ማለዳ ማዘገቧ አይዘነጋም።
በተጨማሪም የቤት አከራዮች ቅድመ ክፍያ መጠየቅ የሚችሉት የሁለት ወር ብቻ እንዲሆን የሚደነግግ ሲሆን ተከራዮችን ለማስለቀቅም የሁለት ወራት የዝግጅት ጊዜ እንዲሰጥ ያስገድዳል። ከዚህ ባለፈም መንግስት ማግኘት ያለበትን ግብር እንዲያገኝ እንደሚያስችል የምክር አባላት ገልጸው ነበር።
ነምቤኦ (NUMBEO) የተባለ በሰርቢያ አገር መቀመጫውን ያደረገ የአገራትን የኑሮ ደረጃ የሚመዝኑ መረጃዎችን የሚያጋራ ድረ ገጽ የአገራቱን ዜጎች ገቢ እና የመኖሪያ ቤት ዋጋ ጥምርታን በማነጻጸር ባወጣው ሪፖርት ኢትዮጵያውያን ለመኖሪያ ቤት የሚያወጡት ዋጋ ከገቢያቸው ላይ 43 ነጥብ 1 በመቶ እንደሆነ ተመላክቷል። #አዲስ_ማለዳ
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
10.0K viewsedited 13:25
2024-06-04 16:21:37
#Inbox
ድምፃችን ስለሚትሆኑ እናመስግናለን
ጉዳዩ ፦የክረምት ትምህርት ጀምሮ ያልጨረሱት የመምህራን ጉዳይ ስለሚመለከት ይሆናል ።
ከላይ በርዕሱ ለመግለጽ እንደተሞከረው የክረምት ትምህርት መምህራን ደረጃቸውን ለማሻሻል በቁጥር ብዙ የሚባሉ መምህራን እየተማሩ እንዳሉ ይታወቃል ፥ ይሁን እንጂ ባለፉት ሁለት ዓመታት ማለትም በኮቭድ 19 እና በ2015 ዓ.ም መንግስት የትምህርት ክፍሌ ጊዜ /ካላንደር / ለማስተካከል በሚል መዘጋቱ ግልጽ ነው።
በዚህ ምክንያት መምህራን በሰባዊም ሆኔ በማህበራዊ በጣም ተጎድተው አሳልፏል ። ዘንድሮ ደግሞ ያለ ምንም ምክንያት ማቋረጥ ስለፈለገ ድምፅ እንድትሁን በአክብሮት እናሳውቃለን ። አንድ ድግሪ ለማገኘት 9 ዓመት ሙሉ ያለምክንያት ፈጀው ።
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
11.0K viewsedited 13:21
2024-06-04 13:29:59
#Ads
የኦንላይን ስራ እንዴት ልጀምር?https://t.me/online_business25
9.9K viewsedited 10:29
2024-06-03 09:54:49
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
12.2K viewsedited 06:54
2024-06-02 15:41:14
Hamster Kombat እውነተኛ መሆኑ ተረጋግጧል!
አሁኑኑ ጀምሩ ስክሪናችሁን tap tap በማድረግ!
Steps
1. Start
2. Play in 1 click
3. Tap Tap Tap
4. Share for your friends
https://t.me/hamster_kOmbat_bot/start?startapp=kentId812359129
@Ethiopian_Digital_Library
@Ethiopian_Digital_Library
14.6K viewsedited 12:41