Get Mystery Box with random crypto!

Ayu Zehabesha-Official (አዩ ዘሀበሻ)

የሰርጥ አድራሻ: @ayuzehabeshaofficial
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 181.36K
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ❗
መረጃ ለማድረስ እና ማስታወቂያ ለማሰራት ከስር ባለው ሊንክ ይጻፉልን👉http://t.me/ayulaw

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-16 18:36:33 በዎላይታ ዞን ውዝፍ የወር ደመዝ ያልተከፋላቸውን ለመጠየቅ ሰልፍ የወጡ የመንግስት ሰራተኞች ድብደባና እስራት ገጠማቸው
በትናንትናው ዕለት የሶስት ወር ደሞዝ ባለመክፈሉ አደጋ ላይ ወድቀናል የሚሉ የዎላይታ ዞን ሶዶ ዙሪያ መንግስት ሰራተኞች በሰላማዊ ሰልፍ እስከ ክልሉ ርዕሰ መስተደድር ቢሮ ድረስ የሄዱ ሲሆን ጥያቄያቸውን ይዘው ወደ አደባባይ እንዲወጡ ያስገደዳቸው የወረዳውን ሆነ የዞኑን መንግስት በተደጋጋሚ ቢጠይቁም በቂ ምላሽ ባይሰጥም በድጋሚ ዛሬ ወደ ዞኑ የሄዱትን ፓሊስ እንዲያባርርና እንዲታሰሩ መደረጉን ከስፍራው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ እየሆነ ያለው ነገር የመንግስት ሠራተኛን ከእነ ቤተሰቦቹ ጭምር ለረሃብና ችጋር በማጋለጥ ወደ ጎዳና እንዲወጡ የማድረግ ስልታዊ አሠራር ነው። ብሎም የተማረ የሠው ሃይልን በማዳከም ሌላውን የማህበረሰብ ክፍልን ለመዝረፍና ለመጨቆን ሆነ ተብሎ እየተሠራ ያለ አምባገነናዊነትና ማሀይምነትን ለማስፋፋት ምቹ አጋጣሚዎችን ሁሉ አሟጠው የመጠቀም ህዝብን የማማረር አደገኛ ተልዕኮ ነው" በሚል ያምናሉ።

በመሆኑም የሚመለከተው አካል የሠራተኛውን እና ቤተሰብ ህይወት ለመታደግ ደሞዝና የተለያዪ ጥቅማጥቅም በማስከበርና በመክፈል፣ ትውልድ የማስቀጠል አስቸኳይ እና ቀዳሚ የነፍስ አድን ሥራ እንዲሠራ ስንል እኛም ሆንን ቤተሰቦቻችን ከሞት አፋፍና ጣር ላይ ሆነን እንደአንድ የመንግስት ሠራተኛ ጩሄታችንን ስናሠማ፣ በተራበ አንጀትና በደከመ ጉልበታችን በጠወለገ ድምፃችን ነው" ስሉ የሰልፉ አስተባባሪዎች ገልጿል።

በተቃራኒው የዎላይታ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ ከ 3 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡ የተገለፀ ቢሆንም በአከባቢው ልማት ስራዎች ቆሞ በአብዛኛው መዋቅር ደመዝ መክፈል አለመቻሉ ለበርካቶች "ለምን" የሚል ጥያቄ ፈጥሯል።

በዎላይታ ዞን በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መንገድ ደሞዝ ለመንግሥት ሰራተኞች ባለመክፈሉ ምክንያት በአብዛኛው መዋቅር ትምህርት ቤቶች፣ ጤና ተቋማት እንዲሁም አገልግሎት ሰጪ መንግስታዊ ተቋማት አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን ተከትሎ ተገልጋይ ህብረተሰብ ክፍሎችም ከፍተኛ ችግር ውስጥ ስለመግባታቸው የመረጃ ምንጮቼ ገልፀዋል።
ደሞዝ ባለመክፈሉ "አደጋ ላይ ወድቀናልና እኔም የመንግሰት ሠራተኛ ነኝ ልጆቼንና ቤተሰቦቼን አድኑልኝ" የሚል ጥሪ በማሰማት ላይ ይገኛሉ።
ለተጨማሪ መረጃዎች join us
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የውስጥ መስመር   t.me/ayulaw
13.1K viewsAyu, edited  15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 18:36:32
12.5K viewsAyu, 15:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 18:29:45
የህወሃት ሀይሎች በራያ አላማጣ ወረዳ ትንኮሳ በመፈፀማቸው ምክንያት ትምህርት በመቋረጡ የአላማጣ ከተማ አስተዳደር ከወልደያ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ወልደያ ዩኒቨርስቲ ገብተው እንዲማሩ ተደረገ
የህወሃት ታጣቂዎች ሚያዚያ 7/2016 ዓ/ም በራያ ትንኮሳ በመፈፀሙ ምክንያት ትምህርት መዘጋቱ ይታወቃል።የአላማጣ ከተማ አስተዳደር የ 12ኛ ክፍል  ተማሪዎች  የዓመት ልፋት እንዳይስተጓጎል በማሰብ ተማሪዎችን እና የተማሪ ወላጆችን በማወያየት ከዛሬ ጀምሮ በወልዲያ ዩኒቨርስቲ ገብተው እንዲማሩ ተደርጓል።
ለሚቀጥሉት ሁለት ወራት የምግብ ፣ የትምህርት ፣ የመኝታ እንዲሁም የ ላይብረሪ ጥቅምን እንዲያገኙ ሙሉ ወጫቸውን ከተማ አስተዳደሩ በመሸፈን ወልደያ ዩኒቨርስቲ ገብተዋል።
ተማሪዎቹ በ 2016 ዓ/ም የትምህርት መርሀ ግብር ሲከታተሉ የነበሩ ሲሆን በተፈጥሮ የትምህርት መስክ እና በማህበራዊ የትምህርት ዘርፍ ሲከታተሉ የነበሩ ወንድ 266፣ ሴት ደግሞ 306 በድምሩ 577 ተማሪዎች ናቸው።
አዩዘሀበሻ
ለተጨማሪ መረጃዎች join us
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የውስጥ መስመር   t.me/ayulaw
12.7K viewsAyu, 15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 13:37:55
የግብፅ ነገር
የግብጽ ምሁራኖች አባይ ግድብ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ሊደርስበት ይችላል እያሉ ነው
ግንቦት 8/2016 ዓ.ም -አዩዘሀበሻ
በካይሮ ዩኒቨርሲቲ የጂኦሎጂ እና የውሃ ሃብት ፕሮፌሰር አባስ ሻራኪ በኢትዮጵያ ባሳለፍነው ሰኞ በደቡብ ኢትዮጵያ 4.9 በሬክተር ስኬል የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ጠቅሰው ከፍተኛ ጉዳት ሊያደርስ እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
የግብፁ አል-ሾሮክ ጋዜጣ  እንደዘገበው የመሬት መንቀጥቀጡ በጥንካሬው መጠነኛ ቢሆንም፣ መጠኑ ለአፍሪካ አህጉር ትልቅ ነው ብለዋል።
የዚህ የመሬት መንቀጥቀጥ በተለይ 35 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በሚይዘው እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ (GERD) ያሉ ግድቦች ላይ ችግር ይፈጥራል፣ ይህም ግድቡ የመሰንጠቅ አደጋ ቢደርስበት በሱዳን ጎርፍ እንደሚያስከትል አስጠንቅቀዋል።
ምስራቅ አፍሪካ በአፍሪካ አህጉር ውስጥ በጣም ንቁ የሆነ የመሬት መንቀጥቀጥ (seismic region) ያለበት ክልል ተደርጎ ይወሰዳል፣በእነዚህ ክልሎች ላይ የሚሰሩ ትላልቅ የውሃ ግድቦች ከተሰነጠቁ ወይም ከተበላሹ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ከፍተኛ አደጋዎች መረዳት አስፈላጊ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ሻራኪ እ.ኤ.አ. በ2023 በዳንኤል አውሎ ንፋስ ምክንያት በሰሜናዊ የሊቢያ ዴርና ከተማ ዙሪያ ያሉትን ሁለቱ ግድቦች መፍረስን እንደማጣቀሻ ያነሱ ሲሆን ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ(GERD) መጠን ደግሞ ከእነዚህ ጋር ሲነፃፀር “በ15,000 እጥፍ” ይበልጣል ብለዋል። ይሄ ግድብ የመሰጠንቅ አደጋ ቢደርስበት ሊያስከትል የሚችለው ጉዳት ከባድ ነው ብለዋል(አዩዘሀበሻ)።
ለተጨማሪ መረጃዎች join us
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የውስጥ መስመር   t.me/ayulaw
20.1K viewsAyu, edited  10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 13:37:37
ጥራቱ የተመሰከረለት ሻሎም የጥርስ ህክምና ክሊኒክ
አራት ኪሎ ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እና
ኮተቤ 02 ጆሲ  ሙል ላይ በሚገኙ ክሊኒኮች የተሙላ የጥርስ ህክምና እየሰጠ ይገኛል።
የሚሰጣቸው አገልግሎቱች
የቁሸሾ ጥርስ   ማጠብ
የተቡረቡሮ ጥርስ መሙላት
በአበቃቀል የተበላሹ ጥርሳችንን ብሬስ ማስተካከል (በተመጣጣኝ ዋጋ እና አከፋፈል አማራጮች )
የጥርስ ስር ህክምና
የድድ  መድማት ችግር ላለባቸው
ሁሉንም አይነት ሰው ሰራሽ ጥርስ አንተክላለን ፤ ለተተከለዉም ዋስትና እንሠጣለን
ታክመው የማይድኖ ጥርሶች እንነቅላለን
አድራሻ   ቁጥር-4 ኪሎ ቅድስት ስላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ
,ቁጥር 2 - ኮተቤ 02 ጆሴ ሞል
ለበለጠ መረጃ  0911424242
ስለ ጥርስ ንፅህና አጠባበቅ እንዲሁም የተለያዩ መረጃዎችን ለማግኘት Telegram join
https://t.me/shalomdentalclinic
https://t.me/shalomdentalclinic
https://t.me/shalomdentalclinic
17.9K viewsAyu, 10:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 12:32:59
1 ሺህ 554 የሲቪል ማህበራት ህልውናቸውን እንዲያጡ መወሰኑ ተጠቆመ
በቀድሞው አዋጅ መሠረት ተመዝግበው ዝርዝራቸው ያሉ ነገር ግን በአዲሱ አዋጅ ደግሞ ድጋሚ ያልተመዘገቡ 1 ሺህ 554 #የሲቪል ማህበራት ህልውናቸውን እንዲያጡ መወሰኑን የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ፋሲካው ሞላ አስታወቁ።

ዳግም እንዲመዘገቡ ከሚጠበቁት ድርጅቶች መካከል ሁለት ሺህ የሚሆኑት ግዴታቸውን የተወጡ መሆኑን የጠቆሙት ሃላፊው 1 ሺህ 554ቱ ግን የድጋሚ ምዝገባውን አላከናወኑም ብለዋል።

ሕጋዊነታቸውን ሳያረጋግጡ ስም ይዘው ብቻ መቀጠል ስለማይቻል ድጋሚ ምዝገባ ያላከናወኑ ድርጅቶቹ ላይ የሚወሰደው ርምጃ ከሐምሌ አንድ ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይሆናል ሲሉ አስረድተዋል።

ባለሥልጣኑ በሲቪል ማበረሰብ ድርጅቶች ላይ በሚያደርገው ክትትል 293 ድርጅቶች ሪፖርት የማድረግ ግዴታቸውን እንዳልተወጡ መረጋገጡን አመላክተዋል።

ሪፖርት ማድረግ የድርጅቱ ህልውና ስለመኖሩ አንድ ማረጋገጫ ነው ያሉት አቶ ፋሲካው፤ እስካሁን ሪፖርት ባለመደረጉ ቦርዱ ሚያዚያ 30 ባደረገው ስብሰባ 293 ድርጅቶች ሕጋዊነታቸው እንዲሰረዝ ውሳኔ ማስተላለፉን አስታውቀዋል።

አንድ ድርጅት ሲፈርስ የነበረው ሀብት ተመርምሮ እንደሚጣራ የተናገሩት ምክትል ዋና ዳይሬክቱሩ፤ በተላለፈው ውሳኔ መሠረት ከሐምሌ ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ያላቸውን ሀብት የማጣራት ሥራው ይጀመራል ብለዋል።

እንዲሰረዙ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ድርጅቶች እስከ ሰኔ 30 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ አሳማኝ ምክንያት ማቅረብ ከቻሉ ከስረዛው ነጻ የሚሆኑበትን መንገድ ማመቻቸቱንም አቶ ፋሲካው መግለጻቸውነ ከኢፕድ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ለተጨማሪ መረጃዎች join us
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
18.3K viewsAyu, edited  09:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 12:25:32
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ጉብኝት እያደረጉ ነው
የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቻይና ጉብኝት እያደረጉ ነው።

ፑቲን ከቻይናው ፕሬዚዳንት ዢ ጂንፒንግ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውን የሺንዋና ሬውተርስ ዘገባ ያመላክታል።

ዢ ጂንፒንግ የሃገራቱን ግንኙነት አድንቀው ቻይና የሞስኮ የምንጊዜም ወዳጅ ናት ብለዋል።

ሀገራቱን ወደ ተሻለ ምዕራፍ ለማሻገር ከፑቲን ጋር በቅርበት እንደሚሰሩም ገልጸዋል።

መሪዎቹ በውይይታቸው በሃገራቱ የሁለትዮሽና ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ላይ መምከራቸውም ተሰምቷል።

ከዚህ ባለፈም በሃገራቱ መካከል የተለያዩ የመግባቢያ ስምምነቶችን የተፈራረሙ ሲሆን፥ የጋራ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎም ይጠበቃል።

የአሁኑ የፑቲን ጉብኝት በዓመት ውስጥ ለሦስተኛ ጊዜ ሲሆን፥ ለአምሥተኛ ጊዜ የሩሲያ ፕሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡ በኋላ የመጀመሪያ የውጭ ሃገር ጉብኝታቸው ነው።
ለተጨማሪ መረጃዎች join us
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የውስጥ መስመር   t.me/ayulaw
17.4K viewsAyu, 09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 12:25:16
ልብ ይበሉ ሽልማቱ ቀድመዉ ለደወሉ 15 ሰዎች ብቻ ነዉ

እንሆ ሊያልቅ ጥቂት ፍሬዎች የቀሩትን  ተወዳጁን w26 pro max special watch  ሲያዙ እኛ ደሞ
original ሌዘር የ ኤርፖድ መያዣ በስጦታ መልክ ያሉበት በነፃ እናደርስሎታለን

አሁኑኑ ይደዉሉ 0954633900


በጥቂት ጊዜያት ዉስጥ ከፍተኛ ተቀባይነት ያገኘዉ ተች ሴንሰር የተገጠመለት ተቆጥረዉ የማያልቁ አገልግሎቶችን ከስልክ ጋር ተገናኝቶ መስጠት የሚችለዉ W26 pro max ለእናንተ

W26 PRO MAX Special with
Earbuds

ለወንድም ለሴትም የሚሆን ዘረፈ ብዙ ጥቅምች ያሉት smartwach ከ pro wireless earpode ጋር

   የራሱ ቻርጀር እና power bank ያለዉ
የልብ ምትዋን  ይለካል
ስፖርት ስንሰራ ምን ያህል ካሎሪ እንዳቃጠልን ያሳውቃል
ብዙ ሰአት ስንተኛ ይቀሰቅሰናል
ስልካችን ሲጠፋ ለመፈለጊያ ያግዘናል
ቴክስት መላክ እንዲሁም መቀበል የሚያስችል
ከስልክ ጋ በ Bluetooth ተገናኝቶ ስልክ መደወል እንዲሁም ማናገር ያቻላል
  wireless charger እና በሁለት አይነት የእጅ መሳርያ የቀርበ
  Blood Oxygen Detection
Stress & Mood Testing

አዲስ አበባ ዉስጥ ነፃ እና ፈጣን  የዴሊቨሪ አገልግሎት እንሰጣለን።

ዋጋ  2199 ብር ብቻ
       ፈጥነዉ ይደዉሉ

0954633900

  ወይም ስልክና አድራሻዎን
@AAU_Shop  ላይ ይላኩልን።

ተጨማሪ እቃዎችን ለማየት
@AAU_Market ን ይቀላቀሉ።
15.9K viewsAyu, 09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-16 10:43:36
በደቡብ ኢትዮጵያ እና የኦሮሚያ ክልሎች አዋሳኝ ዳግም በተነሣ ግጭት ሦስት ሰዎች መገደላቸው ተገለጸ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ጎርካ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል የምዕራብ ጉጂ ዞን ሱሮ ባርጉዳ እና ገላና ወረዳዎች አዋሳኝ አካባቢዎች፣ በታጠቁ ሰዎች መካከል ውጊያ እየተካሔደ መኾኑን ነዋሪዎች አስታወቁ፡፡

በምዕራብ ጉጂ ዞን የገላና ወረዳ አስተዳደር ሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢያሱ ጂኦ፣ ግጭቱ ትላንት ማክሰኞ መቀስቀሱንና አንድ አርብቶ አደር ሲገደል ሌላ አንድ መቁሰሉን አረጋግጠዋል፡፡

የኮሬ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ተፈራ ቦንዶራ በበኩላቸው፣ ከጃሎ እና ከሻፉለ ቀበሌዎች፣ ሁለት ሰዎች ሲገደሉ አንድ ሰው መቁሰሉን ተናግረዋል፡፡ በርካታ ሰብልም በገጀራ ቆራርጠው አበላሽተዋል ሲል አንድ የአዩዘሀበሻ ቤተሰብ ከላይ ያለውን ምስል አያይዞ ገልጿል (አዩዘሀበሻ)።
ለተጨማሪ መረጃዎች join us
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የውስጥ መስመር   t.me/ayulaw
17.4K viewsAyu, 07:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-11 18:05:17
ራያ
በአማራና በትግራይ ክልል መካከል የማንነት ጥያቄ ከሚነሳባቸው ቦታዎች አንዱ በሆነው አላማጣ ወረዳ በዛሬው እለት 03/09/2016 የህወሓት አመራሮች በራያ አላማጣ ከተማ ገረጀሌ ቀበሌ የሆስፒታሉን ሰራተኞች ስብሰባ በመጥራት ከሰኞ ጀምረው የተቋረጠውን የሆስፒታል ስራ እንዲጀምሩና እነሱም በቅርቡ ወረዳውን ሙሉ በሙሉ ተረክበው እንደሚያስተዳድሩ ኦረንቴሽን ሰጥተው የውሎ አበል 600 ብር ለእያንዳንዳቸው ሰጥተው ልከዋቸዋል ብለዋል። ሰራተኞቹ ከዚህ በፊት በመከላከያና በፌደራል አመራሮች ስራ እንዲጀምሩ ቢታዘዙ አንሰራም ያሉ ናቸው።በዚህ ስብሰባ አብዛኛው ከፍተኛ ባለሙያዎች እና ሌሎች ሰራተኞች ያልተገኙ ሲሆኑ ህወሃት በድብቅ መድባ በመረጃነት ሲያገለግሏት የነበሩ አካላት ናቸው በስብሰባው ላይ የተገኙት ሲሉ የአየዘሀበሻ የውስጥ ምንጮች ገልፀዋል። ስብሰባውን በተመለከተ የወቅቱ ኮማንድ ፖስት አመራሮች መረጃው ቢኖራቸውም ለመበተን የተሰራ ስራ የለም ሲሉ ነዉ የአዩዘሀበሻ ምንጮች የገለፁት። ከሳምንታት በፊት የህወሓት ታጣቂዎች በራያ አላማጣ ወረዳ ትንኮሳ በመጀመራቸው ምክንያት በርካታ የአላማጣ ነዋሪዎች ተፈናቅለው በቆቦ ከተማ ይገኛሉ[አዩዘበሀሻ]።
======================
For more upcoming news Join now and invite to others
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s

የውስጥ መስመር t.me/ayulaw
13.4K viewsAyu, edited  15:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ