Get Mystery Box with random crypto!

Agape-True Love

የቴሌግራም ቻናል አርማ agapetruelove — Agape-True Love A
የቴሌግራም ቻናል አርማ agapetruelove — Agape-True Love
የሰርጥ አድራሻ: @agapetruelove
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 188
የሰርጥ መግለጫ

True love is God and he gave us his only son Jesus Christ. Throught Jesus Christ we had an eternal life.

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-01-01 10:17:11 . ▷ ወንጌል ◁
. ተከታታይ ልበ-ወለድ

Written by Bethlehem Dejene

. #ክፍል_4
- - - - - - - - - - - - - - - -- - - - - -
➟ይህ ሁሉ ሲሆን ወንጌል አላስተዋለችም ግን ናኦድ እየተሰናከለባት ነበር ልብሷንም ቀይራ እንደጨረሰች የመስኮቷን መጋረጃ ዘጋችው፡፡ ናኦድ ተበሳጨና እዛው ቁጭ ብሎ መፃፉን ማንበብ ቀጠለ፡፡ ወንጌልም ስጦታዎቿን መክፈት ጀመረች፡፡

ቸኮሌት፣መፃፍ፣የፀጉርጌጥ፣ .....በስተመጨረሻም የመሰረትን ስጦታ ስትከፍተው ተለቅ ያለ አጀንዳ ነው፡፡ "አይ እማ ምን እንዳረግበት ነው ይህን የሰጠችኝ"? አለች የሚያምሩ ጥርሶቿን እያፈገገች ስትገልጠውም ተፅፎበታል፡፡ ቶሎ ብላም ወደ መጀመሪያው ገፅ አመራች እና ማንበብ ጀመረች፡፡ <ውቡ ከተማና መንገዶቹ ለልጄ ወንጌል ይድረስልኝ> ይላል፡፡ ሁለተኛውን ገፅ ከፍታ ማንበቧን ቀጠለች፡-
ልጄ በመጀመሪያ ከስሜ ልጀምር ፅጌሬዳ በርይሁን እባላለሁ ወላጅ እናትሽ ነኝ ፡፡

ይላል ወንጌልም ባነበበችው ነገር ግራ ተጋባችና የማዬ ስም መሰረት አደል እንዴ? የምን ፅጌሬዳ ነው? አለችና ንባቧን ቀጠለች ፡-
ውዷ ልጄ ይሄን ፁፍ እንድታነቢው 13 አመትሽን በጉጉት ነበር የጠበኩት፡፡ እናም ቀጣዩን ገፅ ከመክፈትሽ በፊት ለሚከተሉት መመሪያዎች ቃል ጊቢ- 1 የየቀኑን ንባብ በየቀኑ አንብቢ
2 የፅሁፉን ሀሳብ ተግባራዊ አርጊ
3 ጠንካራና ለተፈጠርሽለት አላማ ተገኚ ሁኚ ልጄ ለነዚ ትዛዞች ቃል ማትገቢ ከሆነ ቀጣዩን ገፅ እንዳከፍቺው፡፡አደራ እናትሽ ፅጌሬዳ ፡፡
ይላል ወንጌል ግራ ተጋባችና አጀንዳውን ዘግታ በፍጥነት ወደ መሠረት ክፍል አመራች ፡፡

መሠረት ክፍሏ የለችም ሁሉም ክፍሎች ፈልጋ አጣቻትና ወደሳሎን ሮጠች፡፡ ሳሎንም የለችም፡፡ የግርግዳ ሰአቱን ቀና ብላ ስትመለከት 3:40 ይላል፡፡ "የት ሄዳ ነው በዚ ምሽት?" አለች ጥልቅ በሆነ ግራ መጋባት "የዛሬው ሰርፕራይዝ ደሞ አያልቅም እንዴ? ብላ ወደ በሩ ስትጠጋ በሩ ክፍት ነው፡፡ ስትወጣም ጥቁሩ ረጅሙ ሰውዬ ፊት ለፊቷ ቆሟል.......

ይቀጥላል!

@agapetruelove
@agapetruelove
947 views07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-30 20:46:38 . ▷ ወንጌል ◁
. ተከታታይ ልበ-ወለድ

Written by Bethlehem Dejene

. #ክፍል_3
- - - - - - - - - - - - - - - -- - - - - -
➟በሩንም ከፍታ ስታይ ማንም የለም፡፡ "ጆሮዬ ነው ማለት ነው"? ብላ ንግግሯን ቀጠለች " እናም ወንጌል ከዚ በሇላ ትልቅ እንደሆንሽ ስለሚሰማኝ ዛሬ ትልቁን ስጦታሽን ሰጥሻለሁ፡፡ ብላ በነጭ ስጦታ ወረቀት የተጠቀለለውን ስጦታ ሰጠቻት ወንጌልም ደስ ብሏት ተቀበለች፡፡ ሁሉም የተለያዩ ስጦታ ሰጧት ኬክ ቆረሰች፡፡

የሚያምርም የልደት ጊዜ ካሳለፉ በሇላ ጓደኞቿ ወደ ቤታቸው አመሩ። ወንጌልም "እማ ደና "ደሪ ብላ ስጦታዎቿን ይዛ ወደ ክፍሏ አመራች፡፡ ወንጌል የመስታወት ፍቅር አለባት! ከዚ ፍቅሯ የተነሳ ልብሷን ስትቀይር ሳይቀር መስታወት እያየች ነው።ይሄንንም የምታረገው ብዙ ጊዜ የክፍሏን መጋረጃ ከፍታ በመስኮቷ መስታወት ነው። እንደለመደችው የመስኮቷን መስታወት እያየች ልብሷን ስታወልቅ ክፍሏ የበራው መብራት ከውጭ ወደ ውስጥ ያሳይ ነበር፡፡ ናኦድ ማታ ማታ በክዋክብት ድምቀት ታግዞ የማንበብ ልማድ አለው፡፡ ቤታቸው ከነወንጌል ቤት ጎን ነው፡፡ የነ ወንጌል ቤት ባለ 2 ፎቅ ስለሆነ የነ ወንጌልን ቤት ማየት የሚፈልግ ሰው እነናኦድ ጊቢ ሆኖ ልይ ቢል ሁሉም ነገር ይታያል፡፡

ናኦድ ከናቱጋ ጅማ ነበር ሚኖረው ጅማን ትቶ ከመጣና የዩኒቨርስቲ ትምርቱን ከጀመረ 2 አመታት ተቆጥረዋል እናቱም ያላንተ ማንም የለኝም ብቸኝነት ሊገለኝ ነው ብላ አሳምናው ጅማ ያለውን ቤቷን ሸጣ ናኦድጋ መታ አሁን የሚኖርበትን ቤት ገዛች ግን አዲሱ ቤቷ ብዙም አልቆየችም ምንም ግልፅ ሳታረግለት ይሄ ጥሩ እድል አይለፈኝ ብላ አሜሪካ ሄደች ናኦድ እናቱ ከሄደች ጀምሮ ብቸኝነቱን ሊረሳ ሚሞክረው በመፃፎቹ አማካኝነት ነው የዛን ቀንም እንደለመደው መፃፉን ይዞ ከቤት ሲወጣ ድንገት ወደ ወንጌል ክፍል መስኮት አነጣጠረ የወንጌል ክፍልም ፎቁ ላይ ስለሆነ በደንብ ትታይ ነበር ናኦድም በወንጌል ውበት ተገረመ ሲያያት ደስ አለችው በፍጥነት ወደ መስኮቱ ተጠጋ..........

ይቀጥላል!

@agapetruelove
@agapetruelove
617 views17:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-28 14:53:50 . ▷ ወንጌል ◁
. ተከታታይ ልብ-ወለድ

Written by Bethlehem Dejene

. #ክፍል_2
- - - - - - - - - - - - - - - -- - - - - -
➟መሰረት ድንጋጤ በተሞላ ንግግር " ወንጌሌ ምንም እንዳደብቂኝ አድርጌ አደል ያሳደኩሽ እስኪ የሆነውን ሁሉ ሳደብቂ ንገሪኝ" አለቻት በተማጽኖ ወንጌልም " እማ እኔ ቅድም ከነገርኩሽ ውጭ ምንም ምነግርሽ ነገር የለም" አለች "መሠረትም በይ ተነሺና ኮት ደርቢ ሆስፒታል እንሄዳለን" ብላ ብድግ አለች ወንጌልም ብድግ ብላ "እማ ግን ምንም አለመሆኔን ብዙ ሊያረጋግጡ የሚችሉ ነገሮች አሉ 1ኛ እግ/ር ከኔጋ ነበር ለዛም ይመስለኛል ከድንጋጤ ውጪ ሚሰማኝ ምንም አይነት ስሜት የሌለው ከተጠራጠርሽ ግን ሆስፒታል ለመሄድ ዝግጁ ነኝ ምክንያቱም ለኔ ያለሽ እምነት እንዲጓደል አልፈልግም " አለቻት መሠረትም "

አመሰግናለሁ ልጄ እግ/ር ካንቺጋ በመሆኑ ውስጥ ክፉ ባንቺ ህይወት እንደማያሸንፍ ስለተረዳሽ ግን ማረጋገጡ
አይጎዳም "አለቻት ወንጌልም "እማ የእምነታችን ማረጋገጫ እራሱ እግ/ር ነው አይተንና ዳሰን ያረጋገጥነውን ነገር እንዴት እምነት ብለን ልንጠራው እንችላለን? አለቻት መሠረትም ፈገግ ብላ "እሺ የኔ ውድ ልጅ ተስማምቻለሁ አሁን ልጆቹ አይምሽባቸው ነጬን ቀሚስሽን ልበሺና ልደትሽን እናክብር " አለቻት

ወንጌልም በትዛዝዋ መሠረት ረጅም ነጭ ቀሚሷን አርጋ ያንን ውብ ፀጉሯን ለቃ በአንፀባራቂ አይኖቿና ውበትን በተሞላው ፊቷ ታጅባ ከመሠረትጋ ወደሳሎን አመሩ ሁሉም ቆመው ሀፒ በርዝ ዴ እያሉ ተቀበሏት ሄዳም በተዘጋጀላት ቦታ ተቀመጠች መሠረትም ፊት ለፊቷ ቆማ ንግግር ማረግ ጀመረች "ዛሬ የወንጌል 13ተኛ አመት የልደት በአሏ ነው። የልደቷም ሴርሞኒ ብሎም እሷና እናንተ በነጭ ልብስ እንድትዋቡ ያረኩት ያለ ምክንያት አደለም ነጭ የንፁ ነገር ምሳሌ ነው፡፡

አሁን ያላችሁበት እድሜ ደሞ የወጣትነታቹ ጅማሬና አዳዲስ የተፈጥሮ ክስተቶች ወደናንተ ሚመጡበት እድሜ ነው ለምሳሌ ከዚ እድሜ ጀምሮ የፍቅር ስሜት ብሎም ፣አዳዲስ ተፈጥሮዎች.. ወደናንተ ይመጣሉ እና ወሳኙ ነገር እኝን ስሜቶች ለምን መጣቹ ማለት ሳይሆን እንዴት በስርአት ልምራቸው የሚለው ነው፡፡

እናም በዚ እድሜያቹ ነጭ ከሆናቹ ነገ ብቆሽሹ እንኳን ብዙ አመነችኩም ምክንያቱም የታነጻችሁበት መሠረት ወሳኝ ስለሆነ።ስለዚ "ብላ ንግግሯን ሳጨርስ የኮቴ ድምጽ ከውጭ ይሰማ ጀመር...........

ይቀጥላል......
SHARE SHARE SHARE SHARE
@agapetruelove
@agapetruelove
128 views11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-28 14:48:29 . ▷ ወንጌል ◁
. ተከታታይ ልብ-ወለድ

Present by #agapetruelove

Written by Bethlehem Dejene

. #ክፍል_1
- - - - - - - - - - - - - - - -- - - - - -
➟ቀኑ እሮብ ነበር ገና ከለሊቱ 11:30 የክፍሏ በር ተንኳኳ፡፡ ወንጌል ከ12 ሰአት በፊት የመነሳት ልምድ ስለሌላት የበሯ መንኳኳት አስደንግጧት በርግጋ ተነሳችና"ማነው"? አለች "ወንጌልዬ እኔ ነኝ" አለቻት ተነስታም በሩን ስትከፍት መሰረት ነጫጭ አበባዎች ታቅፋ ከበራፏ ቆማለች "እንዴ እማ ምንድነው የያሽው"? አለቻት በግርምት፡፡"ልጄ ላንቺ ዛሬ ትልቅ ቀን ነው መልካም ልደት ጣፋጯ ወንጌል"!ብላ ግንባሯን ስማ አበባውን ሰጠቻት፡፡ ወንጌልም በፈገግታ "አመሰግናለሁ እማ ዛሬ ለካ ልደቴ ነው ረስቼው ነበር" ብላ አበባውን ካስቀመጠች በሁዋላ ወደ መታጠቢያ ቤት አመራች::

12 አመታትን ልጅ የሚያስፈልገውን ሁሉ አጊንቶ እንዲያድግ አርጋ ስላሳደገቻት ያለ እድሜዋ እንደ ትልቅ ከመሆኗም ባሻገር የየቀን ህይወቷም በእቅድ የተሞላ ነበር፡፡ እናም ወንጌል ከመታጠቢያ ቤት ወታ የጠዋት ክንውኗን ከጨረሰች በሁዋላ ወደ ት/ቤት አመራች፡፡ ከትምርት ቤትም ስትመለስ የጊቢውም የቤቱም በር ክፍት ነው መሠረት ግን ያለ ወትሮዋ አልነበረችም። እማ የት ሄዳ ነው በሚል ሀሳብ ትንሽ ከተብሰለሰለች ወዲ ሮብ 11 ሰአት የቸርች ፕሮግራም ስላላት ወደዛው አመራች፡፡

ስትመለስ አምሽታ ነበር ጊቢውስጥም ያለወትሮው መብራት አልበራም ወደ ቤትም ስትጠጋ ጨልሞ በሩ ተዘግቷል ብዙ አንኳኳች መልስ የለም ከትንሽ ቆይታም በሁዋላ የጊቢውን በር ከፍታ ስትወጣ ከሁዋላዋ ትከሻዋ ሲያዝ ተሰማት ዞር ስትል አይታ የማታቀው ጥቁር ጺሙን ያንጀረገገ ረጅም ሰውዬ አፈናትና እጁ ላይ ወደቀች።

በዚያው ቅስፈት ነበር የጊቢው መብራት የበራው መሰረት ነጩን ክሬም ኬክ በሳህን ይዛ በሩን ከፍታ ስትወጣ ማንም የለም፡፡ ወደቤትም ተመልሳ "ልጆች ወንጌልን ሰርፕራይዝ እንደምናደርጋት ገብቷታል እንዴ?"አለች ሁሉም "ኧረ" አሉ አንገታቸውን እየነቀነቁ፡፡ ቤቱ በጣም አምሯል! ነጭ ምንጣፍ፣ ክሪስማሱ ላይ ያለው ነጭ የሚያበራው ዲምላይት፣ ነጬ ኬክ ላይ የተቀመጡት እንጆሪዎች፣ በነጭ ሽፍን የተጠቀለሉት ቸኮሌቶች....ብቻ የልደት ሴርሞኒው እንከን አቷል!

መሠረት በድጋሚ ተመልሳ ወጣች አሁንም ጊቢ ውስጥ ማንም የለም መጣራት ጀመረች መልስ የለም እናም ለልደቷ የተሰበሰቡት የወንጌል ጓደኞች ከመሰረትጋ አብረው ይፈልጓት ጀመር ዮዶት አሰብ አርጎ"ምን አልባት ሰው ስታጣ ተመልሳ ይሆን?" አለና ወደ ጊቢው በር አመራ በሩንም ሲከፍተው ወንጌል ዝርግት ብላ ወድቃ ተመለከተ ወዲያው የድንጋጤ ጩኸት ጮኸ፡፡ ሁሉም ተሰበሰቡና ወደቤት አስገቧት፡፡ መሠረትም አረጋግታቸው ፀለዩላትና ብዙም ሳይቆይ ነቃች፡፡

ገና አይኗን ከመግለጧ "ሰርፕራይዝ" አለች ሊና " ሰርፕራይዝ ነበር እንዴ? ይሄ ሁሉ" አለ ዮዶት ሊና ላይ አፍጦ " አረ ጌታን እኔ ማንም ሳይቀድመኝ ልበላት ብዬ እንጂ ከናንተ የተደበቀ ሰርፕራይዝ የለኝም" አለች ሁሉንም በዙር እያየች፡፡ ወንጌልም እራሷን አረጋግታ ስትመለከታቸው ሁሉም በነጭ ልብስ አጊጠዋል ቤቱም በልደት ሴርሞኒ አሸብርቋል፡፡"ሰርፕራይዝ ነበር እንዴ "? አለች በንዴት " ምኑ አሏት ሁሉም አፈናው ነዋ አለቻቸው "አፈና አለች መሠረት እቅፍ አድርጋት ወንጌልም "እራሴን ከመሳቴ በፊት የሆነ ደስ ማይል ሰውዬ አፍኖ እንደጣለኝ ትዝ ይለኛል ግን ምንም ሳያረገኝ ይሆን የሄደው?" አለቻቸው መሠረትም በጣም ተደናግጣ እጇን ይዛ መኝታ ክፍሏ አስገባቻት...

#ይቀጥላል....


@agapetruelove
@agapetruelove
549 views11:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-23 18:08:12

137 views15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-06 17:01:47

158 views14:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-28 18:09:45 አፀደከኝ ||Atsedekegn
ዳዊት ጌታቸው (Dawit Getachew / Dave )
192 views15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-22 08:38:54 #ህብረትን_መምረጥ

መልካም ፍፃሜ የመልካም ህብረት ውጤት ነው፡፡ ያላችሁበት ህብረት ወይ ይሰራችኀል ወይ ያፈርሳችኀል፡፡ከጠቢባን ጋር ከተጓዛችሁ ጠቢብ ትሆናላችሁ የሞኞች ጓደኛ ከሆናችሁ ግን ራሳችሁን ለጥፋት እያዘጋጃችሁ ነው፡፡

“ከጠቢባን ጋር የሚሄድ ጠቢብ ይሆናል፤ የሰነፎች ባልንጀራ ግን ክፉ መከራን ይቀበላል።”
— ምሳሌ 13፥20

እያንዳንድ የከበረ ፍፃሜ የተወለደው ከመልካም ህብረት ነው፡፡በተመሳሳይ ክብር አልባ የሆኑ ፍፃሜዎቸ የሚወለድት ከክፉዎች ህብረት ነው፡፡

አንድ ግልፅ እና አጭር ምሳሌ ልስጣችሁ
#ከ 5 ጎበዞች ጋር ከሆንክ 6 አንት ነክ
#ከ 5 ሰነፎች ጋር ከሆንክ 6 አንተ ነክ
#ከ 5 ሚፀልዩ ጋር ከሆንክ 6 አንት ነክ
#ከ 5 ሰባኪዎች ጋር ከሆንክ 6 አንተ ነክ
“አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 15፥33

ከዚህ ቀን ጀምሮ ጌታ መንፈስ ቅዱስ ራዕያችሁን ወደ የሚያፈጥን ወደ ትክክለኛ ህብረት ይምራችሁ!በኢየሱስ ስም አሜን!


Share. ... #ሼር አድርጉ
Join
@agapetruelove
@agapetruelove
397 views05:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-15 14:02:29
#divineservice1040
172 views11:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-03 04:00:08 #ቃሉን ይላክላችሁ


        ሀኪም ህመምተኛን አይፀየፍም። ምንድነው ያመመህ እያለ ቁስልህን አገላብጦ ያይኻል፣ልብስህን አውልቅ ብሎ አራቁቶ ይመለከትሃል ያክምሃል። እግዚአብሔር ከንፅሁነቱ የተነሳ ማንንም ሳይገፈትር ሳይፀየፍ ደዌያችንን ያክመናል። በፊቱ በንስሐ ስንራቆት ይመረምረናል ያነፃናል ይፈውሰናል።

        ሀኪሞች የአቅማቸውን ይነግሩናል። ተስፋ የለህም ህይወትህ የቀራት ሽርፍራፊ ቀን ነው ብለው ያሸብሩሃል። ለዘላለም በፀናው የእግዚአብሔር ቃል ህይወታችን ይበረታል ይታደሳል።

        “ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።” (መዝሙር 107፥20)
ወዳጆቼ የችግራችሁን ማዕበል የሚከፍል፤ ያስጨነቃችሁን የሚያስጨንቀውን፤ ትንሳኤን የሚያውጀውን፤ ሙት ነገራችሁን ጠርቶ የሚያስነሳውን፤ የደማችውን ነፍሳችሁን የሚያክማትን፤ ተስፋ የቆረጠችውን ልብ የሚያበረታላችሁን ቃሉን ይላክላችሁ። ከታላቁ ከእግዚአብሔር የተነሳ መፅናናት፣ መዳን፣ መሻገር ለቤታችሁ ለህይወታችሁ ይሁንላችሁ።

@agapetruelove

ቻናላችንን ያጋሩ / ይቀላቀሉ

@agapetruelove
@agapetruelove
1.4K views01:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ