2022-10-04 08:28:19
ከጠቀማችሁ!
፩) ለአንድ ሰው ከሁለቴ በላይ አይደውሉ። ምናልባት የማያነሱ ከሆነ ወይ አላዩትም፣ ወይ ለማንሳት የሚመች ቦታ አይደሉም፣ ወይ ደግሞ ማንሳት አልፈለጉም። ስለዚህ መልሰው እስኪደውልሎት ይጠብቁ።
፪) የተበደራችሁትን ገንዘብ አዳሪው ከማስታወሱ ወይም ከመጠየቁ በፊት ይመልሱ። ይሄ የታማኘነታችሁ ወይም የመልካም ስብዕናችሁ መገለጫ ነው። ምናልባት ምልሰቱ ከእስክሪብቶ፣ ከእስርሳስ ሊጀምር ይችላል።
፫) አንድ ሰው ሆቴል ሲጋብዛችሁ ውድ ምግቦችን እና መጠጦችን ከማዘዝ ይቆጠቡ። ምክንያቱም ያስገምታችኋል።
፬) "እስካሁን ለምን አላገባህ/ሽም፤ ልጆች ለምን አልወለድክ/ሽም፤ አይነት በጣም ደባሪ ጥያቄዎችን አይጠይቁ። በፈጣሪ ስም! ይሄ የእናንተ ችግር አይደለም።
፭) ከኋላችሁ የሚመጣ ሰው ካለ ሁሌም በሩን ከፍታችሁ አስገቡት። ሴት ትሁን ወንድ፤ ታላቅ ይሁን ታናሽ ማተር አያደርግም። ሰዎችን በማክበር እናንተ አትዋረዱም።
፮) ጓደኛችሁ ዛሬ የታክሲ ከከፈለ፣ ነገ እናንተ ለመክፈል ሞክሩ።
፯) ልዩነቶችን ያክብሩ። ለእናንተ 6 ቁጥር የመሰለው ለሌላው 9 ቁጥር ሊመስል ይችላልና ሐሳቡን እንደተቀናቃኝ ሳይሆን እንደአማራጭ ይውሰዱት።
፰) የሰዎችን ንግግር አያቋርጡ። እስኪጨርሱ በሚገባ አድምጠው የእርሶን ይቀጥሉ።
፱) ሰው ላይ አፊዘው ደስተኛ ካልመሰለ በድጋሚ እንዳትቀልዱባቸው። ምክንያቱም የእርሶ ሽንቁር ሌላውን ለማስገብት ትሞክራለች።
፲) በማንኛውም ነገር እርዳታ ስታገኙ "አመሰግናለሁ" ማለትን ይልመዱ።
፲፩) ሰውን በሕዝብ ፊት ያወድሱ፣ ለብቻ ይገስፁ።
፲፪) የሰው መልክ፣ ቁመና፣ ፀባይ፣ ውፍረት… ላይ ምንም አስተያየት የመስጠት በቂ ምክንያት የላችሁም። የምትሏቸው ነገር ቢኖር "ውብ ናችሁ" ብቻ ነው። የምትናገሩት መልካም ካልሆነ ግን ዝምታን ይልመዱ።
፲፫) ሰዎች አንድ ፎቶ ብቻ ሊያሳዯችሁ ፈልገው ስልካቸውን ከሰጧችሁ ወደፊት፣ ወደኋላ አያድርጉ። ምክንያቱም ቀጣዩ ምን እንደሆነ አታውቁም።
፲፬) ጓደኛችሁ የሕክምና ቀጠሮ እንዳላቸው ከነገሯችሁ ምን እንደሆነ በፍፁም እንዳትጠይቋቸው። "እንደሚሻልህ/ሽ ተስፋ አደርጋለው" ብቻ ይበሉ። የጤና እክላቸውን ተናግረው የሚረብሽ ኹኔታ ውስጥ እንዳትከቷቸው ተጠንቀቁ። እነሱ መንገር ከፈለጉ ያለናንተ ጥያቄ ይነግሯችኋል።
፲፭) ለዶክተር፣ ለባለስልጣን፣ ለባለፀጋ ክብር በምትሰጡት ልክ ለፅዳት ሰራተኛም፣ ለተራው ዜጋም፣ ለነዳዲያንም ስጡ። ሰውን መናቅ ብልግናችሁን ቢሆን እንጂ ሌላ ምንም አያሳይም። ሁሉንም ሰው በእኩል አይን ማክብር ትልቅነት ነው።
፲፮) ሰዎች ፊት ለፊት እየተመለከቱ ሲያናግሯችሁ ሞባይል፣ ኮምፒተር ወይም መጻሕፍትም ቢሆኑ ተተክላችሁ አትመልሱ። ተገቢ አይደለም። በወቅቱ ቀዳሚው መሆን የሚገባው ሰዎቹ እንጂ ቁስ አይደለም።
፲፯) ከረጅም ጊዜ በኋላ ጓደኛችሁን ወይም ወዳጃችሁን ካገኟችኋቸው እነሱ ለመናገር ካልፈቀዱ በስቀር ስለኑሯቸው፣ ስለሕይወታቸው ከመጠየቅ ተቆጠቡ።
፲፰) በቀጥታ ካልተመለከታችሁ በስተቀር በማያገባችሁ ጉዳይ አትግቡ።
፲፱) ሰዎች መንገድ ሲያናግሯችሁ የአክብሮት ምልክት በመሆኑ የፀሐይ መነፅራችሁን የማውለቅ ልምድ ይኑራችሁ። ከቃላት እኩል የአይን ግንኙነት ጠቃሚ ነው።
፳) ስለባለፀግነታችሁ በነዳዲያን ፊት ከመለፍለፍ ይቆጠቡ። በተመሳሳይ ስለልጆች በመሃኖች ፊት አያንሱ።
፳፩) ካልተጠየቃችሁ በስተቀር ለማንም ምክር ለመስጠት እትሞክሩ። "ባንተው ምክር ሄጄ፣ ባንተው አስጨከነኝ" እንዳለው ድምፃዊው አንተስ ምን እያደረክ ነው ካላችሁኝ ምናልባት ይሄ በጥቆማ ደረጃ ከተወሰደ ቢሆን እንጂ ምክር መሆን የሚችል አይመስለኝም።
┄┅┅┄┅✶ ✶┅┄┅┅┄
#Share
@Yenefekir
@Yenefekir
294 views05:28