Get Mystery Box with random crypto!

Habesha media

የቴሌግራም ቻናል አርማ yegtmmaebel — Habesha media H
የቴሌግራም ቻናል አርማ yegtmmaebel — Habesha media
የሰርጥ አድራሻ: @yegtmmaebel
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13
የሰርጥ መግለጫ

እንኳን ወደ ቻናላችን በሰላም መጡ
ከተቀላቀሉን
☞ግጥም
☞ተከታታይ ልብ ወለድ
☞የፍቅር ጥቅሶች
☞ቀልዶች
☞ወጎችን
☞ታሪኮችን
☞ኢትዮጲያዊነትን እንዘምራለን
ሀሳብ እና አስተያየትዎን እንዲሁም
ግጥም ለመላክ 👉 @joiamant22
ኢትዮጲያ ትቅደም 🙏

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-29 18:52:58
1.7K viewsSamuel Belete(bama), 15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:52:25 ህጻናትን ከትምህርት ቤት ወደ ጦርነት የትህነግ ሌላኛው ክፋት ሲጋለጥ

አልሸባብ በሶማሊያ ጎዳናዎች ላይ ህፃናትን ፈንጂ አስታጥቆ በማሰማራት ጥፋት እንደሚያደርስ ሁሉ የትህነግ የሽብር ብድንም እድሜያቸው ከ15-19 ያሉ  ታዳጊዎችን በመመልመል ወደ ጦርነት እየማገዳቸው ይገኛል።

አሸባሪው ትህነግ እድሜያቸው ከ15-19 የሆኑ ታዳጊዎችን ደብተርና እስኪቢርቷቸውን አስጥሎ ክላሽ በማስታጠቅ ወደ ጦርነት እሳት እየማገዳቸው ይገኛል።

ለአሸባሪው ትህነግ ዓለማ ለጥቂት ሰዎች የግል ስልጣንና ጥቅም ብቻ ሲባል ህጻናት ትምህርታቸውን አቋርጠው ጫካ ገብተው እንዲያልቁ ተፈርዶባቸዋል፡፡

ህፃናትን ለጦርነት መመልመል በአለም አቀፍ ህግ እና በኢትዮጵያ ህግ ከፍተኛ ወንጀል ነው፡፡ እናም ድርጊቱ ከሞራል ብቻ ሳይሆን ከሕግም አኳያ ይታያል፡፡ ህጻናት ለወታደርነት  መልምሎ ስልጠና መስጠት እና መጠቀም የተባበሩት መንግስታት ስምምነትን እንደ መጣስ እና እንደ የጦር ወንጀል ይቆጠራል፡፡ ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት በጦርነት ውስጥ ምንም አይነት ተሳትፎ እንደማይኖራቸው በአለም አቀፍ ህግ በግልጽ ተደንግጓል።

አትዮጵያ ባፀደቀችው የአለም አቀፍ ህጎች ውስጥ ህፃናትን ለጦርነት መጠቀም ፤የጦር፤ መሳሪያ ማስታጠቅ እና ለጦርነት መመልመል የተመለከቱ የህግ ማህቀፎች መካከል African charter on the rights and welfare of the child አንቀፅ 22 ንዑስ (2)፤- ማንኛውም ልጅ  በጦርነት ውስጥ በቀጥታ ማሳተፍ የለበትም፡፡  ንዑስ ( 3 )፤ በግጭቶች ውስጥ በተለየ መልኩ ለህፃናት ጥበቃ ያስፈልጋል ይላል፡፡ The convention of right of child (UNCRC) አንቀፅ  38 ንዑስ (2 )፤ 15 አመት ያልሞላቸውን በጦርነት ተሳትፎ መከልከል፤  ንዑስ( 3) ፤ 15 አመት ያልሞላቸውን ወደ ጦር ሃይል ከመቅጠር መቆጠብ እንደሚገባ ያትታል፡፡
እነዚህ የጸደቁ ስምምነቶች በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግስት አንቀጽ13 (2) እና 9 (4) መሰረት የሀገሪቱ ሕግ አካል በመሆናቸው መንግስት እና ሌሎች አካላት የሕገ መንግስቱን እና የስምምነቶችን ድንጋጌዎች ከማስፈጸም አኳያ አስተዋጽኦ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡
የሀገራችንም የተለያዩ ሕጎች የህፃናትን በጦርነት ማሳተፍ እንደሚያስጠይቅ ደንግገዋል፡፡ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የጦር መሳሪያ አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ 1177/2012ዓ.ም አንቀ 4 የጦር መሳሪያ ከተፈቀደለት ሰው /አካል ውጪ የጦር መሳሪያ እንዲይዝ ያሰለጠነ በወንጀል ያስጠይቃል፤ እንዲሁም በአንቀፅ 8 ንዑስ 1  መሰረት የመሳሪያ ተጠቃሚውን ልዩ  ሁኔታ ሳያገናዝብ የጦር መሣሪያውን ያስታጠቀ በዚሁ አዋጅ አንቀፅ 22 ነዑስ 11 ላይ የህግ ሰውነት ባላቸው ቡድን ወይም ተቋም  ከሆነ በወንጀል ተጠያቂ ያደርጋል፡፡

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 36 ላይ የሕጻናት መብትን አስመልክቶ የተቀመጠ ግንጋጌ ይገኛል፡፡ ይህ ድንጋጌ ማንኛውም ሕጻን  ጉልበቱን ከሚበዘብዙ ልማዶች የመጠበቅ፣ በትምህርቱ፣ በጤናው እና በደህንነቱ ላይ ጉዳት የሚያደርሱ ሥራዎች  እንዲሰራ ያለመገደድ ወይም ከመሥራት የመጠበቅ መብት እንዳለው አስቀምጧል፡፡ ሕጻናትን የሚመለከቱ እርምጃዎች በሚወሰዱበት ጊዜም የሕጻናት ደህንነት በቀደምትነት መታሰብ እንዳለበት አጽንኦት ይሰጣል፡፡

በ1996 ዓ.ም የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 270/ኀ/ መሰረት ማንም ሰው በጦርነት  ግጭት ወይም በጠላት ወረራ ጊዜ የዓለምአቀፍ ሕግ ድንጋጌዎችን እና የዓለምአቀፍ የሰብአዊነት ሕግጋትን በመጣስ በሰላማዊ ሕዝብ ላይ ጉዳት ለማድረስ በማደራጀት፣በማዘዝ ወይም ድርጊቱን በመፈጸም ወይ ምበማናቸውም ሌላ መንገድ ዕድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች የሆኑ ልጆችን በጦርነት ውስጥ እንዲሳተፉ ለማድረግ ለወታደራዊ አገልግሎት አባልነት የመለመለ እንደሆነከ 5 ዓመት እስከ 25 ዓመት ለመድረስ በሚችል ጽኑ እስራት ወይም ነገሩ  በጣም ከባድ በሆነ ጊዜ በዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ወይም በሞት ሊያስቀጣ የሚችል መሆኑ ተደንግጎ እናገኘዋለን፡፡

የትህነግ የሽብር ብድን የዓለም አቀፍና የሀገሪቱን  ህጎች በጣሰ መልኩ እድሜያቸው  ከ18 በታች የሆኑ ህጻናትን ለጦርነት እየተጠቀመ እንደሆነ በግልጽ ታውቋል:: ይህ ጉዳይ ለትውልድ ተቆርቋሪ ነኝ የሚል ሁሉም  በደረጃ ካላወገዘና ለህግ ተጠያቂ ካለደረገ እየተባባሰ መምጣቱ አይቀርም ኢ-ህገመንግስታዊ በመሆኑ ‹‹ሳይቃጠል በቅጠል›› ሊባል ይገባል፡፡

#አዲስ መረጃ
1.6K viewsSamuel Belete(bama), 15:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 18:37:34 የአሸባሪው ትህነግ ተከፋይ አክቲቪስቶች ተጋለጡ

   አሸባሪው ሕውሓት ከኢትዮጵያ ጠል አገራት ጋር በማበር ኢትዮጵያን ለማፈራረስና ለመበታተን በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል። በስልጣን በነበረበት ወቅት ለክፉ ቀን ብሎ ያስቀመጣቸው የክፋት ተካፋዮቹ አሁንም እኩይ ዓላማውን እያገዙ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማፈራረስ ታጥቀው ተነስተዋል።

  ትህነግ   በርካታ ኢ-ሰብአዊ ድርጊት ሲፈጽም ህጻናትን ወደ ጦር እሳት ሲማግድ ዝም ጭጭ በማለት ትህነግ በግፍ ከተሞችን ሲቆጣጠርና ንጹሃን ኢትዮጵያውያንን ሲያጎሳቁል። አይተው እንዳላዩ እያለፉ ነገር ግን ትህነግ ኢትዮጵያን በማፈራረስ ሂደት ውስጥ ሁሉ መምቻ አቀባዮች ናቸው።

  ብዙዎች እንደሚስማሙበት ጦርነቱ ከትህነግ ጋር ብቻ ዐይደለም ጦርነቱ ከበርካታ ኢትዮጵያን ከማይፈልጉ ሐይሎች ጋር ነው።

  ከሰሞኑ የአሸባሪው ትህነግ የሀሰተኛ መረጃ  አሰራጭ የሆኑ የውጭ ተከፋዮችን ኢትዮጵያዊያን እና የኢትዮጵያ ወዳጆች እኩይ ተግባራቸውን እያጋለጡ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ መንግስት በተደጋጋሚ ለሰላም እጁን ቢዘረጋም አሸባሪው ትህነግ በአጸፋው አጥፍቶ ማጥፋቱን ቀጥሎበታል። በእርግጥ የትህነግ መሪዎች ኢትዮጵያ ስትፈርስ ማየት እንፈልጋለን ሲሉ ተደምጠዋል። በነዚህ ጥቂት ቀናት ውስጥ በኢትዮ 360 ብቻ የተሰሩ ፕሮግራሞችን ብንመለከት እንኳ እውነትም ትህነግ እስከ አፍንጫው የታጠቀው የሐሰት ፕሮፖጋንዳ አምራች አለው ለማለት እንገደዳለን የኢፌደሪ ጠቅላይ ኢታማጆር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ "ጦርነት ተገደህ የምትገባበት ጉዳይ ነው ሳይሆንልህ የምትገባበት ነው። በሰላም የመጣ በሰላም እናስተናግዳለን ሲሉ" በንጻሬው ትህነግ መሪዎች በራሳቸው አንደበት ቢናገሩት የማይሰሙት የትህነግ መሪዎች እንደ ኢትዮ 360 ባለው ሚዲያቸው "ጦርነቱን ሕዝባዊ የማድረግ አባዜ የሚል" ለውይይት የማይበቃ ተራ ትርክት አንስተው ጉንጫቸውን ሲያለፉ ብዙ ኢትዮጵያዊ ታዝባል መቼም ጦርነቱ ከትግራይ ህዝብ ጋር እንዳልሆነ ይታወቃል ነገር ግን የትህነግ ሚዲያዎች እንዲህ ይላሉ።

የነገሩ ዋነኛ ኢላማ ኢትዮጵያና መንግስቷ ናቸው። አላማው ደግሞ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህዝቧ ላይ ስነ ልቦናዊ ጫና በማሳደር የትህነግን የመከፋፈል ትርክት እንዲቀበሉ ማድረግ ነው።

የትህነግ ሚዲያዎች የሚሉትን ማብራራት አስፈላጊ አይደለም እርሶም ለምን እንዲህ ያደርጋሉ ብለው ሊጠይቁ ይችላል መልሱ ቀላል ነው። ትህነግ የኖረው በውሸት የሚኖረው በውሸት ስለሆነነው  የሚጠነሰስሳቸው የሽብርና የማባላት ስልቶች ሲሰሩለትን ይሁንታ ሲጋገኙለትም ታዝበናል።

የትህነግ ሴራ አጋዦች በነ ኢትዮ 360 አይበቃም ወደ ባህር ማዶም ይሻገራል። የግድቡ ሶስተኛ ጉር ሚሌት ሲከናወን "እንኳን ደስ አላችሁ ያለው ማርቲን ፕላውት አቋም እንደሌለው እንደእስክንድር ነጋ ሆኖ ሰንብቷል። ቅርጹን እንደ ውኃ እየቀያየረ ኢትዮጵያን ሲወጋ ትህነግን ሲያባብልና ሲደግፍ የትህነግን ደም አፋሳሽ አጥፊ ከፋፋይ ድርጊት ሲያራግብ እየታየ ነው።

የትህነግ እሳቤና ዓለማ የሚናፈሰው በነ ማርቲን ፕላውን በነ ሀብታሙ አያሌው በነ ኤርምያስ በነ ቴዎድሮስ ጸጋዬ  ብቻ አይደለም ከሰሞኑ ራሽድ አብዲ፣ አሌክስ ድዋል፣ ሸትል ትሩንቮል፣ ዊሊያም ደቪሰን ያሉ ተቀጣሪ አክቲቪስቶችን አገር ወዳዶች ሁሉ ሴራቸውን እየተከታተሉ እያጋለጡ ነው።

  ይህን ለጆሮ የሚከብድ ኢትዬጲያን የመጥላት ጉድ ከሰሙ ብኋላ ኢትዮጵያውያን የትህነግ ደጋፊዎቹ እነ ሐብታሙስ እሺ የኖጮቹ አክቲቪስቶችስ ምን ፈልገው የሚል ጥያቄ ካነሱ ልክ ኖት፥ አልተሳሳቱም። ነገር ግን መልሱ ቀሊል ሆኖ እናገኘዋለን የኢትዮጵያ ስላም መሆን ለእየርሱ እንጀራ ማጣት ለትህነግም ኅልውናውን ማሳጣት ሲሆን ህጻናት ከትምህርት ቤት ወደ ጦርነት መሄዳቸው በነሱ መስፈርት የሚለካ ነገር አይደለም። የትህነግ አገር የማፈራረስ ስልት ውስብስ ነው።

#አዲስ መረጃ
1.4K viewsSamuel Belete(bama), edited  15:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 17:22:29 ዋናው ስቲዲዮ
ሰበር ዜና


1.5K viewsSamuel Belete(bama), edited  14:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 15:06:39
WHO is the bigger Liar
1.6K viewsSamuel Belete(bama), 12:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 20:31:53
Picture of the day
1.9K viewsSamuel Belete(bama), 17:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 19:15:38 ከደባርቅ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት።

የደባርቅ ከተማ አስተዳደር የፀጥታ ምክር ቤት በወቅታዊ የፀጥታ ስጋት አስመልክቶ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።

1ኛ= በከተማችን የሚገኘው የተፈናቃይ መጠለያ ነዋሪ ከ12:00 በሗላ ወደ ውስጥም ሆነ ወደ ከተማ መግት ከልክሏል።

2ኛ= የከተማችን ባጃጅ ተሽከርካሪ ከምሽቱ 1:00 በሗላ መንቀሳቀስ አይችልም ይህን ሲያደርግ የተገኘ ባለባጃጅ ህጋዊ እርምጃ ይወሰድበታል።

3ኛ=መላው የከተማችን ማህበረሰብ በአደረጃጀቶች አካባቢውን ሌትና ቀን ከሰርጎገብ በንቃት እንዲጠብቅ።

4ኛ=ፀጉረ ልውጥ ሲያጋጥም በፍጥንት ለህግ አካል ጥቆማ በመስጠት በህግ ቁጥጥር ስር እንዲውል ማድረግ።

5ኛ=የከተማችን ባለሆቴሎች እና ባለአልጋ ቤቶች ማንነቱ ያልታወቀ አንጋች በድርጅታችሁ ሲጋጥማችሁ ለህግ አካላት ጥቆማ እንድትሰጡ።

6ኛ=በከተማችን ያላችሁ የቤት አከራይዎች ያከራያችሁትን ግለሰብ ማንነትቱን ለይታችሁ እንድታከራዩ የተከራየውንም በመረጃ ፎርም ሞልታችሁ ለፀጥታ ጽ/ቤት እንድታሳውቁ።

እነዚን የውሳኔ ሀሳቦች በማጥስ ማንኛውም አካል ህጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ በጥብቅ መልዕክቱን ያስተላልፋል።

የደባርቅ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን መረጃ።
1.9K viewsSamuel Belete(bama), edited  16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 18:55:23
ህወሓት ሕፃናትን ለውትድርና ሲያሰልፍ የባይደን አስተዳደር ዝምታን በመምረጡ ተወቀሰ
 
በካሊፎርኒያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ታዋቂው መምህርና የሕግ ምሁሩ ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም በትዊተር ገፃቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፥ አሸባሪው ህወሓት ሕፃናትን በጦር አውድማ ሲያሰልፍ ዝምታ የመረጠውን የባይደን አስተዳደር ኮንነዋል።
 
ወትሮም ቢሆን ለሕፃናትና ታዳጊዎች ግድ የሌለው አሸባሪው ህወሓት በአካልና በአዕምሮ ያልጠነከሩ ሕፃናትን ለውትድርና መልምሎ ወደ ጦር አውድማ እየማገዳቸው ይገኛል።
 
በሰብዓዊ መብት፣ በፕሬስ ነፃነት እና በአየር ንብረት ለውጥ ተሟጋችነታቸው የሚታወቁት ዶክተር ቫን ቴራራ በበኩላቸው፥ አሸባሪው ህወሓት ሕፃናትን ለጦርነት እየተጠቀመባቸው እንደሚገኝ ሰሞኑን በትዊተር ገፃቸው ይፋ ማድረጋቸውን የኢዜአ ዘገባ አስታውሷል።
 
ዶክተር ቫን ቴራራ በጽሑፋቸው፥ የህወሓት እኩይ ድርጊት በአስቸኳይ መቆም እንዳለበት ነው ያሳሰቡት።
 
ሕፃናትን ለውትድርና መጠቀም የጦር ወንጀል በመሆኑ ድርጊቱን የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሊያወግዘው እንደሚገባም ነው የተጠቆመው።
1.7K viewsSamuel Belete(bama), 15:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 18:43:05
Hundreds of thousands of Child soldiers who were recruited by the #TPLFTerrorisGroup to fight in the conflict are seeking assistance.Exonerate #Ethiopia by opposing use of #childsoldiers #DisarmTPLF #TPLFBelligerenceMustBeCondemned #TPLFisthecause #EthiopiaPrevails
1.5K viewsSamuel Belete(bama), 15:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-28 18:26:57 ሰበር_ዜና ጀግናው የመከላከያ ሠራዊት፣ ኮማንዶ፣ ልዩ ኃይልና ፋኖ በጥምረት የቆቦን ከተማ መልሶ ተቆጣጠረ። የአራቱንም ጥምር ምት መቋቋም የተሳነው የህወሓት ጀሌ ቆቦን ለቆ
ወደ አላማጣ ጉዞ ጀምሯል። እንደገና ዛሬ 4 ሰዓት አካባቢ በግዳን በኩል ለመግባት ሞክሮ አከርካሪውን ተመትቶ ተመልሷል።

ኮማንዶዎች የወልዲያን ዩኒቨርስቲ መግቢያ በር፣ ወደ ባህርዳር የሚወስደውን መንገድ ማንም እንዳይገባና እንዳይወጣ ከዘጉ በኋላ ነው የቆቦ ኦፕሬሽን የተከናወነው። የምሥራቁ ኮከብ ፋኖ ምሬ ወዳጆ ከመከላከያና ከልዩ ኃይል ጎን ሆኖ የሰራው  ጀብዱ ታሪክ የሚዘክረው ይሆናል።

-አሁን ግምባር ላይ ያለው ወኔ፣ እልህና ቁጭት የሚገርም ነው። መከላከያ ነፍሱን እየሰጠ ነው፤ ልዩ ኃይሉ አጥንቱን እየከሰከሰ ነው፤ የምሥራቅ ዐማራ ፋኖ ደሙን እያፈሰሰ ይገኛል። ከኛ የሚጠበቀው ሞራል፣ ስንቅ፣ ደጀንነት ብቻ ነው።

-ነገርግን እዚህ የሚኖረው በስነልቦናው ስልብ የሆነው የፌስቡክ ጀሌ መከላከያን ያህል የሀገር ተቋም ሲሳደብ፣ ሲያንቋሽሽ፣ ሲሳለቅ ይውላል፥ ኧረ ሞራል ወዴት አለሽ? በምን ሞራል ነው ደሙን እያንጠባጠበ፣ ላቡን እያፈሰሰ፣ ሸለቆ ውስጥ አጥንቱን እየከሰከሰ ያለ ወታደር የሚሰደበው?
ቤተሰብ፣ ሃይማኖትና ትምህርት ቤት የሚባሉ ተቋማት ይህን ትውልድ እንዴት አድርገው አስተምረው ቢያሳድጉት ነው እንዲህ ያለ የተሳሳተ ትውልድ (wrong generation) የተፈጠረው?

በፊት መከላከያ የቅጥር ማስታወቂያ ሲያወጣ ተመዝገቡ፣ ዐማራ በልኩ ውክልና ያግኝ፣ ዘመናዊው መሳሪያዎችና ሥልጠናዎች የሚገኙት ከዚህ ተቋም ነው ስንል "አይሆንም" ብለው ሰፊ ዘመቻ ከፍተው የሚመዘገቡ ጠፍቶ ክልሉ የሚያስመዘግበው ሰው አጥቶ እንደነበር አስታውሳለሁ።  የትናንቱ ረስተው ዛሬ ደግሞ በመከላከያ ተከዳን የሚል ትናንትና ውስጥ ይገኛሉ። አሁንም የምመክረው ወቀሳውን ከፖለቲካ አመራሩ ላይ አድርጉ እጃችሁን ከመከላከያ ላይ አንሱ!

-በጣም ያስገረመኝ ወያኔ ከጦርነቱ በፊት  በድጅታል ሚዲያ ሊያግዛት የሚችል ይህን ያህል አማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ግብረ ኃይል ታዘምትብናለች ብዬ በፍጹም አልጠበቅሁም ነበር።

የሆነው ሆኖ ባንዳ አንገቱን ደፍቶ ይቀራል የኢትዮጵያ ሕዝባዊ ሠራዊት ድል ማድረጉን ይቀጥላል።
ከታደለ ጥበቡ የቴሌግራም ገፅ
1.8K viewsSamuel Belete(bama), edited  15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ