Get Mystery Box with random crypto!

ጌታዬ ሁለመናዬ!

የቴሌግራም ቻናል አርማ yarieddessale — ጌታዬ ሁለመናዬ!
የቴሌግራም ቻናል አርማ yarieddessale — ጌታዬ ሁለመናዬ!
የሰርጥ አድራሻ: @yarieddessale
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.11K
የሰርጥ መግለጫ

ስለ አንዲት፡ ቅድስት፡ ሐዋርያዊትና ኩላዊት ቤተ-ክርስቲያን ምንነትና ምን እንደምታስተምር ለማወቅ፣ ስለ ቤተክርስቲያን ታሪክ፤ ስለመላዕክት፣ ስለቅዱሳን-ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ፣ ተዓምራት፤ የር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስን ወቅታዊ ትምህርቶች፤ መንፈሳዊ ፊልሞችን ሁሉ በቀላሉ ያገኙበታል፡፡ #ክርስትናን_ክርስቶስን_እንወቅ፡፡
“አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፡፡” (ማቴ. 6:33)

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-08-29 01:40:45
ማሳሰቢያ፡-

የክቡር አባ ሬንዞ ማንቺኒ ስርዓተ ቀብር ሽኝት ሰኞ እለት በዱቦ ሉርድ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ከ 4:00 ሰዓት ጀምሮ ይከናወናል።

ክቡር አባ ነፍሶትን እግዚአብሔር አምላክ በአብርሃም በይስሃቅ፣ በያዕቆብ እቅፍ ከቅዱሳን ጋር ያኑርልን፤ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ሁሉ መጽናናትንም ይላክልን።አሜን



https://t.me/YariedDessale/5210
451 viewsedited  22:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 13:03:51


#ዜና_ዕረፍት



ክቡር አባ ሬንዞ ማንቺኒ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ የህክምና ዕርዳታ በሶዶ ክርስቲያን ሆስፒታል ሲደረግላቸው ቆይተው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩን (አረፉ)።

ነፍስ ይማር!!



''መልካሙን ገድል ተጋድየአለሁ ሩጫዬንም ጨርሻለሁ፣ ሃይማኖቴን ጠብቄአለሁ፣ ከእንግዲህ ወዲህ የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶ ይጠብቀኛል፡፡ ይህንንም አክሊል ቅን ፈራጅ የሆነው ጌታ በዚያን ቀን ይሰጠኛል፡፡ ይህንንም ለእኔ ብቻ ሳይሆን የእርሱን መገለጥ ለሚወድዱ ሁሉ ይሰጣቸዋል”
(2ኛ ጢሞ 4: 6-8)


የክቡር አባን ነፍስ ጌታ አምላክ ከቅዱሳን ጋር ያኑርልን!!

አሜን አሜን


https://t.me/YariedDessale/5209
977 viewsedited  10:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 21:07:23

#የአዲስ_ዓመት_ስጦታ!!




የሶስት ቀን ሱባዔ ግብዣ

#ቦታ፡ ሞጆ ሱባዔ ማዕከል

#ቀን፡ ከመስከረም 6 - 8/2015 (አርብ ከሰዓት በኋላ ጀምሮ፣ ቅዳሜ ሙሉ ቀን ውሎ እሁድ ከሰዓት በፊት በቅዳሴ የሚጠናቀቅ፡፡

ሱባዔውን ለመሳተፍ የሚያስፈልገው #ፍላጎት ብቻ ነው፡፡

ፍላጎት ያላችሁ ከካቶሊካውያን ወጣቶች ሁሉ ተጋብዛችኋል፡፡

ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቅድሚያ ለመጣ ቅድሚያ ይሰጠዋል የሚለው መርህ እንከተላለን፡፡

ለበለጠ መረጃ እንዲሁም
#ለመመዝገብ፦
+251922944936 ይጠቀሙ፡፡



ለተለያዩ  የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዎች፡ እንዲሁም አዳዲስ ዜናዎችን ለማግኘት ይረዳዎት ዘንድ ከዚህ በታች ያለውን የቴሌግራም ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑን!!




https://t.me/YariedDessale/5208




The Universal Catholic Church Teaching Channel.
957 viewsedited  18:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-24 04:19:36
#ለ200_የጉምዝ_ማህበረሰብ የመጀመሪያ ምስጢረ ጥምቀትና ምስጢረ ሜሮንን
በድብጣ ቅ/ሚካኤል ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ተሰጠ።

በባህር ዳር - ደሴ ሀገረ-ስብከት በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተከል ዞን በድባጤ ወረዳ የባህር ዳር ደሴ ሀገረ-ስብከት ሐዋሪያዊ ሥራዎች ቢሮ ዋና አስተባባሪ የሆኑት በክቡር አባ ደሳለኝ ኃይሌ አማካኝነት በተሰጣቸው ውክልና መሠረት በአዲሱ የቅዱስ ሚካኤል ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን ለ200 የጉሙዝ ማህበረሰብ በፍልሰታ ለማርያም ቀን (ነሐሴ 16/2014 ዓ.ም) ከድባጤ፣ ከባኑሽ፣ ከዶሽ ፣ ከሲርበን እና ዋርካ ሰፈር የተውጣጡና የተዘጋጁትን ከህጻን እስከ አዋቂ ምስጢረ ጥምቀትንና ምስጢረ ሜሮንን ተቀብለዋል።

ከዚህም በተጨማሪ በመተከል ዞን በድባጤ ወረዳ ለተከታታይ 15 ቀናት ከነሐሴ 1-15/2014 ዓ.ም ለ50 ወጣቶች በቋሚነት መንፈሳዊ ህይወታቸውን እንዲያጠናክሩ ጥልቅ የሆነ የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት በመተከል ዞን በድባጤ ወረዳ በቅዱስ ሚካኤል ካቶሊክ ቤተ-ክርስቲያን ግቢ ውስጥ በክቡር አባ ደሳለኝ ኃይሌ አማካኝነት ተሰጥቷቸዋል።

አዘጋጅና አቅራቢ፦ ያሬድ ደሳለ

የባህር ዳር ደሴ ሀገረ-ስብከት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ፡፡

(ባህር ዳር)

https://t.me/YariedDessale/5207

ምንጭ፦

https://www.facebook.com/111985127170625/posts/pfbid06Wsxxyq8QGqbCrdZZQGSCdDRpQG6uB5KeVk1iSfsru59teiqEuuLa7m2WSBcaAkml/?app=fbl
654 views01:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-23 22:36:20
474 views19:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-30 15:59:24 Don't forget to pray everyday!!


https://t.me/YariedDessale
271 viewsedited  12:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 22:24:40 AM PROUD TO BE A ROMAN CATHOLIC PRAISE THE LORD, AMEN.
427 views19:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 09:56:18 #ጌታ_ሆይ_አንተ_ማን_ነህ?



#ጳውሎስ ከዚህ ቀደም የክርስቲያኖች ጠላት እና አሳዳጅ ነበር።

(ር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስ)




#ጳውሎስ_በንጉሱ_ፊት_መሰከረ:

#ጳውሎስ ከዚህ ቀደም የክርስቲያኖች ጠላት እና አሳዳጅ ነበር። አሁን ግን በአጭሩ በክርስቶስ ላይ ያለው እምነት በሚፈተንበት ሁኔታ ላይ ነው። ከ25 ዓመታት በሗላ ሐዋርያው ከክርስቶስ ጋር መገናኘቱን እንደጥሩ አጋጣሚ ይቆጥረዋል።

ጳውሎስ ክርስቲያኖችን ሲገድል እንደነበር ይናራል፣ አንድ ቀን ይህንኑ ለማድረግ ወደ ደማስቆ እየሄደ እስካለበት ጊዜ ድረስ። በዚያን ቀን ከጸሀይ የደመቀ ብርሃን በእርሱ እና በአጋሮቹ ላይ በራ (ሐዋ 26፡13) እርሱ ብቻ ግን “ድምፅ” ሰማ፤ የክርስቶስን ድምፅ እርሱን በስሙ ጠርቶ ሲያናግረው ሰማ።

#ሳውል!_ሳውል!
በማስተዋል ይህንን ክስተት እናጢነው፤ ጌታ ሳውልን በስሙ በመጥራት እሱን በደንብ እንደሚያውቀው እንዲገነዘብ ያደርገዋል። ማን እንደሆንህ እና ምን ልታደርግ እንደሆነም ሳይቀር አውቃለሁ በቀጥታም እያናገረው ይሄንን ይለዋል። ጌታም ሁለት ጊዜ ጳውሎስ በሚል በልዩ ሁኔታ ጥሪውን በሚያመለክት ስም ልክ ከዚህ ቀደም ከሙሴ ጋር (ዘጸ 3:4) ከሳሙኤል ጋር (1ሳሙ 3:10) እንዳደረገው ጠርቶታል። ይህም ግልጠት ወደ ግራ መጋባት ውስጥ ከቶታል፤ እንዲያበቃለት ግን አላደረገም። ይልቁንም ራሱን በሌላ ስም ሲጠራ እንዲያገኝ አደረገው እንጂ።
በግል ዝምድና በሆነ መተዋወቅ በሆነ መልኩ ከክርስቶስ ጋር ስንገናኝ ብቻ ህይወት ይቀየራል። ኢየሱስም ጳውሎስን በደንብ እንደሚያውቀው በውስጥም በውጪም አሳይቶታል። ምንም እንኳን ጳውሎስ አሳዳጅ ቢሆንም ልቡም ለክርስቲያኖች ባለው ጥላቻ የተሞላ ቢሆንም ኢየሱስ ይሄ ካለማወቅ የመጣ መሆኑን ተረድቷል። ምህረቱን ሊያደርግለት እና በእርሱም ላይ ሊያሳድር ፈልጓል። ይህ እንዲሁ ሊገኝ የማይችል እና ከሌላ ምንም ሳይጠብቅ የሚሰጥ የፍቅር ትሩፋት ለሳውል ሕይወት መሰረታዊ የለውጥ ብርሃን ሆኗል።


#ጌ_ ሆይ_አንተ_ማን_ነህ?

ከዚህ ምስጢራዊ ግንኙነት እና የስሙ መጠራት ተከትሎ ጳውሎስ “ጌታ ሆን አንተ ማን ነህ?” (ሐዋ 16:15) ሲል ጠየቀ። ይህ ጥያቄ ወሳኝ የሆነና ሁላችንም ራሳችንን ልንጠይቀው የሚገባን ጥያቄ ነው። ሌሎች ሰዎች ስለ ኢየሱስ ሲያወሩ መስማት ለብቻው በቂ አይደለም፤ እርሱን ጠለቅ ባለ መልኩ እራሳችን ልናወራው ይገባል። ይህ ነው እንግዲህ ጸሎት ማለት። ጸሎት በቀጥታ ከኢየሱስ ጋር ማውራት ነው። ምንም እንኳ ልቦቻችን ግራ የተጋቡ ቢሆንም አዕምሮአችን በጥርጣሬዎች የተሞላ ቢሆንም ክርስቶስን እና ቤተክርስቲያኑንም የምንንቅ ብንሆንም እንኳ ሁሉም ወጣት በልቡ ይሄንን ጥያቄ ለራሱ መጠየቅ ይችል ዘንድ ጸሎቴ ነው። “ጌታ ሆይ አንተ ማን ነህ?”

መቼም ሁሉም ሰው ኢየሱስን ያውቀዋል ብለን መደምደም አንችልም። በዚህ በኢንተርኔት ዘመን እንኳ ብዙ ሰዎች ኢየሱስን እና ቤተክርስቲያኑን የሚጠይቁት ተመሳሳይ ጥያቄ ነው “አንተ ማን ነህ?” (ኢየሱስን)። በአጠቃላይ በዚህ ታሪክ ላይ ጳውሎስ ብቸኛ የተናገረባት ቦታ ይህች ብቻ ናት። ጌታም ወዲያውኑ “እኔ አንተ የምታሳድደኝ ኢየሱስ ነኝ” ሲል መልሶለታል።

“እኔ አንተ የምታሳድደኝ ኢየሱስ ነኝ።”

በዚህ መልኩ ኢየሱስ ለሳውል ትልቅ ምስጢር ገልጦለታል። እርሱም ይህ ነው ራሱን ከቤተክርስቲያን እና ከክርስቲያኖች ጋር አንድ አድርጎ እንደሚያሳድድ ነው። እስከዛ ድረስም ጳውሎስ የሚያሳድዳቸውን ክርስቲያኖች እንጂ (ሐዋ 26:10) ኢየሱስን አላየም ነበር። ክርስቲያኖች ለክፉ እንዴት መልስ ይመልሱ እንደነበር፣ ፍትህ በተጓደለበት ጊዜ እንኳ በሰከነ መልኩ ለጥላቻ ፍቅርን ይመልሱ እንደነበር አይቷል። ባያውቀውም በዚህ አይነት መልኩ ሳውል ክርስቶስን አግኝቶት ነበር፤ ያየውም በክርስቲያኖች ውስጥ ነበር።



ከጌታ ጋር መጋጨት (መማታት) ይጎዳል።
ጳውሎስ ከወደቀ በሗላ በእነዚህ ቃላት ጌታ ለተወሰነ ጊዜ በምስጢር እንዲህ ብሎታል . . . . . . .

#ይቀጥላል።።።።


ለተለያዩ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዎችን ለማግኘት ታች ያላውን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑን፡፡
#ሼር።




https://t.me/YariedDessale/5079

https://t.me/YariedDessale/5091


The Universal Catholic Church Teaching Channel.
1.1K viewsedited  06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-27 13:17:24
ዘማሪ #ክቡር_አባ_ዳዊት_ውብሸት



ለ25ኛ አመት የክህነት በዓል






በዝማሬ፣ በስብከተ ወንጌል፣ በጣዕመ ቅዳሴያቸው የምንናፍቃቸው ተወዳጅ አባታችን #ክቡር አባ ዳዊት ውብሸት
እንኳን ለ25ኛ አመት የክህነት በዓል በሰላም አደረስዎት።
ጌታ አምላክ የአገልግሎት ዘመንዎት የተባረከ ይሁንልን። አሜን።

#Happy_25th_Anniversary

20-11-2014 ዓ.ም


ቤተሰብ ይሁን

https://t.me/YariedDessale/5090
1.1K viewsedited  10:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 14:29:20

605 views11:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ