Get Mystery Box with random crypto!

ጌታዬ ሁለመናዬ!

የቴሌግራም ቻናል አርማ yarieddessale — ጌታዬ ሁለመናዬ!
የቴሌግራም ቻናል አርማ yarieddessale — ጌታዬ ሁለመናዬ!
የሰርጥ አድራሻ: @yarieddessale
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.11K
የሰርጥ መግለጫ

ስለ አንዲት፡ ቅድስት፡ ሐዋርያዊትና ኩላዊት ቤተ-ክርስቲያን ምንነትና ምን እንደምታስተምር ለማወቅ፣ ስለ ቤተክርስቲያን ታሪክ፤ ስለመላዕክት፣ ስለቅዱሳን-ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃ፣ ተዓምራት፤ የር.ሊ.ጳ ፍራንችስኮስን ወቅታዊ ትምህርቶች፤ መንፈሳዊ ፊልሞችን ሁሉ በቀላሉ ያገኙበታል፡፡ #ክርስትናን_ክርስቶስን_እንወቅ፡፡
“አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፡፡” (ማቴ. 6:33)

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-07-24 21:43:16
በአዲስ አበባ ካቶሊካዊ ሰበካ ወጣት ፍቅሩ አቦ በልደታ ማርያም ካቶሊክ ካቴድራል ማዕረገ ድቁናን ተቀበለ።

እሁድ ሐምሌ 17-2014 ዓ.ም በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን በአዲስ አበባ ካቶሊካዊ ሰበካ በልደታ ማርያም ካቶሊክ ካቴድራል ፍቅሩ አቦ ወይም በክርስትና ስሙ ንፍቀ ዲያቆን ፍቅረ ማርያም አቦ ከብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሊቀ ጳጳስ ዘካቶሊካዊያን እጅ ማዕረገ ድቁናን ተቀብሏል፡፡

ዲያቆን ፍቅረ ማርያም ለ9 አመታት በሲታዊያን ማህበር እስከ 1ኛ ነገረ መልኮት ትምህርቱ የቆየ ሲሆን በ2012 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ካቶሊካዊ ሰበካ በመቀላቀል አዲስ አበባ አስኮ አካባቢ በሚገኘው በቅዱስ ፋራንችስኮስ የፍልስፍና እና የነገረ መለኮት ትምህርት ቤት ለ3 አመት በፍልስፍና እንዲሁም ለ4 አመት በነገረ መለኮት ትምህርቱን አጠናቋል፡፡

ንፍቀ ዲያቆን በእለቱ ለዚህ አገልግሎት በመንፈሳዊ ትምህርት እና በተለያዩ ምክሮች ላገዙት ክቡራን ካህናት ፣ ቤተሰቦቹ እና ጓደኞቹ ላቅ ያለ ምስጋናውን አቅርቧል፡፡

በዱቁና መርሃ ግብሩም ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ ሊቀ ጳጳስ ዘካቶሊካዊያን ፣ ክቡር አባ ተስፋዬ ወ/ማርያም የአዲስ አበባ ካቶሊካዊ ሰበካ እንደራሴ ፣ ክቡር አባ ጴጥሮስ በርጋ የአዲስ አበባ ካቶሊካዊ ሰበካ የሐዋርያዊ ስራዎች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ፣ ክቡራን ካህናት ፣ ደናግላን፣ ወጣት መዘምራን ፣ ቤተሰቦቹ እና ምዕመናን ተገኝተዋል፡፡

#ምንጭ፦

ካቶሊክ ቲቪ ኢትዮጵያ Catholic Tv


https://t.me/YariedDessale/5088?single
745 views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 20:42:29
764 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 20:42:19 ፎቶ
693 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 20:41:56 “ #ሲኖዶሳከመላው የሚጀምረው ከመላው የእግዚአብሔር ሕዝብ ከመስማት ነው። የምታስተምር ቤተክርስቲያን በመጀመሪያ የምትሰማ ቤተክርስቲያን መሆን አለባት፤ ሁለተኛው የቫቲካን ጉባኤ እንደሚያስታውሰን ሁሉም ምእመናን በአጠቃላይ በመንፈስ ቅዱስ የተቀቡ ናቸው ስለሆነም ሁሉንም የቤተክርስቲያን አባላት ማማከር አስፈላጊ ነው ።” ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ

በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የ53ኛ መደበኛ የጳጳሳት ጉባኤ የሰበካዎች የሲኖዶስ ውይይት ውጤት የሆነውን የተጠናቀረ ጽሁፍ የሲኖዶስ ሀገርአቀፍ ኮሚቴ ሰብሳቢ በሆኑት በክቡር አባ ገብረመስቀል ሽኩር ቀረበ።

ሀምሌ 14 ቀን 2014 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽ/ቤት ብጹዓን ጳጳሳት፤ የሀገረስብከት ተወካዮች፤ የተለያዩ ማህበራት እና እንቅስቃሴ ተወካዮች እንዲሁም የጠቅላይ ጽ/ቤቱ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ክቡር አባ ገብርኤል ወ/ሃና የሲኖዶስ ኮሚቴውን በመወከል ቤተክርስቲያን በሲኖዶስ እንቅስቃሴ ላይ ያደረገችውን ተሳትፎ አብራርተዋል። እንቅስቃሴው ከጥቅምት ወር ጀምሮ ላለፉት 8 ወራት የቆየ ሲሆን የጳጳሳት ጉባኤ የሲኖዶስ እንቅስቃሴ በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲዳረስ በጠቅላይ ጽ/ቤቱ የሲኖዶስ ቢሮ እና የቢሮውን አስተባባሪ በመሾም የተጀመረ ሲሆን በመቀጠልም በሃገር አቀፍ ደረጃ 8 አባላትን የያዘ የሲኖዶስ ኮሚቴ ተቋቁሞ በመስራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል። ክቡር አባ ገብርኤል ኮሚቴው ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ የተደረጉ የምክክር መድረኮች፣ የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅቶችን እንዲሁም ውይይቶች፣ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በከፍተኛ የሃይማኖት ምሁራን ለብጹዓን ጳጳሳት፣ ካህናት፣ የሃገረስብከት ተወካዮች እና ለሲኖዶስ ተወካይ ምዕመናን መደረጋቸውን ገልጸዋል።

የሲኖዶስ ሀገርአቀፍ ኮሚቴ ሰብሳቢ በሆኑት በክቡር አባ ገብረመስቀል ሽኩር የቀረበው ከየሀገረስብከቶች የተሰበሰቡ ባለ 10 ገጽ ሪፖርቶችን መሰረት በማድረግ በሀገር አቀፍ የሲኖዶስ ኮሚቴ ተጠናቅሮ የቀረበውን ጽሁፍ አቅርበዋል። የቀረበው ጽሁፍ የመጀመሪያ ረቂቅ ሲሆን ሲኖዶስ በኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ምንነት፤ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ተግዳሮቶች እና የወደፊት አቅጣጫዎችን የያዘ ነው። ጽሁፉ በ 16 የተለያዩ ክፍሎች የተዋቀረ ሲሆን በያንዳንዱ ሁኔታ ያሉትን ተግዳሮቶች፤ ጥያቄዎች እናም ተያይዘው የሚመጡ እድሎችን ወደተግባር የሚውሉበት ሀሳቦች ተዳሰዋል። የአምልኮ ስርዓት፣ ጥሪ፣ ገዳማውያን፣ ወጣቶች፣ ካታኪስቶች፣ መደማመጥ እና መነጋገር፣ የቤተክርስቲያን አስተምህሮ በጽሁፉ ከተነሰሱት ሃሳቦች መካከል ይጠቀሳሉ።
ክቡር አባ ገብረመስቀል “ውይይት ከርዕሰ ሊቃነ ጳጳሱ ጋር በርዕሰ ሊቃነ ጳጳሱ ስር” የሚለውን የርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንቸስኮስ ሃሳብ ውይይት “በሀገርስብከት ከጳጳሱ ጋር በጳጳሱ ስር ፤ በቁምስና ከቆሞሱ ጋር በቆሞሱ ስር እንዲሁም በቤተሰብ ከአባወራ ጋር በአባወራ ሥር አውርደን መስራት አለብን” ብለዋል።

ቤተክርስቲያን ይህንን ጽሁፍም ለወደፊት አቅጣጫ መሰረት በማድረግ የምትጠቀመው በመሆኑ የተጠናቀረው ጽሁፍ ወደሮም ከመላክ በተጨማሪ በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ያሉትን ተግዳሮቶች ለመፍታት እና ወንጌልን ለማስፋፋት ጥቅም ላይ እንደሚውል ተገልጿል። የቀረበው ጽሁፍ ላይ መጨመር ያለባቸው፤ መስተካከል ያለባቸው ሃሳቦች ከተሳታፊዎች ተስጥቷል።
የሀገር አቀፍ የሲኖዶስ አባል የሆኑት ሲስተር ሉጂና ገብረወልድ “ሲኖዶስ ካቶሊካዊ ማንነታችን ያንጻል፤ ይህ ሲኖዶስ ለአንዲት ቤተክርስቲያን እድገት መታነጽ ትልቅ እድል ነው” በማለት በሃሳብ የገለጽነው ሁሉ ወደተግባር ማዋል የሁሉም ካቶሊክ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸዋል።

ሲኖዶሱ የብዙዎችን ድምጽ የተሰማበት እና የእግዚአብሔርን ድምጽ በመስማት ወደፊት ለስብከተ ወንጌል ምን የተሻለ መስራት እንድምንችል አቅጣጫ የሚያሳይ ውይይት መሆኑ ተገልጿል። የተነሱት ሃሳቦች ወደጋራ ተልዕኳችን መንገድ የሚመሩን ሊሆን የሚገባ መሆን እንዳለበት እና የሚታቀዱት ሥራዎች ሁሉ በህብረት፤ በተሳትፎ እና በጋራ ተልዐኮ መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰጥተዋል።


ምንጭ፦ CBCE


https://t.me/YariedDessale/5082
692 viewsedited  17:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-22 20:39:45
በ53ኛው መደበኛ የጳጳሳት ጉባኤ ላይ ከተለያዩ ቁምስናዎች የተውጣጡ ወጣቶች የሲኖዶስን ሀሳብ የያዘ አዲስ ዝማሬ ለብጹዓን ጳጳሳት እና በዕለቱ ለተገኙ ተሳታፊዎች አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ጽ/ቤት በሲኖዶስ ሀገርአቀፍ ኮሚቴ አስተባበባሪነት የሰበካዎች የሲኖዶስ ውጤት በቀረበበት ቀን ከተለያዩ ቁምስናዎች የተውጣጡ ወጣቶች የሲኖዶስን ሃሳብ ማዕከል ያደረገ ዝማሬ አዘጋጅተው አቅርበዋል።

የመዝሙሩ ይዘት የሲኖዶስ ሀሳብ የሆነውን በህብረት፣ በተሳትፎ ለጋራ ተልዕኮ የያዘ ሲሆን በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ለአገልግሎት መጠራትን አንፀባርቋል።

ወጣቶቹ በሲኖዶስ ሀገር አቀፍ ኮሚቴ እና በወጣት ቢሮ አስተባባሪነት በበጎፍቃደኝነት የተሰባሰቡ ሲሆኑ ላዘጋጁት ዝማሬ ለመልካም ፍቃዳቸው ልዩ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።


CBCE




https://t.me/YariedDessale/5081
560 viewsedited  17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 10:01:50 “ነገር ግን ተነሣና በእግርህ ቁም፤ ስለዚህ እኔን ባየህበት ነገር አንተም በምታይበት ነገር አገልጋይና ምስክር ትሆን ዘንድ ልሾምህ ታይቼሃለሁና።” የሐዋርያት ሥራ 26፡16
621 views07:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 10:00:48 የርዕሰ ሊቃነጳጳሳት ፍራንችስኮስ ለ35ኛው የአለም የወጣቶች ቀን ያስተላለፉት ሐዋርያዊ መልዕክት



“ነገር ግን ተነሣና በእግርህ ቁም፤ ስለዚህ እኔን ባየህበት ነገር አንተም በምታይበት ነገር አገልጋይና ምስክር ትሆን ዘንድ ልሾምህ ታይቼሃለሁና።” የሐዋርያት ሥራ 26፡16





ውድ ወጣቶች ሆይ,

እጆቻችሁን በመያዝ በ2023 በሊዝበን ወደሚከበረው የዓለም የወጣቶች ቀን በመንፈሳዊ ንግደት ልጓዝ እወዳለሁ።

ባለፈው ዓመት ከወረርሽኙ አስቀድሞ ባስቀመጥሁት መሪ ቃል “አንተ ወጣት ተነስ እልሃለሁ በሚለው (ሉቃስ 7:14) በመለኮታዊ ቸርነቱ ጌታ ልንጋፈጣቸው በነበረው ከባድ ተግዳሮቶች እያዘጋጀን ነበር።

በሁሉም የዓለም ክፍል ባጋጠመንና ባጣናቸው ለኛ ውድ በሆኑ ሰዎች መለየት እና ባጋጠመን ከማኅበረሰቡ መገለል ተሰቃይተናል። ድንገተኛ የጤና ችግሩም ለብቻው የወጣቱን አካሄድ የሚያዘግም እና ህይወታችሁንም ከተፈጥሮአዊው መልኩ ወጣ ያደረገ ነበር። በትምህርት ቤቶቻችሁ እና በዩኒቨርስቲዎቻችሁ በስራም ይሁን በማኅበረሰባዊ ስብሰባዎቻችሁ ራሳችሁን በከባድ እና ልትጋፈጡት በማትችሉበት ሁኔታ ውስጥ አግኝታችሁት ይሆናል። በጣም የከበዳቸው እርዳታ ያጡ እና ሌሎች በተሳሳተ መልኩ እንደተረዷቸው፣ የተሰማቸው እንዲሁም በቤተሰብ ውስጥ ችግሮች ሲነሱ ስራ ማጣትና ድብርት ብቸኝነት እና የሱሰኝነት ጠባዮች እየጨመረ ለመጣው ጭንቀት እና የቁጣ መገንፈል እንዲሁም ጥቃት ምክንያት ሲሆኑ አይተናል።

ሆኖም እግዚአብሔር ይመስገን ይሄ የሳንቲሙ አንደኛው ገፅታ ብቻ ነበር። ይህ ክስተት የኛን በቀላሉ ተሰባሪነትም አሳይቶናል በተቃራኒውም የኛን መልካም ኃይላት ገልጧል፤ የአብሮነት መንፈሳችንንም ጨምሯል። ለአንድነት ያለንን ዝንባሌም ጨምሯል በሁሉም የዓለም አቅጣጫዎች ብዙ ቁጥር ያላቸው ግለሰቦች ብዙ ወጣቶችን ጨምሮ ህይወትን ለማዳን የተስፋን ዘር ሲዘሩ ነበር፤ ነጻነትንና ፍትህንም ሲደግፉ ነበር። ሰላም እና ዕርቅ ፈጣሪዎች አገናኝ ድልድዮች በመሆን ሲሰሩም ነበር።

ሁሌም ቢሆን ወጣት በሚወድቅበት ጊዜ በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ የሰው ዘር በሙሉ ይወድቃል። ነገር ግን አንድ ወጣት በሚነሳበት ጊዜ እውነታው ዓለም ሁሉ አብሮት እንደሚነሳ ነው። ወጣቶች ሆይ እንዴት ያለ አቅም ነው በእጃችሁ ላይ ያለው እንዴትስ ያለ ጥንካሬ ነው በልባችሁ ያላችሁ?!

ዛሬም ቢሆን እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችሁ “ተነሱ!” ይላችሗል። በአፅንዖት ተስፋ የማደርገው ለአዲሱ እና ለሚመጣው የሰው ልጆች የታሪክ ገፅ ይህ እንዲረዳን ነው። ነገር ግን ያለ እናንተ ምንም ነገር መጀመር አንችልም። ውድ ወጣቶች ሆይ ዓለማችን የምትነሳ ከሆነ የእናንተን ጥንካሬ ትጠይቃለች፣ የእናንተን ጥልቅ መሻት እና የጠበቀን ጉጉት ትፈልጋለች። ስለዚህም ከእናንተ ጋር በሐዋርያት ሥራ ኢየሱስ ለሐዋርያው ጳውሎስ “ተነስ እና ያየኸውን እንድትመሰክር ሾሜሃለሁ!” የሚለውን መልዕክት ላሰላስል እወዳለሁ።

ጳውሎስ በንጉሱ ፊት መሰከረ . . . . .


#ይቀጥላል።።።።


ለተለያዩ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዎችን ለማግኘት ታች ያላውን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑን፡፡ ሼር።




https://t.me/YariedDessale





The Universal Catholic Church Teaching Channel.
638 views07:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-21 06:53:43 " የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከእናንተ ጋር ይሁን።"
(1ኛ ቆሮ 16:23)

https://t.me/YariedDessale/5078
565 viewsedited  03:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 12:23:13

የመቁጠርያ “ጠጠሮችን” (rosary beads) የያዘ ሽቦ፡-




የመቁጠርያ ጸሎታችንን መስቀሉ ያለበት ቦታን በመያዝ የሐዋርያት ጸሎተ ሃይማኖት በመድገም እንጀምራለን፣ ከዚያም በኋላ ሦስቱን ትንንሽ ድቡልቡል (ጠጠሮችን) አንድ በአንድ በመያዝ እግዚአብሔር እምነት፤ ተስፋና፤ ፍቅር እንዲሰጠን እንጠይቃለን፣ ከዚህ በኋላ ከእያንዳንዱ አሥር “ጸጋ የሞላሽ” በፊት “በሰማይ የምትኖር አባታችን ሆይ!” የሚለዉን ጸሎት እናደርሳለን፣ አሥሩን “ጸጋ የሞላሽ” በምናደርስበት ጊዜ አሥሩን ድቡልቡሎች እንቆጥራለን፣ ከእያንዳንዱ አሥር “ጸጋ የሞላሽ” በኋላ “ለአብና ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይሁን” የሚለዉን ጸሎት እናደርሳለን፡፡

I) የደስታ ምስጢራት፡
በክርስቶስ ሕይወት ዉስጥ የመጀመሪያዉ ደረጃ፡የመጀመሪያዎቹ 12 ዓመታት

1. የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ ኃይል መጸነስ (ሉቃ. 1፡26-38)

2. የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅድስት ኤልሳቤጥን መጎብኘት (ሉቃ. 1፡39-56)

3. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም በከብቶች በረት ዉስጥ መወለድ (ሉቃ. 2፡1-7)

4. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ቤተመቅደስ መቅረብ (ሉቃ. 2፡22-32)

5. የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተመቅደስ ውስጥ መገኘት (ሉቃ. 2፡41-52)


II) #የብርሃን_ምሥጢራት፡

በክርስቶስ ሕይወት ዉስጥ ሁለተኛዉ ደረጃ፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ይፋዊ ሕይወት፡
የብርሃን ምሥጢራት ክርስቶስ በመጨረሻዎቹ ሦስት ዓመታት ዉስጥ የሠራቸዉን ሥራዎች እያስታወስን እንድንጸልይ ይረዳናል፣ በዚህ ወቅት የምናደርሳቸዉ አሥሩ “ጸጋ የሞለሽ” ጸሎቶች ትንሽ ጊዜ ቆም ብለን በክርስቶስ ሕይወት የተከሰቱ ክስተቶችን እያሰብን እንድንቆይና ከማርያም ጋር ሆነን ወደ ክርስቶስ አተኩረን እንድንመለከት፤ እንዲሁም እንደ ማርያም እሱን ከልብ ማዳመጥ እንድንችል ይረዱናል፣

1. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ወንዝ ተጠመቀ (ሉቃ. 3፡13-17)

2. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ ዉሃን ወደ ወይን ጠጅ ቀየረ (ዮሐ. 2፡1-11)

3. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እግዚአብሔር መንግስት ሰበከ (ማር. 1፡15)

4. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ክብሩን በደብረ ታቦር ላይ ገለጸ (ማቴ. 17፡1-13)

5. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱስ ቁርባንን ሰጠን (ሉቃ. 22፡14-20)


III) #የህማም_ምሥጢራት

በክርስቶስ ሕይወት ሦስተኛዉ ደረጃ፡ የክርስቶስ ህማማት

የህማማት ምሥጢራት ጋር መቁጠርያን በምንደግምበት ወቅት እመቤታችን ማርያም ወደ ጎልጎታ ከክርስቶስ ጋር ባደረገችዉ ጉዞ እናጅባታለን፥ ከርሷ ጋር በመሆን የመስቀል ጉዞ እስከ ልጇ መስቀል ሥር ድረስ አብረን እንጓዛለን፣

1. የኢየሱስ ሥቃይ በጌተሰማኒ አትክልት ቦታ (22፡39-46)

2. የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግንድ ላይ ታስሮ መገረፍ (ዮሐ. 19፡1-5)

3. በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራስ ላይ የእሾህ አክሊል ተደፋበት (ማር. 15፡16-20)

4. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀሉን ተሸከመ (ዮሐ. 19፡16-19)
5. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሞተ (ማቴ. 27፡45-50)


IV) #የክብ_ ምስጢራት፡

በክርስቶስ ሕይወት አራተኛዉ ደረጃ፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት መነሳት ነዉ፡፡

ከክብር ምስጢራት ጋር የምንደግመዉ የመቁጠርያ ጸሎት ከክርስቶስ ጋር የምናደርገዉን ጉዞ ወደ ክብር ፍጻሜ የሚያደርስ ነዉ፣ ክርስቶስ ከሞት እንደተነሳ ሁሉ እኛም በመጨረሻዉ ቀን እንነሳለን፤ የሕይወት አክሊልንም እንደፋለን፣ ይህ ደግሞ ለእመቤታችን ማርያም የተደረገላት እዉነታ ነዉ፣ ስለዚህ እኛም ልክ እንደርሷ ክርስቶስን ከልብ መከተል ከቻልን እኛንም የሚጠብቀን ይህ ክብር ነው።

1. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት መነሳት (ማቴ. 28፡1-10)

2. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ዐረገ (ሉቃ. 24፡50-53)

3. ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ50ኛዉ ቀን መንፈስ ቅዱስን ላከ (ሐሥ. 2፡1-4)

4. እመቤታችን ማርያም በክብር ወደ ሰማይ ወጣች (ራዕ. 12፡1-4)

5. እመቤታችን በሰማይ የክብር አክሊል ተቀዳጀች (ራዕ. 21፡5-7



ለተለያዩ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዎችን ለማግኘት ታች ያላውን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑን፡፡ ሼር።




https://t.me/YariedDessale/5076





The Universal Catholic Church Teaching Channel.
802 viewsedited  09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-19 14:49:58

የመቁጠርያ ጸሎት እንዴት የካቶሊኮች ጸሎት ሊሆን እንደቻለ የሚያሳይ አጭር ታሪክ!




ከጥንት ጀምሮ ገዳማዊያን፤ ካህናት፤ ሲስተሮች (እህቶች)፤ ወንድሞች ሁሉ 150ዉን ዳዊት ለዕለታዊ ጸሎት ይጠቀሙ ነበር፣ ሆኖም ግን ይህ በቤታቸዉ ሆነዉ ለመጸለይ ለሚፈልጉ ምዕመናን አስቸጋሪ ነበር፣ ምክንያቱም በድሮ ጊዜ መዝሙረ ዳዊት ማግኘት በጣም ከባድ ስለነበር ነዉ፤ እንደዛሬ መጽሐፍትን በህትመት የማባዛት ቴክኖሎጂ ያልታወቀበት ዘመን ስለነበር እያንዳንዱ መጽሐፍ በእጅ ነበር የሚጻፈዉ፣ ከዚህም በተጨማሪ ብዙ ሕዝብ ማንበብና መጻፍ አይችልም ነበር፣ በዚህ ሁኔታ የነበረዉ የእግዚአብሔር ሕዝብ የመቁጠርያ ጸሎትን ፈጠረ፣ 150 ጊዜ “ጸጋ የሞላሽ ማርያም” እየተባለ የክርስቶስን የልጅነት ሕይወቱን፤ ሥቃዩንና ሞቱን፤ እንዲሁም ከሞት መነሳቱን እያሰላሰሉ መጸለይ ተጀመረ፣ በቅርቡ ደግሞ ር.ሊ.ጳ ዮሐንስ ጳዉሎስ ዳግማዊ የኢየሱስን ይፋዊ ሕይወቱንና ሥራዉን የሚያስታወሱ አምስት ምሥጢራትን በመጨመር የብርሃን ምሥጠራት ተብሎ እንዲጠሩ ደንግገዋል።
እመቤታችን ቅድስት ማርያም በፈረንሳይ አገር ሉርድ በተባለ ሥፍራ እና በፖርቹጋል ሀገር ፋጢማ በተባለ ሥፍራ ለሦስት ህጻናት በተገለጠች ጊዜም የመቁጠርያ ጸሎትን አዘዉትረዉ እንዲጸልዩ ታበረታታቸዉ ነበር!!
የመቁጠርያ ጸሎት በምናደርስበት ጊዜ ለመቁጠር እንዲያመቸን ከእንጨት ወይም ከብረት የተሠሩ ድቡልቡል ክብ ነገሮችን ለመቁጠር እንጠቀማለን፣ ይህም የመቁጠርያ ጸሎት ጉዞአችንን ከማርያም ጋር በፍቅር እንድንጓዝ ይረዳናል፣

#በክርስቶስ_ሕይወት ዙሪያ በምናደርገዉ የመቁጠርያ ጸሎት ጉዞ አራት ደረጃዎች አሉት፤

1) #የመጀመሪያዉ_ደረጃ፡
የክርስቶስን የመጀመሪያዎቹ የ12 ዓመታት ህይወቱን የሚመለከቱ ሲሆኑ እነሱም የደስታ ምሥጢራት ተብለው ይጠራሉ።

2) #ሁለተኛዉ_ደረጃ፡
የክርሰቶስን ይፋዊ ሕይወቱንና ሥራዎቹን የሚመለከቱ ሲሆኑ እነሱም የብርሃን ምሥጢራት ይባላሉ።

3) #ሦስተኛዉ_ደረጃ፡
የኢየሱስን ሥቃይና ሞቱን የሚያስታዉሱ ክፍሎች ናቸዉ፤ እነዚህ ክፍሎች የህማም ምሥጢራት ይባላሉ።

4) #አራተኛዉ_ደረጃ፡ የክርስቶስን ከሙታን መነሳት የሚያወሱ ናቸዉ፣ እነዚህ ደግሞ የክብር ምሥጢራት ተብለዉ ይጠራሉ፡፡

ከእያንዳንዱ አሥር “ጸጋ የሞላሽ” በኋላ የሚደገመዉ የፋጢማ ጸሎት፡
ከእያንደንዱ አሥር “ጸጋ የሞላሽ” በኋላ የሚከተለውን የፋጢማ ጸሎት ተብሎ የሚጠራውን ጸሎት እንደግማለን፤ “ጌታ ሆይ በደላችንን (ኃጢአታችንን) ይቅር በለን፣ ከገሃነም እሳት ሰውረን፤ ለነፍሳት ሁሉና ያንተ ምህረት ለሚያስፈልጋቸዉ ሁሉ መንግስተ ሰማይን ክፈትላቸዉ፤ አሜን።”

#የመቁጠርያ_ጸሎትን_እንዴት_መጸለይ_እንዳለብን_የሚያሳይ_ምሳሌ፡-

እዚህ ላይ የመጀመሪያዎቹን አስሮች ወይም የመጀመሪያ የደስታ ምሥጢር እንዴት እንደሚጸለይ እንይ፤

“ክርስቶስ በመንፈስ ቅዱስ አማካይነት ተጸነሰ”፡ በዚህ ምስጢር፡

- ሊቀ መልአኩ ገብርኤል ወደ እመቤታችን ማርያም ቤት ሲገባ በሀሳባችን እናስታዉሳለን፤
- ከዚያም አሥሩን “ጸጋ የሞላሽ” እናደርሳለን፤ ይህ አሥሩ “ጸጋ የሞላሽ” ለርሷ በጣም ቅርብ እንድንሆን ይረዳናል፤ በተጨማሪም በጸጥታ እየጸለይን በመልአኩ ብሥራት ጊዜ የማርያምን ቤት የሞላዉን ራስን በሙላት ለእግዚአብሔር የመክፈትን ድባብ በመንፈስ እንቃኛለን፡፡

#ይቀጥላል።።።።


ለተለያዩ የካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዎችን ለማግኘት ታች ያላውን ሊንክ በመጫን ቤተሰብ ይሁኑን፡፡ ሼር።




https://t.me/YariedDessale/5076





The Universal Catholic Church Teaching Channel.
934 viewsedited  11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ