Get Mystery Box with random crypto!

Addis Ababa Education Bureau

የሰርጥ አድራሻ: @wwwaddisababaeducationbureau
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 106.72K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ትምህርት ቤት ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የትምህርት መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 73

2022-10-07 14:42:32
ቀን 27/1/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተና በሚሰጥባቸው የፈተና ጣቢያዎች የመስክ ምልከታ ተካሄደ።

የመስክ ምልከታው በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም ላም በረት አከባቢ በሚገኘው የኢፌድሪ ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲቲዩትና በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ ሲሆን የትምህርት ሚኒስተር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱን ጨምሮ የቢሮው አማካሪ አቶ ጥላሁን ፍቃዱ እና የተቋማቱ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

የመስክ ምልከታው በዋናነት በተቋማቱ የተከናወኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ማወቅን መሰረት አድርጎ የተካሄደ ሲሆን የመፈተኛ ክፍሎች፣የመመገቢያ አዳራሾች እንዲሁም የመኝታ ክፍሎች ዝግጅት ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ምልከታ ተካሂዶባቸዋል።

የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች በነገው እለት በተዘጋጀላቸው ተሽከርካሪ ወደፈተና ጣቢያዎች ገብተው በዩኒቨርሲቲዎቹ ኦረንቴሽን ተሰቷቸው የፊታችን ሰኞ ፈተናውን መፈተን እንደሚጀምሩ ቀደም ብሎ መገለጹ ይታወቃል።


ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:



Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
8.9K viewsAbebe Chernet, 11:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 09:51:58 ዶክተር ዘላለም አክለውም ቀደም ሲል ፈተናው ከሚሰጥባቸው የከፍተኛ ትምህርት ተቃማት አመራሮች ጋር መሰል ውይይቶች መካሄዳቸውን ገልጸው ቢሮው ከነገ ጀምሮ ተፈታኝ ተማሪዎችን ወደ ፈተና ጣቢያ የሚያጋጉዙ ተሸከርካሪዎችን ማዘጋጀቱን በመግለጽ የጸጥታ አካላት ፈተናው ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲካሄድ የተለመደ ተግባራቸውን በአግባቡ ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:



Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
3.0K viewsAbebe Chernet, 06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 09:51:41
ቀን 27/1/2015 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ቅድመ ዝግጅት ላይ ፈተናዉን ለማስተግበር ከተቋቋመዉ ኮማንድ ፖስት አባላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

ውይይቱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ የመሩት ሲሆን በውይይቱ የቢሮው ማኔጅመንት አባላት ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እና የትራፊክ ጽህፈት ቤት አመራረችን ጨምሮ የክፍለ ከተማ የትምህርት ጽፈት ቤት ሀላፊዎችና የአዲስ አበባ ከተማ መምህራን ማህበር አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

ዘንድሮ ፈተናው በሀገር አቀፍ ደረጃ ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንደሚሰጥ ቀደም ብሎ በትምህርት ሚኒስቴር የተገለጸ ሲሆን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርም ፈተናውን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፤ ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤ ኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና ፌደራል ቴክኒክና ስልጠና ኢንስቲትዩት ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸው ተገልጻል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ዘንድሮ ፈተናው ለመጀመሪያ ጊዜ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚሰጥ እንደመሆኑና የፈተናው ሂደትም በበላይነት በትምህርት ሚኒስቴር የሚመራ ቢሆንም ከተማ አስተዳደሩ ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ ያለምንም እንከን እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በመስራት ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡
3.1K viewsAbebe Chernet, 06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 16:19:04
ቀን 25 /1/2015 ዓ.ም

ከመዉሊድ በዓል ጋር ተያይዞ የ12ኛ ክፍል የእስልምና እምነት ተከታይ ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ቦታቸው የመግቢያ ቀን ላይ ማስተካከያ ተደረገ፡፡

መስከረም 28 የሚከበረውን የመዉሊድ በዓል አስመልክቶ የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች በቀጣዩ ቀን ተገኝተው ስለፈተና የሚሰጣቸውን አጠቃላይ መግለጫ መከታተል እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ሚኒስቴሩ እንደገለጸው መስከረም 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሚጀምረው የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ አገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች መስከረም 26-28 ተጠቃለው በመግባት መስከረም 29 ስለፈተናውና ተያያዥ ጉዳዮች በየተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች ገለጻ የሚደረግበት ዕለት ነበር፡፡

ይሁንእንጂ የእስልምና እምነት ተከታዮች መስከረም 28 የመዉሊድ በዓል አክብረዉ መስከረም 29/2015 ዓም እሁድ ጠዋት መግባት እንዲችሉ በልዩ ሁኔታ የተፈቀደላቸዉ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ይህን ተከትሎም የፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ገለጻ /Orientation/ ይህንን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እሁድ ከሰዓት በኋላ እንዲሰጥ ማስተካከያ መደረጉን በመግለጽ የእምነቱ ተከታይ ተማሪዎች ይህን አውቀው በተጠቀሰዉ ሰዓት በመገኘት ገለጻውን እንዲትከታተሉ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:

9.1K viewsAbebe Chernet, 13:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 15:07:42

ቀን 25 /1/2015 ዓ.ም

በአዲስ አበባ የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና ሚሰጥባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች የቅድመ ዝግጅት ስራቸዉን በማጠናቀቅ ተማሪዎችን በመጠበቅ ላይ መሆናቸዉ ተገለጸ፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ201 ትምህርት ቤቶች ዝግጅታቸዉን ሳደርጉ የቆዩ 49 ሺህ 2 መቶ 3 ተማሪዎች በአዲስ አበባ በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ላይ በዘጠኝ ካንፓሶች የከፍተኛ ትምህርት ተቋም መግቢያ ፈተና ይወስዳሉ፡፡

በመጀመሪያዉ ዙር የሶሻል ሳይንስ እና በሁለተኛ ዙር የናቹራል ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና የሚወስዱ ሲሆን የሚፈተኑባቸዉ የመፈተኛ ክፍሎች እና ወንበሮች ፣ የማደሪያ ክፍሎቻቸዉ ፣ የመመገቢያ ቦታዎች እና ሌሎች አስፈላጊ ግብዓቶች ሁሉ ተማልተዉ ዩኒቨርስቲዎች ዝግጁ ሆነዉ እየጠበቋቸዉ መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳኛዉ ገብሩ ገልጸዋል፡፡

ሀላፊዉ አክለዉም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በ5 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፣ በኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ የኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፣ የኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ፣ የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና የፌደራል ቴክኒክና እልጠና ኢንስቲትዩት ኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፤ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እና በፌደራል ቴክኒክና እልጠና ዩኒቨርሲቲዎች ለፈተናዉ አስፈላጊ የሆኑ ቅድመ ዝግጅቶች መጠናቀቃቸዉን ተናግረዋል፡፡ በነዚህ የፈተና ጣቢያዎች ላይ ተማሪዎችን ሊፈትኑ የሚችሉ 997 ፈታኞች ፣ ሱፐርቫይዘሮች እና የጣቢያ ሀላፊዎች ተዘጋጁተዉ ተማሪዎችን እየጠበቁ መሆናቸዉን ገልጸዋል፡፡

ተማሪዎችን ከሚማሩባቸዉ ትምህርት ቤቶች ወደ ሚፈተኑባቸዉ ዩኒቨርሲቲዎች የሚያጋጉዙ 300 አውቶቢሶች መዘጋጀታቸዉንም ጨምረዉ የገለጹ ሲሆን የኒቨርሲቲዎችም ፈተናዉን ለመስጠት ሙሉ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ ማጠናቀቃቸዉንም አሳውቀዋል፡፡


ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:



Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
7.6K viewsAbebe Chernet, edited  12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-05 10:37:40

ቀን 25 /1/2015 ዓ.ም

የአዲሰ አበባ ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናና ለመስጠት የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን ማጠናቀቁን ገለጸ

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:



Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
3.9K viewsAbebe Chernet, 07:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 19:53:51 ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ!

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:



Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
5.2K viewsAbebe Chernet, 16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 19:53:38
ቀን 23 /1/2015 ዓ.ም

የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት የ2014 ዓ.ም ማጠቃለያ ትምህርት ጉባኤ አካሄደ፡፡

የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽፈት ቤት በባለፈዉ ሳምንት በ2014 ዓ.ም የስራ አፈጻጸም ሪፖርት እና በ2015 የትምህርት ዘመን እቅድ ላይ ውይይት ያደረገ ሲሆን በዛሬው እለት ጉባኤዉን የቀጠለ ሲሆን በጉባኤዉ ላይ የክፍለ ከተማዉ አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ በቀለ ጉታ ፣ የክፍለ ከተማዉ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሪት ሳምራዊት ቅባቱ እና ጥሪ የተደረገላቸዉ እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

በጉባኤዉ የመክፈቻ ንግገር ያደረጉት የአዲስ ከተማ ከፍለ ከተማ አፈጉባኤ የተከበሩ አቶ በቀለ ጉታ ሀገር የመቅረጽ ተግባር ሀገር በመገንባት ስራ ውስጥ ትልቁን ድርሻ የሚወስድ በመሆኑ በቀጣይም የትምህርት ዘመን ላይ ጠንክሮ መስራት ይገባል ብለዋል፡፡

የክፍለ ከተማዉ ትምህርት ጽ/ቤት ሀላፊ ወ/ሪት ሳምራዊት ቅባቱ በበኩላቸዉ ጥናቶችን የሸልፍ ሲሳይ ከማድረግ ይልቅ የስራዎቻችን አጋዥ አድርገን ልንጠቀምባቸው ይገባል ብለዋል፡፡

በእለቱ የክፍለ ከተማ ት/ጽ/ቤት በትምህርት ስራ ላይ ያስጠናቸዉ ሶስት ጥናቶች ቀርበዉ ውይይት የተደረገባቸዉ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ በበጀት አመቱ በክፍለ ከተማዉ የላቀ ውጤት ያስመዘገቡ ቡድኖች ፣ በተማሪዎች ውጤት የተሻለ አፈጻጸም ያስመዘገቡ የወረዳ ት/ጽ/ቤቶች እና ትምህርት ቤቶች እውቅና ተሰጥቷቸዋል፡፡ የስራ ዘመናቸዉን በጥሮታ ላጠናቀቁም ርዕሰ መምህራን የሽኘት እና እውቅና የመስጠትም ተግባር ተከናውናል፡፡ ት/ጽ/ቤቱ በስራቸዉ ስራዎች ከጎኑ በመሆን እገዛ ላደረጉ ባለድርሻ አካላትም እውቅና ሰጥቷል፡፡

ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!
5.3K viewsAbebe Chernet, 16:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 12:33:36 መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!

You Tube:



Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau

Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc

Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication

Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/

Website: - aaceb.gov.et

Email;- aacaebc@gmail.com

Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
6.0K viewsAbebe Chernet, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 12:33:22
ቀን 23 /1/2015 ዓ.ም

ትምህርት ሚኒስቴር የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና አሰጣጥ ላይ ማብራሪያ ሰጠ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ፈተናውን በተሳካ ሁኔታ ለመስጠት አስፈላጊው ዝግጅት መደረጉን የገለጹ ሲሆን ሂደቱ ተማሪዎች በራስ ጥረት ብቻ ውጤታማ የሚሆኑበት ነው ብለዋል።

ከዚህም መካከል የፈተናው ዝግጅትና ህትመት በቴክኖሎጂ ታግዞ በከፍተኛ ጥንቃቄና ከደህንነት ስጋት ነፃ በሆነ መልኩ መከናወኑን በመግለጫቸው ተናግረዋል።

እስከ አሁን በነበረው የቅድመ ዝግጅት ሂደትም ከሚመለከታቸው የፌደራል እና የክልል መንግስታት የስራ ሃላፊዎች ጋር በቅንጅት እየተሰራ እንደሆነም ሚኒስትሩ ገልፀዋል።

በመግለጫው ሀገር አቀፍ ፈተናው በሁለት ዙር የሚሰጥ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም በመጀመሪያው ዙር የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች ከመስከረም 30,2015 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 02,2015 ዓ.ም ፈተናውን ሲወስዱ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከጥቅምት 8,2015 ዓ.ም እስከ 11,2015 ዓ.ም ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሏል።

ተፈታኞችም ፈተናው ከሚሰጥበት ቀን በፊት ባሉት ሶስት ቀናት በሚፈተኑበት ዩኒቨርስቲዎች መገኘት እና ኦረንቴሽን መውሰድ እንደሚጠበቅባቸውም ተነግሯል።

ከፈተናው ቀን በፊት ባሉት ቀናት ተማሪዎችን ወደ ፈተና ቦታ የማምጣት እና ፈተናው እንዳለቀም ተማሪዎችን ወደየመጡበት አካባቢ የመመለስ ስራ እንደሚሰራም ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።


ሀገርን በዘላቂነት እናልማ!’

የፈረሰውን አብልጠን እንገንባ!

ለማንኛውም ፈተና እንዘጋጅ!

ባልታጠበ እጅ አይንዎን አፍዎን እና አፍንጫዎን ባለመንካት በዙሪያዎ ላሉ ሰዎች አርአያ ይሁኑ
6.1K viewsAbebe Chernet, 09:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ