Get Mystery Box with random crypto!

ወግ ብቻ

የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የቴሌግራም ቻናል አርማ wegoch — ወግ ብቻ
የሰርጥ አድራሻ: @wegoch
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.51K
የሰርጥ መግለጫ

✔በየቀኑ ምርጥ ምርጥ የጥበብ ስራዎችን ለማግኘት የቻነላችን ተከታይ ስለሆኑ እናመሰግናለን።
✔ @getem @serenity13
✔ @wegoch @Words19
✔ @seiloch
✔ @zefenbicha
Creator @leul_mekonnen1

Ratings & Reviews

4.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 13

2022-10-28 10:34:34 #የመኖር አካፋይ ፣ የመ ፤ ሞ ፣ ት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል አስራ አንድ)
(ሜሪ ፈለቀ)

ጭንቅላቷ ከአልጋ ልብሱ ወጥቶ ባይታይ ኖሮ የደቀቀ ሰውነቷ ከአልጋው ተጣብቆ አልጋው ላይ ሰው የተኛ አይመስልም ነበር። ፊቷ አጥንቱ ቢገጥም መልኳን የት እንደማውቀው ለማስታወስ አልተቸገርኩም። ስልኬ ውስጥ ካገኘኋቸው ፎቶዎች ውስጥ አይቻታለሁ። እናቴ ትሆናለች ብዬ ጠርጥሬም ነበር። አጠገቧ ከተቀመጥኩ ደቂቃዎች ቢያልፉም ከጥቂት የ<ደህና ነሽ?> ቃላት ልውውጥ ውጪ ከምን ጀምሬ ምን እንደምነግራት ወይም ምን እንደምጠይቃት ግራ ገብቶኝ ተጎለትኩ። እሷም እንደእኔ ግራ ገብቷት ይሆን ወይም ስትናገር እያማጠች በመከራ በመሆኑ ደክሟት አላውቅም ዝም ብላለች። በዝምታዋ መሃል እንባዋ ወደጆሮዋ ፈሰሰ። የእኔም እንባ የሚወርድበት ሰበብ እየጠበቀ ያለ ይመስል ተንደረደረ።

«ልጄ ማሪኝ!?» አለችኝ እንባዋን ዋጥ እያደረገች። ላቅፋት እፈልጋለሁ። ወይም እንድታቅፈኝ እፈልጋለሁ። ልጅ እናቱ ጉያ ሽሽግ ብሎ ፍቅር እንደሚምገው እቅፏ ውስጥ ገብቼ ይሄ ብርዳሙ ልቤን ላሞቀው እፈልጋለሁ። ባልገባኝ ምክንያት ልቤ ባዳነት ነው የሚሰማው ……….  እሩቅነት ….. ማን ብዬ ነበር ይሆን የምጠራት? እማዬ? እማ? እናቴ? እትዬ? አስካለ? አቅፋኝ ታውቅ ይሆን እንደዛ? የተፈጠረውን በአጭሩ ነገርኳት።

«ምህረት የምትጠይቂኝ ለምን እንደሆነ አላውቅም!! አንቺንም አላውቅም! ያሳለፍነው ምን እንደሆነም አላውቅም! ራሴንም አላውቅም! ምንም ይሁን ይቅር ብዬሻለሁ። የበደልሽኝ ነገር ካለ እሱን አትንገሪኝ ይቅር። አብረን ያሳለፍነውን ጥሩ ጊዜ እና ፍቅር ብቻ ንገሪኝ። ማወቅ ያለብኝን ራሴን ብቻ ንገሪኝ።» አልኳት አባ ያሉኝን አስታውሼ። <ለበቀል ነው የኖርሽው ልጄ በተሰጠሽ አዲስ ህይወት ለፍቅር ኑሪ! > ብለውኝ ነበር። የቱን እንደምትነግረኝ ጨንቋት ይሆን ዝም አለች ለብዙ ደቂቃ ከዛ መልሳ ማልቀስ ጀመረች።

« አሁን ብሞትም አይቆጨኝ! » አለች ደግሞ ደስ የተሰኘች ነገር መስላ። ግራ አጋባችኝ። ምኑ ነው ደስ ያላት? የእኔ ምንም አለማስታወስ? ወይስ ይቅር ብዬሻለሁ ማለቴ? ግራ እንደገባኝ ስታይ
«የእኔ አበባ ብታስታውሺውም ከሚያንፅሽ የሚያፈርስሽ ታሪክ ይበዛናል። ያለፈውን ለማስታወስ የምታጠፊውን ግዜ አዲስ ህይወት ለመገንባት ብትጠቀሚበት ነው የሚጠቅምሽ የሚመስለኝ። ካለፈው መንገድሽ የሚጠቅምሽን ብቻ አንስተሽ ተጓዥ» ስትለኝ ሳላውቀው ተናደድኩ

«ለምንድነው ማናችሁም የማይገባችሁ? የሚጠቅመኝንም የማይጠቅመኝንም የማስታውሰው ምንም የለምኮ ነው የምልሽ! የገዛ እናቴን አላስታወስኩሽም እኮ ነው የምልሽ! ወንድሜ የት እንዳለ አላውቅም! የት እንደማገኘውም አላውቅም! የማውቀው የነገሩኝን ነው የነገሩን ደግሞ የሰይጣን ቁራጭ እንደነበርኩ ነው። ቢያንስ ያን የሆንኩበትን ምክንያት ማወቅ የለብኝም? ራሴን እንኳን ከማን እንደምጠብቅ ጠላቶቼን እና ወዳጆቼን ለይቼ የማላውቅ ሰው ነኝ። ሌላው ይቅር ለእናቴ ምን አይነት ልጇ እንደነበርኩ ማወቅ እፈልጋለሁ። » ስጮህባት እጇን ሰዳ እንባዬን ጠረገችው።

«ለእናትሽ መተኪያ የሌለሽ ጀግና ልጇ ነበርሽ» አለችኝ ተረጋግታ! እኔ እየጮህኩ እሷ ፈገግ የምትልበት ምክንያት አልገባኝም። ልክ አባ ያለፈውን መርሳቴን ሲያውቁ እንደሆኑት ነው እየሆነች ያለችው። « ልጅም ሆነሽ እንደአባትሽ ጀብደኛ ነበርሽ» አለችኝ ያለፈውን ዘመን ልጓም ስባ በምናቧ ወደዛሬ እያመጣች ፈገግ ብላ

«እኔ ነኝ ሜላት ያልኩሽ! አባትሽ የመጀመሪያ ልጁ  እሱን የሚተካ ወንድ እንዲሆን ይመኝ ስለነበር <አምሳል> ነው የሚልሽ የነበረው። (አባቴ በህይወት አለ? ብዬ ልጠይቃት ፈለግኩ እና ወሬውን ብታቋርጥብኝስ ብዬ ፈርቼ ዝም አልኩ።) መቼም እንዴት ይሳሳልሽ እንደነበር ምንም ቃል አይገልፀውም! የትም ቦታ ሲሄድ ትከሻው ላይ ሰቅሎሽ ነበር የሚሄደው። ከአራት አመት በኋላ ወንድምሽን ብንወልድም አባትሽ ከወንድምሽ ይልቅ ትኩረቱ አንቺ ነበርሽ። እያደግሽ እንደእኩዮችሽ እንጀራ ማስፋት ከመማር ይልቅ የአባትሽን መሳሪያ መወልወል እና ፈትቶ መግጠም ነበር የሚያስደስትሽ። አድገሽ ምን መሆን ነው የምትፈልጊ ስትባዪ <ሽፍታ> ነበር የምትዪው (ፈገግ አለች እና የሽፍታ ትርጉም እንዳልገባኝ ጠርጥራ መሰለኝ ቀጠለች።) አባትሽ ወታደር ነበር። ከውትድርና ከተመለሰ በኋላ ቀዬአችን በማይረባ የይገባኛል ሽኩቻ ስትታመስ አባትሽ ራሱን የቀዬው ጠባቂ አድርጎ ሾመ። ዋጋ እንደሚያስከፍለው ብነግረውም አልሰማኝ። የእርሱ ቢጤ ደጋፊዎቹን አስከትሎ ጫካ ገብቶ ሸፈተ።»

«አባቴ ያጨስ ነበር?» አልኳት

«ከጊዜ በኋላ ያመጣው ዓመል እንጂ አጫሽስ አልነበረም።» ካለችኝ በኋላ በጥርጣሬ ዓይን አተኩራ አየችኝ።
«የወታደር ልብስ ቀለም ያለው የሲጋራ መለኮሻ እቤቴ ካዝና ውስጥ አጊንቼ ነበር። የሆነ ብልጭ የሚል ምስል ጭንቅላቴ ውስጥ ሽው ይላል። የሆነ ደም የነካው እጅ ያንን የሲጋራ መለኮሻ ይዞ …… ፊቱ ወይም የቀረው ሰውነቱ አይመጣልኝም። ፍርጥም ያለ ሰፊ በደም የራሰ ጠይም እጁ ብቻ ነው የሚታየኝ።» እያልኳት ጭንቅላቷን በአወንታ እየነቀነቀች ፊቷ ላይ የነበረው ደስታ በአንዴ ድፍርስርስ ብሎ ሃዘን ይንጣት ጀመር። ማስረዳት የማልችለው ስሜት አባቴ እንደሞተ ነገረኝ። ያ ቀን እጁ …..የሚታየኝ ቀን ….. አባቴን ያየሁበት የመጨረሻ ቀን መሆኑን ገመትኩ። 

«ሞቷል አይደል? ምን ሆኖ ነው የሞተው? ሰው ነው የገደለው? ሲሞት አጠገቡ ነበርኩ አይደል? የሚታየኝ ምስል የሞተ ቀን ነው አይደል?» ቃላት ከአፏ ማውጣት አቅቷት በጭንቅላቷ ንቅናቄ ብቻ አዎ አለችኝ ከእንባዋ ግብግብ እየገጠመች። ዝም አልኩ። ዶክተሩ የሲጋራ መለኮሻ ላይተሩን ፣ ሽጉጡን ፣ ንቅሳቴን ሳይ ሽው የሚልብኝን አንድ የሰው እግር እና ጨለማ ክፍል ፣ ፎቶውን ሳይ የተሰማኝን የሳር እርጥበት ስነግረው

«ምንም እንኳን ያለፈ ትውስታሽን ብታጪ ጭንቅላታችን ያሳለፍነውን ከባድ ጊዜያት ወይም ትሮውማ የፈጠሩብንን አጋጣሚዎች በተለየ መዝግቦ የመያዝ አጋጣሚው ሰፊ ነው። ከገጠመኙጋ የሚያያዙ ነገሮች ስታዪ ጭንቅላትሽም ሰውነትሽም ሪአክት ያደርጋል። ምናልባት በተለየ ያስታወስሻቸው ነገሮች እንደእነዚህ ያሉ ክስተቶች ይሆናሉ።» ብሎኝ ነበር። ያ ቀን ፣ ያ የሲጋራ መለኮሻ ላይተር ፣ የሚታየኝ የአባቴ እጅ …….. የመራራዋ ሜላት ጥንስስ ሊሆን እንደሚችል አሰብኩ። ስለዛ ቀን እንድትነግረኝ ፈለግኩ ግን ደግሞም ፈራሁ። ክፉ ትውስታዎቼ ሁሉ ግልብጥ ብለው የሚመጡብኝ መሰለኝ። ትናንቴን መፈለጌ ውስጥ እስከዛሬ ያላሰብኩበት ነገር ሰውነቴን አደነዘዘኝ።

ትናንቴን ሳገኘው ተመልሼ የትናንትናዋን ሜላት ብሆንስ? ከትውስታዬጋ ማንነቴም ተመልሶ ቢመጣስ? ያቺን ሴት ተመልሼ መሆን እንደማልፈልግ እርግጠኛ ነኝ። ግንሳ ያቺን ሴት ያደረጉኝን መንገዶቼን ሳውቅ ቂሜ ፣ መከፋቴ፣ ንዴቴ ፣ መራርነቴ ፣ ሁሉም ስሜቶች ከትውስታው ጋር መጥተው ይወሩኝ እና ያቺን ሜላት እንቢ ብዬ ላመልጣት ባልችልስ?

«ማነው የገደለው?» አልኳት ሳላስበው ውስጤ የሆነ የተለየ ስሜት እያፈነው። ምናልባት ያቺ አባ የነገሩኝ በቀለኛዋ ሜላት ተሸፍና እንጂ አልጠፋች ይሆናል።

« የእኔ አበባ አባትሽን የገደሉትን ሰዎች አድገሽ አንድ በአንድ ተበቅለሻቸዋል። አታስታውሺው ይሄ ይቅርብሽ!! » አለችኝ በልመና።
«አባቴ ሲሞት ስንት ዓመቴ ነበር?» አልኳት ውስጤን የአባቴን መልክ የማስታወስ ከፍተኛ ፍላጎት እያተራመሰው። ወዲያው ቀጥዬ «አባቴ ምን ይመስል ነበር?»
2.2K viewsDAVE / PAPI, 07:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 10:48:04 ቁስሌ አገግሞ ከሆስፒታል ከወጣሁ በኋላ ፤ ጎንጥ አንቱ እና አንቺ ማምታታት ካቆመ በኋላ ፤ እቤት እንደገባሁ ሰፋፊ ጅንሶች እና ብረታ ብረት የበዛባቸው ልብሶቼን ካቃጠልኩ በኋላ ፣ ብዙ ነገሮችን እንደአዲስ ከተማርኩ በኋላ ፤ እናት እና ወንድሜን ለማግኘት ብዙ ያልተሳካ ፍለጋ ካደረግኩ በኋላ ፣ አባን ደግሜ አጊንቼ ጉልበታቸውን ተደግፌ ከተመከርኩ በኋላ ፣ ብዙ ቀናት ዳዊት ደውሎ ከተልመጠመብኝ በኋላ …….. ስልኬ ጠራ!

«ሜላት ነሽ? አስካለ ደውዪላት ብላኝ ነው።»

«አስካለ? አስካለ?»

«እናትሽ !» አባባሏ መገረም ነበረው። ከተቀመጥኩበት ዘልዬ ተነሳሁ።

«የት ልምጣ?» አልኩኝ ሳላስበው።

«ህም! እቤት ገብታለች። ዛሬ ነገ ሳትዪ መጥተሽ እያት! ጥሩ ሁኔታ ላይ አይደለችም!» ያለችኝ ቤቱን እንደማውቀው እርግጠኛ ሆና ነው።

«እባክሽ የቤቱን አድራሻ ንገሪኝ?» አልኳት ገና ሳትጠይቀኝ እንዴት የእናቴን ቤት እንደረሳሁት ማብራራት እያደከመኝ። አልጠየቀችኝም። እጅግ ግርምት ባለበት አነጋገር ሰፈሩን ነገረችኝ።

«ስትደርሺ ደውዪልኝ እና እመራሻለሁ!» ብላ ስልኩን ዘጋችው። ለተወሰነ ደቂቃ በቆምኩበት ደርቄ ቆየሁ። እየቆየሁ እንደመባነን ነገር አደረገኝ እና ልብሴን መቀያየር ጀመርኩ። ከታች ቀይሬ ከላይ ሳልቀይር ወደሳሎን ተመልሼ ጎንጥን መጣራት ጀመርኩ።

«በትክክል እናትሽ ባይሆኑስ?» ብሎ ያላሰብኩትን ጥርጣሬ አቀበለኝ የተደወለልኝን ስልክ ስነግረው

«ማረጋገጥ የምንችልበት ብቸኛ መንገድ ስንሄድ ብቻ አይደል?» አልኩት። ተመልሼ የቀረኝን ልብስ ቀያይሬ ስመለስ እሱ መኪናውን ከጊቢ እያወጣ ነበር።

በስልክ እየተመራን ደረስን። ልቤ እየዘለለች በአፌ ልትወጣብኝ ታገለችኝ። በስልክ ያናገረችኝ ሴት በሩ ላይ ጠብቃን እየመራችን ወደጊቢው ስንዘልቅ ጎንጥ እጄን ያዝ አድርጎ ከፊቴ ቀደመ። በአንድ እጁ አንድ እጄን እንደያዘ ሌላኛውን እጁን ወደ ወገቡ አካባቢ ሲሰድ ዓይኔ እጁን ተከትሎ የጨበጠው ነገር ላይ አረፈ። በደረበው ጃኬት ስር ሽጉጥ ይዟል። መጮህ ቃጣኝ ነገር እና የሆነ ድምፅ አወጣሁ።የያዘውን እጄን ሳላውቅ መነጨቅኩት።  ሴትየዋ ስትዞር ደንግጬ ቆምኩ። ከዚህ በኋላ ልቤን እንዲህ የሚያስደልቃት የጎንጤ ሽጉጥ ይሁን እናቴን ማግኘት አልገባኝም። እግሬን ብርክ ያዘው። ጎንጥ መልሶ እጄን ቀለበብኝ እና ወደጆሮዬ ጠጋ ብሎ

«ምን እንደሚገጥመን አናውቅም! መሳሪያ ቢገጥመኝ በባዶ እጄ ልጠብቅሽ አልችልም!! » አለኝ ድምፁ ቁጣ ነገር አለው። የሆነ <ዋጥ አድርጊያት> የሚል ዓይነት ቁጣ …… ምርጫ ነበረኝ? ማሰቢያ ጊዜ አልሰጠኝም። ድንጋጤዬን ዋጥ አድርጌ ተከተልኩት። ሴትየዋ እየመራች የሆነ ድክም ያለ ባለሁለት ክፍል ቤት አስገባችን!!

                  ………. ይቀጥላል ………..

@wegoch
@wegoch
@paappii
2.5K viewsDAVE / PAPI, 07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-27 10:48:04 #የመኖር አካፋይ ፣ የመ ፤ ሞ ፣ ት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል አስር)
(ሜሪ ፈለቀ)


«ንገረኛ? የማንን ፊት ነው ያየኸው?»

«የሚያውቋቸው  እ የምታውቂያቸው ሰዎች አይደሉም!! ከራሴ ያለፈ ህይወት ጋር እንጂ ካንቺ ጋር የሚያያዙ ሰዎች አይደሉም!»

«ንገረኛ ልወቃቸው? አሁንኮ ከእኔ ህይወት ጋርም የሚያገናኛቸው ድርጊት ኖረ አይደል?»

«እትይ አያስጨንቁኝ ስለራሴ ማውራት አልፈልግም!» ካለ በኋላ አንቱ ማለቱ ሲታወሰው «አይ እንግዲህ! እትይ ሱሪ ባንገት አያድርጉብኝ ቀስ ብዬ ልልመደው!» አለ እጁን አየር ላይ እየወረወረ። የሆነች ጥርጣሬ ልቤ ውስጥ ተሰነቀረች። ቅሬታ ያቀፈች ትንሽዬ ጥርጣሬ …… መከፋት ያዘለች ትንሽዬ ጥርጣሬ …… በእንባ የዳመነ ዓይኔን ያስከተለ ትንሽዬ ጥርጣሬ ……. የገባው መሰለኝ አልጋው ጠርዝ ላይ እየተቀመጠ ድምፁን ዝግ አድርጎ

«እትይ ጠረጠሩኝ እንዴ?» ሲለኝ በትክክል የጠረጠርኩት ምን እንደሆነ ጠፋኝ! ቅሬታዬ ማን መሆኑን አለማወቄ እንጂ ልቤን በየትኛውም ጠርዝ ብበረብረው ይጎዳኛል የሚል የጤፍ ፍሬ የምታክል ጥርጣሬ አጣሁ። እንዴት ነው ማን መሆኑን የማያውቁትን ሰው በዚህ ልክ ማመን የሚቻለው?

«አላውቅም! አትቀየመኝ ጎንጥ አላውቅም! …….. በየትኛውም አቅጣጫ ብዞር ካንተ ሌላ ፊቴን ላዞር የምችልበት ሰው የለኝም ፤ ብቸኛው የማልፈራበት ሰዓት አንተ አጠገቤ ስትሆን ብቻ ነው ፤ ያለቅዠት የምተኛው እንኳን አንተ እጆቼን ስትይዘኝ ነው። በዚህ ርቀት የተደገፍኩት ሰው ማን እንደሆነ አለማወቅ ……. » ሳልጨርስ ሀሳቤን ቀማኝ

«እትይ ያለፍኩትን መንገድ አለማወቅዎ የሚያውቁትን እኔን እንዴት ያጠፋብዎታል? (<እኔን > ሲል ደረቱን በቡጢ ነገር ደለቅ ደለቅ አደረገ።) ትናንት ምንም ዓይነት ሰው የነበርኩ ቢሆን እንዴት ዛሬ ላይ የሆንኩትን እኔን ይውጠዋል?» አለኝ ማባበል ባለው ድምፅ

ይሄ <ትናንት> የሚሉት ጦስ ይኸው ዛሬዬን መዞሩን አልተወም!! የሰው ልጅማ ትናንቱን ነው ብያችሁ አልነበር? ነው ግን?

ጎንጥ ዛሬ የማውቀው ፣ ልቤ ያለገደብ የተደገፈው ደግ ፣አማኝ ፣ ለሳምንታት ለሊቶቹን ጎኑን ሳያሳርፍ የሆስፒታል አልጋ ላይ አንገቱን ደፍቶ እጆቼን ይዞ የተኛው ፣ ጎንጥ ነው ወይስ የማላስታውሰው እና የማላውቀው ያለፈ ትናንቱ ውስጥ ያለው እሱነቱ? አያድርገው እና በማላውቀው ትናንቱ ክፉ ሰው የነበረ ቢሆን ዛሬ የሰጠኝን የደግነት ጥግ አጣፋበታለሁ? እሱ ለትናንቱ ክፋቴ ሳይሆን ለዛሬ መሸነፌ ህይወቱን አደጋ ላይ ጥሎ የደበደቡኝን ሰዎች ደብድቦልኝ የለ?

ትናንትማ የዛሬ ማንነታችን መንገድ እንጂ የእኛነታችን መገለጫ አይሆንም። ትናንት ማንነት ቢሆን የትናንት ትውስታ የሌለኝ እኔ ማንነት ላይኖረኝ አይደል? ትናንት ለዛሬ ማንነታችን መንገድ ነው!! እርግጥ መንገዱ ለዛሬ መዳረሻ የሚያዋጣው ምሰሶ እና ማገር ዛሬ ለቆምንበት እኛነት መሰረት ነው።

«ቃሌን እሰጥሻለሁ!! አቅሜ በፈቀደ ሁሉ እጠብቅሻለሁ!! በምችለው ሁሉ ማንም እንዳይጎዳሽ መድረስ ያለብኝ ጥግ ድረስ እደርሳለሁ። እትይ? እንዲያምኑ …. እንድታምኚኝ እፈልጋለሁ? እ? በአምላክ ስም እምልልሻለሁ አንቺን የሚጎዳ ነገር አላደርግም! እ?» እያንዳንዱን ዓረፍተ ነገር <አንቺ> ብሎ ለመጨረስ እየታገለ <እትይ> ማለቱ ፈገግ አስባለኝ።

«እንደማትጎዳኝ ልቤ ያምንሃልኮ …… አላውቅም! ምናልባት እኔ አንድም ነገሬ ሳይቀር ለትናንትም ለዛሬም እንዳመንኩህ ሁሉ ትናንትህን ልትነግረኝ እንድታምነኝ ፈልጌ ይሆናል። አላውቅም!»

«አሁን አይደለም! እትይ እባክዎ አያስጨንቁኝ! ጊዜው ሲሆን አወጋዎታለሁ!»

«እሺ!» ብቻ አልኩኝ። እንደቅድሙ ጀርባዬን እያሻሸ በዓይኖቹ ሌላ ቦታ ተጓዘ። ልቡም ዓይኑን እንደተከተለው ያስታውቃል።

«እትይ ካልከኝ ቀጥለህ አንቺ ልትለኝ አትችልም! በስሜ ጥራኝ ! ስሜን አትወደውም እንዴ ለምን ከበደህ?» ስለው እንደመባነን ነገር ብሎ

«ኸረ ይቅር ይበሎት!» ካለ በኋላ ራሱ ሳቀ …….. ብዙ ጊዜ አይስቅም! ከንፈሩን ለወጉ ሸሸት ያደርጋል እንጂ! ሲስቅ የሚያማምሩት ችምችም ያሉ ጥርሶቹ ብቻ አይደለም የሚስቁት ዓይኑም ፣ ግንባሩም ፣ ጉንጩም ይስቃሉ። እያየሁት እንደሆነ ሲያውቅ ጥርሱን ከድኖ በከንፈሩ ብቻ ፈገገ።

«ሜ - ላ - ት » አለ የሆነ አጠገቡ ያለሁትን እኔን ሳይሆን እሩቅ ያለ ሰው አስታውሶ የሚጠራ በሚመስል ድምፅ

«አየህ ? አያንቅህም ወይ ትን አይልህም! ደግሞ አፍህ ላይ ያምራል!» ብዬው ሸርተት ብዬ ተኛሁ። እንደተለመደው ወንበሩን ወደ አልጋው ጠጋ አድርጎ ተቀምጦ ሲያበቃ እጄን ያዘኝ። መልእክቱ ዓይንሽን ከድነሽ ማረፍ ትችያለሽ ነው። እንደማመስገን ነገር የያዘኝን እጁን ጨበጥ ሳደርገው ጥርሱን ነክሶ ፊቱን ቀጨም አደረገ።

«ውይይ ይቅርታ ረስቼው ነው» ብዬ እጄን አስለቀቅኩ። ከንፈሩን አሽሽቶ መልሶ እጄን ያዘኝ። እንደደከመው ያስታውቃል። ምናልባት እንቅልፉን ከተኛ ብዙ ሰዓታት አልፈውት ይሆናል። ምናልባት እህል የአፉን ደጃፍ ካለፈ ቆይቷል። ምናልባት ያበጡት እጆቹ እና የበለዘ አይኑ እየቆጠቆጠው ይሆናል። ለመጀመሪያ ጊዜ ከፀጉሩ ጀምሮ ፍትፍት አድርጌ በዓይኔ አስተውለው ጀመር። እያደገ ያለ ያልተበጠረ ጥቁር ፀጉሩ ፊት ላይ በጎን በኩል ሆነ ብሎ ያቀለመው የሚመስል ሽበት አለው። ግንባሩ ላይ ያሉት የሚኮሳተርባቸው መስመሮች ሞገስ ነገር ሆነውታል ልበል? ዓይኖቹ ብቻቸውን መሳቅም መኮሳተርም ያውቁበታል። ዓይኖቼን በዓይኖቹ ሲቀልብብኝ አፍንጫ ፣ ከንፈር ፣ አገጩን ዘልዬ ትከሻው ላይ ደረስኩ። ትከሻው ስፋቱ ተጣበው ቢቀመጡ ….. ሁለት በአንደኛው ጎን ሁለት በሌላኛው ጎን አድርጎ  አራት ህፃናት ያሰፍራል። ደረቱ ቀብረር አድርጎ አስር ኪሎ ፍትግ ገብስ ያሰጣል። ክንዱ ……… ክንዱ እየደማ ነው! የለበሰውን ግራጫማ እጅጌ ያለው ቲሸርት እያረጠበው ነው።

«እየደማህ እኮ ነው! » ብዬ ጮህኩ። ዓይኔን ተከትሎ እየደማ ያለ ክንዱን አየት አደረገ እና ህመሙን ሊደብቀኝ እንደፈለገ በሚያቃጥርበት ሁኔታ

« እ ትንሽዬ ቁስል ናት!» ብሎ በእጁ ደገፍ አድርጎት ተነሳ። ከዓይኖቼ ርቆ ደሙን ሊጠራርግ እንደሆነ ገብቶኛል።

«አሳየኝ?  ትንሽዬ አይሆንም አሳየኝ !» ብዬ ስጮክበት የለበሰውን ቲሸርት በቀስታ በአንድ እጁ በኩል ወደላይ አውልቆት ተቀመጠ። ቁስሉ በነጭ ፋሻ ታሽጓል። እኔጋ ከመምጣቱ በፊት ሀኪም ቤት ሆዶ የነበረ ሰውዬ ነው ይሄን ሁሉ ሰዓት ህመሙን ውጦ አጠገቤ የተቀመጠው? ወይስ ስቃዩን አላስተዋልኩለትም?  የታሸገበትን አልፎ ነው ደሙ ልብሱን የነካው።

«በምንድነው የተመታኸው?» አልኩት

«ስለት ነው! » ካለ በኋላ ፊቴን አስተውሎት «መድሃንያለም በሚያውቀው ብዙ አይደለም! ከላይ ነው ጨረፍ ያደረገኝ! ደሙ ዝም ብሎ ሲያዳምቅ ነው!» አለኝ።

«እሺ የታሸገበትን ይቀይሩልህ እና እቤት ሄደህ እረፍ! ተናኜን ላካት!» አልኩት አልሰማኝም! ወጥቶ ቁስሉን አሳክሞ ተመልሶ መጣ ወደቤት ግን አልሄደም!



                                                 *****
2.2K viewsDAVE / PAPI, 07:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 08:59:52 በትክክልም ክፉ ሴት ነበርኩ ማለት ነው። የሚያዩኝ ሰዎች ዓይን ውስጥ ለሞላው ጥላቻ እና ፍርሃት ምክንያት ከክፉነቴ ውጪ ሌላ ሰበብ የለም። ባለፉት ቀናት ሁሉ የምሰማውን ድርጊቴን ምክንያት እያጋባሁ <እንዲህ ስለሆነ ሊሆን ይችላል ይሄን ያደረግኩት> እያልኩ ድርጊቴን በሰበብ እየደገፍኩ ራሴን ይቅር ለማለት ፣ ያለፍኩትን ጥፋት ለመካስ፣ በንሰሃ ተመልሼ የበደልኳቸውን በመልካም ስራ ልዋጅ ……… አውጠንጥኜ ነበር። የትኛውን ሀጢያቴን ከምን ጀምሬ ነው ይቅር የምለው? ማን ያውቃል ከዚህ የባሰም ፀያፍ ነገር ሰርቼ ይሆናል።

«ጎንጥ?» አልኩት ሰውየው ከወጣም በኋላ እዛው በቆመበት የነበረውን ጎንጥን

«አቤት እትይ?»

«ህገ-ወጥ አይደለም በሴቶች መነገድ? ያለው በሙሉ እውነቱን ይመስልሃል? መቼም ህግ መንግስት ባለበት ሃገር እንዲህ አይነት ነገር ስሰራ አንድ እንኳን ለህግ የሚያቀርበኝ ሰው ጠፍቶ ነው? ወይስ ህገ-ወጥ አይደለም?»

«አላውቅም እትይ! ስለነገርየውም ሰምቼ አላውቅ!»

«ነውረኛ ሴት ነበርኩ አይደል? አንተም አውቀህ እየደበቅከኝ እንጂ ብዙ የሰማኸው እና የምታውቀው ነውር አለኝ አይደል? ንገረኝ እስኪ ምን ዓይነት ሴት እንደነበርኩ እያወቅክ አሁንም ድረስ ለምን ትጠብቀኛለህ? ለአንተም ለተናኜም ቢሆን ክፉ ሴት እንደነበርኩ ግልፅ ነው። እንዴት ነው በደሌን ረስታችሁ ከጎኔ የቆማችሁት? እስኪ ንገረኝ አንተንስ ምን ቀምቼህ ይሆን? »

«እትይ ደክሞዎታል ትንሽ ይረፉ ግድ የለም!»

«አንቱ አትበለኝ ማለት አይሰማህም?» በማን እንደተናደድኩ አላውቅም ግን እየተቆጣሁ ነው።

«ይሁን! ይሰማኛል! አንቺ እሎታለሁ። ግን እንደው እትይ በማያስታውሱት ነገር መብሰክሰኩ ምንም ፋይዳ የለውኮ! …….»

«አንቱ አትበለኝ! አንቱ የሚባለው የሚከበር ሰው ነው። አንቱ የሚባለው ክብርን ለመግለፅ ነው። ለየትኛው ክብሬ ነው አንቱ የምትለኝ?» አሁንም እየተቆጣሁ እና እየጮህኩ ነው። እየተቆጣሁ ያለሁበት ምክንያትም እየተቆጣሁ ያለሁትም ሰው የቁጣዬ መንስኤ አለመሆናቸውን ባውቅም ልቆጣጠረው ግን አልቻልኩም። አልጋው ጫፍ ላይ በአንድ ጎኑ ተቀምጦ በግንባሩ እያየኝ እኔ ከምናገርበት ድምፅ በተቃራኒ በእርጋታ እና በለሆሳስ

«እትይ ማንም የነበሩ ቢሆን አለቃዬ ነበሩ! ኖትም! አለቃን አንቱ ማለት ያደግኩ የጎለመስኩበት ስርዓት ነው። ተው ካሉኝ ካስከፋዎት እተዋለሁ። ግን ከበሬታዬን  የተውኩ እንዳይመስልብኝ!»

«አዎ ተው!» አልኩኝ ስናገር በነበረበት ቁጣ

«እሺ እተዋለሁ!» አባባሉ የተረጋጋ ነገር ....... የተከፋ ሳይሆን ለእኔ ያዘነ ዓይነት ነው። ለምን እሱ ላይ እየተናደድኩ እንዳለሁ አላውቅም። የሚያውቀውን ሁሉ አልነገረኝም ብዬ ስላመንኩ? ጭርሱኑ አብልጦ ሊጠላኝ ሲገባ አብልጦ ስለተንከባከበኝ? ወይስ የክፋቴን ልኬት በሱ ጥላቻ ልክ መመዘን ፈልጌ? ከሁሉ ከሁሉ ሚዛኔ እሱ እንዲሆን ለምን ፈለግኩስ?  ለደቂቃ ዝም ማለቴን ተከትሎ እንደቅድሙ ጀርባዬን በቀስታ ወደላይ እና ወደታች ማሸት ጀመረ። ውስጤ እየጎፈላ የነበረ ንዴቴ እየበረደ በምትኩ ሀዘን እና ተስፋ መቁረጥ ተተካ። የፈለግኩት ማልቀስ ነበር።

« እንዴት አገኘሃቸው? ፖሊስ እንኳን ፈልጎ ያላገኛቸውን አንተ እንዴት አገኘሃቸው?» አልኩት ድንገት

«ፖሊስ አልፈለጋቸውም። ያልተፈለገ ወንጀለኛ እንዴት ይገኛል? መድሃንያለም ብቻ በሚያውቀው ምክንያት ፖሊሶቹ ይሄን ጉዳይ መንካት አልፈለጉም። እንደው እትይ ልቤ ሲነግረኝ የተኮሰቦትንም ሰው መፈለጉን እርም ብለው ትተውታል።»

«እነሱ እንዴት አላገኟቸውም አይደለም ያልኩህ አንተ እንዴት አገኘሃቸው ነው ያልኩት። ደግሞ አሁንም አንቱ ማለትህን ተው!» አልኩት በደከመው ለዛ

«መንገዱ ምን ያደርጋል እትይ? ዋናው መዳረሻውም አይደል? እንዴት እንዳገኘሁት ዝርዝሩ ምን ይፈይዳል? ዋናው መገኘቱም አይደል?»

«ለእኔ ዝርዝሩ ይረባኛል! ማወቅ እፈልጋለሁ። አውቀህ ነው የምትጠመው?» አልኩት መልሼ እየተቆጣሁ።

«ካሉ መልካም ….. ይቅር ይበሉኝ  ካልሽ ይሁን! የሰው ፊት አየሁ!» ብሎኝ ይቀጥላል ብዬ ስጠብቅ ልክ የጠየቅኩትን የመለሰ ይመስል ዝም አለ።

«ምን ማለት ነው?»
«እንዴት አገኘኻቸው? አይደልም ጥያቄ …. ዎ …ሽ ? <የሰው ፊት አይቼ!> ነው መልሱ! ከሰው ፊት ቆምኩ!» አለ መልሶ። ከሰው ፊት መቆም ወይም የሰው ፊት ማየት ሀሳቡ የደበደቡኝን ሰዎች ከማግኘት ጋር የሚያያዝበት ገመድ በግልፅ ባይገባኝም እሱ ሲለው ደስ የሚል ነገር እንዳልነበረ ለማወቅ አልተቸገርኩም። ቃላቶቹን እየረገጣቸው ባለመደሰት ነው ያወራው።

«የማንን ፊት ነው ያየኸው? ማን ፊት ነው የቆምከው?» እያልኩት በጭንቅላቴ ውስጥ ድንበር ላበጅለት የማልችለው ሀሳብ ይጓዛል። ጎንጥ ራሱ ማን ነው? ፊቱን አይቶት ወይም ፊቱ ቆሞ ከመኪና ታርጋቸው ውጪ ስለማንነታቸው ምንም ፍንጭ ያልነበራቸውን ደብዳቢዎቼን ያስገኘለት ማነው? ለሰከንድ ክፉ ሀሳብ ሽው አለ። ጎንጥ ራሱ ነኝ ያለኝን ሰው ባይሆንስ?


                                         ………………….  ይቀጥላል   …………………………

@wegoch
@wegoch
@paappii
2.5K viewsDAVE / PAPI, 05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-26 08:59:52 #የመኖር አካፋይ ፣ የመ ፤ ሞ ፣ ት ሲሶ ፣ መንገድ መሃል ………… (ክፍል ዘጠኝ)
(ሜሪ ፈለቀ)

ፍርሃት ልቤን ከደረቴ ጎትቶ ሊያስወጣት ታገለኝ። ሳይታወቀኝ ዓይኔን ከድኜ እግሬን ሰብስቤ ጉልበቴን አቅፌ ጥቅልል አልኩ። ጎንጥ በፊት ለፊቴ መጥቶ ጉልበቴን ያቀፍኩበትን እጄን አምባር ማሰሪያው ጋር ያዝ ሲያደርገኝ ዘለልኩ። ሰውነቴ በሙሉ እየተንቀጠቀጠ ነበር። በሌላኛው እጁ ጀርባዬን እንደልጅ አሸት አሸት አደረገኝ እና ወደጆሮዬ ጠጋ ብሎ

«እትይ ይቅርታ ሊጠይቆት ነው የመጣው! እኔ እዚህ ቆሜ ማን አባቱ ምን ያደርገኛል ብለው ነው የሚፈሩት?» ያለኝ መርበትበቴ አናቴ ላይ ወጥቶ የሰማሁት የቅዠት ድምፅ ይሁን ወይም ያለው ነገር ከነጭራሹ የገባኝ ይሁን እንጃ ብቻ የተናገረበት ድምፅ እና ጀርባዬን ከላይ ወደታች እያሸ የሚያባብለኝ እጁ አላውቅም በአፌ ልትወጣ ጉሮሮዬጋ እየደረሰች የምትመለስ ልቤን በቀስታ ወደቦታዋ መለሳት። በቀስታ ዓይኔን ገልጬ ሰውነቴን ዘና ለማድረግ እየሞከርኩ እየሆነ ያለውን ማጤን ጀመርኩ። እንግዳው ሰው በእኔ አልጋ እና በበሩ መሃል ያለ ቦታ ላይ ቆሞ አንዴ እኔን አንዴ ጎንጥን ያያል። ይሄኔ ነው ከደበደቡኝ ሰዎች መሃል አንዱ መሆኑ የገባኝ እንጂ የዛን እለት ምሽት ፊታቸውን በስርዓት የማይበት እድል ስላልነበረኝ ላውቀው አልችልም ነበር። አይቼው የነበረ ቢሆንም እንኳን በዛሬው ሁናቴው ላስታውሰው አልችልም ነበር። ፍርሃቴ ትንሽ ገለል ሲልልኝ ፊቱ ‘ንፋሱ ተንፍሶ ህፃናት እየተቀባበሉ የተጫወቱበት ኳስ’ መስሎ መጨረማመቱን አየሁ። ግንባሩ ላይ ሁለት ትንንሽዬ ፕላስተር ተለጥፎበታል። ጎንጥን አየሁት። በዓይኑ ሰውየውን ወደ እኔ እንዲጠጋ አሳየው። በዓይኑ ገፈተረው ብል ይቀለኛል። ወደ እኔ እየተራመደ ሲጠጋ እያነከሰ መሆንኑን አስተዋልኩ።

«ይቅርታ!» አለኝ አጠገቤ ደርሶ መሬት መሬቱን እያየ። ጎንጥ የሆነ መልእክት በማስተላለፍ አይነት ጉሮሮውን ጠረገ።

«ይቅርታ አድርጊልኝ! አንቺ ላይ እጃችንን ማንሳት አልነበረብንም! በእኔም በጓደኛዬም ስም ይቅርታ እንድታደርጊልን ልለምንሽ ነው የመጣሁት!» ብሎ እሱም የሆነ መልእክት እንደማስተላለፍ ጎንጥን አየው። ጎንጥ ጭንቅላቱን በአወንታ ነገር ነቀነቀ።

«እሺ» ከማለት ውጪ ግራ የገባው ጭንቅላቴ መልስ አላቀበለኝም። እንደአመጣጡ ፊቱን አዙሮ እግሩን እየጎተተ ሲወጣ ጭንቅላቴ ያልተዘጋጀበትን ጥያቄ አፌ ጠየቀ

«ለምን? ለምንድንነበር ግን እንደዛ ያደረጋችሁት?» አልኩኝ። መለስ ብሎ እኔን ሳይሆን ጎንጥን አየው። እኔም ወደእሱ ዞርኩ።

«የተጠየቅከውን መልስ!» አለው እንደትእዛዝ

«እህቴን …… ፍሪታን ስለቀማሽኝ። ተናድጄ ነበር። በፀባይ ላናግርሽ ስራሽ ቦታ ድረስ ብመጣም አላገጥሽብኝ። እኔ አቅሜ ጉልበቴ ብቻ ነው። አንቺ የገንዘብ አቅም አለሽ ፣ በአንድ ፉጨት ያልሽውን የሚፈጽሙልሽ ቁልፍ ሰዎች አሉሽ፣ ፖሊሶቹ በእጅሽ ናቸው፣  በዛ ላይ ጉልበትም መሳሪያም አለሽ! ........ በእህቴ ገላ አንቺ ገንዘብሽን ስታካብቺ አንጀቴ እየተቃጠለ ዝም ከማለት ውጪ ምንም ማድረግ አልቻልኩም ነበር። ባለፈው ሳምንት አደጋ ደርሶብሽ ምንም እንደማታስታውሺ ስሰማ ደስ አለኝ። (ቀና ብሎ ጎንጥን አይቶ ቀጠለ) እየተከታተልኩሽ ነበር። » ብሎኝ ትከሻውን ሰበቀ። ምንም እንደማላስታውስ ካወቀ የነገረኝ ነገር እንደማይገባኝ እንዴት ጠፋው? ቀና ብዬ የአልጋውን ራስጌ ተደግፌ ተቀመጥኩ። ከምን ጀምሬ ምን እንደምጠይቀው ግራ ገባኝ። ከነአካቴው መጠየቁ ራሱ ልክ ይሆን አላውቅም! የተናገረው ነገር ውስጥ ምንም ለልክ የቀረበ ድርጊት መች አለ? አሰላስዬ ሳልወስን አፌ ቀደመኝ።

« እህትህን? ምን አድርጌ ነው የነጠቅኩህ? በእህቴ ገላ ያልከኝ እህትህ ምንድነው የምትሰራው? እንዴት ነው እኔ በእህትህ ….. (እሱ ያለውን መድገም ዘገነነኝ) እየተከታተልከኝ ከነበር ምንም እንደማላስታውስ የሰማኸው እውነት መሆኑን ማረጋገጥ አይከብድህም መቼም? » አልኩኝ ፍርሃቴ ድምጥማጡ ጠፍቶ። እሱ አሁንም በማስፈቀድ አይነት ጎንጥን አየው። በቁመት ከጎንጥ ጋር ተቀራራቢ ናቸው። ጎንጥም ግዙፍ ዓይነት ወንድ ቢሆንም ደብዳቢዬ ግን የበለጠ ጡንቻው የተወጣጠረ እና ደረቱ የተነፋፋ ነገር ነው። እጅ በእጅ ቢያያዙ ማንም ሰው የሚያሲዘው በደብዳቢዬ ጡንቻ ነው። ታዲያ ጎንጥ ምን ቢያደርገው ወይስ ምንስ ቢለው ነው ይሄን የሚያክል ሰውዬ እንዲህ የሚንበጨበጨው? የተነፈሰ ባሎኒ ኳስ ካስመሰለው በኋላ እንኳን እዚህ ድረስ መጥቶ ይቅርታ እንዲጠይቀኝ ያስደረገው ያልገባኝ ነገር ምን ተከውኖ ነው?

«እናንተ ቤት ስትሪፐር ናት! (እንደማፈርም እንደማዘንም የቀላቀለው ስሜት ድምጹን ወሮታል። ያለኝ ነገር እንዳልገባኝ ሲያውቅ አሁንም ጎንጥን ዞሮ አየው። ጎንጥ በአይኑ <ቀጥል> እንደማለት ነዳው።) አንድ እህቴ ናት ያውም ታናሼ! ልጠብቃት ይገባ ነበር። ማታ ማታ ሆቴል ውስጥ ሪሴፕሽንነት ስራ አገኘሁ ስትለኝ እንኳን <አይሆንም አንቺ አርፈሽ ተማሪ። እኔ አኖርሻለሁ> ብያት ነበር። እንቢ ብላ ስራውን መጀመሯን ነገረችኝ። የምትሰራበትን ቦታ ልትነግረኝ አለመፈለጓ ስለከነከነኝ የሆነ ቀን ተከተልኳት እና እናንተ ክለብ ደረስኩ። (ለሰከንዶች ዝም አለ። የሆነ የሚቀጥለውን ለመናገር ጉልበት እንደሚሰበስብ ያለ ዝምታ) በአይኔ እንኳን ጫን ብዬ ላያት የምሳሳላት እህቴ ስራዋ እቤታችሁ ለሚመጡ ነውረኛ ባለስልጣናት እና ባለሃብቶች እርቃኗን እየደነሰች ማስደሰት መሆኑን አየሁ።» ብሎ ሆነ ብሎ ይመስለኛል ፊቴ ላይ አተኮረ። መደበቅ ያልቻልኩት ድንጋጤ እና መደናገር ፊቴ ላይ ተተረማመሰ። እሰራ የነበረው ስራ ፅድቅ ያለበት አለመሆኑን ምንም በማያስታውስ ወና ጭንቅላቴ እንኳን መገመት ከባድ አልነበረም። ሴትን ልጅ ራቁት እያስጨፈሩ ገንዘብ ማግኘት ግን ሌላ ደረጃ ብልግና መሰለኝ። ከዳዊት ጋር ቀን የሄድኩኝ እለት ያየሁት …… ቤቱ ውስጥ የነበሩት የተለያዩ ክፍሎች…….. ክፍሎቹ ውስጥ የነበሩት ሶፋው መሃል የተንጣለሉት አልጋ የመሰሉ መሃከላቸው ላይ የቆመ ብረት ያለባቸው ሰፊ ክብ መድረኮች ……. መድረክ ነገሩ ላይ አለመልበስ ለብሳ እንቅልፍ ወስዷት የነበረችው በጡት ማስያዣ እና በፓንት የነበረችው ቆንጅዬ ልጅ ……. አንድ በአንድ ከነገረኝ ጋር ላዛምድ ሞከርኩ። ልጅቷ ስታየኝ እየተደነባበረች  «አሁኑኑ ተጣጥቤ ፏ እላለሁ! ይቅርታ»  ብላኝ የነበረው ይሄን ልትሰራ ነበር? እሷው ልጅ ትሆን እንዴ እህቱ?

ጭንቅላቴ ውስጥ የሚተረማመሱትን ጥያቄዎች ሁሉ መጠየቅ ቢያምረኝም የሰውየው ሁኔታ ለመጠየቅ የሚጋብዝ አይደለም። ተገድዶ ቆመ እንጂ በጣም እንደሚጠላኝ ያስታውቃል።

«አሁን ላይ ሆኜ ……ምን አድርጌ እንደነበር ወይም ለምን እንዳደረግኩ የማውቀው ነገር የለም። ምንም ይሁን ብቻ እህትህንም አንተንም ስለበደልኳችሁ ነገር በጣም ይቅርታ! ባለፈው ህይወቴ በጣም ክፉ፣ እግዜአብሄርን የማልፈራ ጨካኝ ፣ ሀጢያትንም ወንጀልንም የምደፍር ሴት እንደነበርኩ ቀስ በቀስ እያወቅኩ ነው። የእኔ ዛሬ ሌላ ሴት መሆን ወይም ምንም አለማስታወስ የደረሰብህን በደል እንደማይሽረው አውቃለሁ። በቃ ግን በጣም ይቅርታ አድርግልኝ ከማለት ውጪ ማድረግ የምችለው የለም።» አልኩት ከልቤ። ምንም እንዳልተዋጠለት ያስታውቃል። <አሁንስ መሄድ እችላለሁ?> በሚል አስተያየት ጎንጥን አየው። የጎንጥን ፈቃድ በምልክት ሲያገኝ ወጥቶ ሄደ።
2.4K viewsDAVE / PAPI, 05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-25 04:37:26 ፓብሎ ኢስኮባር- ቱጃሩ የናርኮቲክ ወንጀለኛ
----
ጸሐፊ: አፈንዲ ሙተቂ
----
ፓብሎ ኢስኮባር ማለት በአንድ ዘመን በCIA በጥብቅ ሲፈለግ የነበረ ቱጃር ነው። በዜግነቱ ኮሎምቢያዊ ነበር። ይህ ሰው በዓለም ታሪክ የሚታወቀው ትልቁ የአደንዛዥ እጽ አምራችና አከፋፋይ ድርጅት የሆነው Medellin Cartel መስራችና ባለቤት በመሆኑ ነው። በዚህ ድርጅት አማካኝነት በየወሩ እስከ ሰማኒያ ቶን የሚደርስ የኮኬን እጽ ወደ አሜሪካ ያስገባ ነበር። ይህ መጠን በሂደት እየጨመረ ሄዶ በ1980ዎቹ መጨረሻ ላይ ድርጅቱ በየቀኑ 15 ቶን ኮኬን ወደ አሜሪካ መላክ ጀምሯል።

ታዲያ ይህ ትልቅ መጠን ያለው እጽ ወደ አሜሪካ ይገባ የነበረው እጅግ በተደራጀ የኮንትሮባንድ መስመር እና የትራንስፖርት ቻናል ነው። ኢስኮባር ከዚህ ንግድ እጅግ ብዙ ሀብት መሰብሰብ ችሏል። ድርጅቱም በዓለም ዙሪያ ከሚመረተውና ከሚሸጠው ኮኬይን የሰማኒያ በመቶ ድርሻ ነበረው።

ኢስኮባር የተሰማራበት የኮኬን ኤክስፖርት በዓለም ታሪክ እጅግ ሀብታሙ ወንጀለኛ እንዲሆን አስችሎታል። ኢስኮባር በ1993 በተገደለበት ወቅት የተጣራ ሀብቱ ከሰላሳ ቢሊዮን ዶላር በላይ ደርሶ ነበር።
----
ኢስኮባር ንግዱን ሲያካሄድ መንገዱ አልጋ በአልጋ አልነበረም። ከእርሱ ጋር ከሚወዳደሩ የኮኬን ነጋዴዎች፣ ከፖሊሶች፣ ከወንጀል መርማሪዎችና ከድንበር ጠባቂዎች ጋር ብዙ ህይወት የጠፋበት ውጊያ ውስጥ ገብቷል። በዚህም የተነሳ በሀገሩ በኮሎምቢያ እና በአሜሪካ መንግሥት በጥብቅ ይፈለግ ነበር። የአሜሪካው CIA ሊገድለው ብዙ ሙከራ አድርጓል።

ኢስኮባር በ1991 ከኮሎምቢያ መንግሥት ጋር የገባበትን ውዝግብ ለመፍታት ሲል ድርድር ጀመረ። በድርድሩም "ለአሜሪካ መንግሥት አሳልፋችሁ ካልሰጣችሁኝና ራሴ በሰራሁት እስር ቤት እንድታሰር ከፈቀዳችሁልኝ እጄን እሰጣለሁ" በማለት አስታወቀ። የኮሎምቢያ መንግሥትም በዚህ ተስማምቶ ለፍርድ አቀረበው። ፍርድ ቤቱም የአምስት አመት እስራት ፈረደበት። ኢስኮባርም La Chatedral ብሎ በሰየመው የግል እስር ቤቱ የወህኒ ጊዜውን ጀመረ።

ከአንድ ዓመት በኋላ የኮሎምቢያ መንግሥት ወደ መደበኛ እስር ቤት ሊወስደው ሲሞክር ግን ኢስኮባር ሊያስሩት የመጡትን ፖሊሶች ገድሎ አመለጠ። የኮሎምቢያ መንግሥት እና የአሜሪካው CIA በቅንጅት ያሳድዱት ጀመር። ከአስራ ስድስት ወራት ፍለጋ በኋላም ለብዙ ዓመታት በነገሰባት የሜዴሊን ከተማ በተደበቀበት አንድ አነስተኛ ፎቅ ቤት ውስጥ ተገደለ።
----
ፓብሎ ኢስኮባር የ'"ናርኮ-ቴሬሪስት" ወንጀለኛ ተብሎ በብዙ የዓለም ሀገራት መፈረጁ እውነት ነው። ይህ እንደተጠበቀ ሆኖ ግን ሰውዬው በሁለት ነገሮች ዘወትር ይታወሳል።

የመጀመሪያው ፓብሎ ኢስኮባር በቤቱ ውስጥ የኖረበት ምቾት በብዙ ሀገራት ቤተ መንግሥታት እንኳ የሌለ መሆኑ ነው። ኢስኮባር በሰፊው ግቢ ውስጥ ከገነባቸው ታላላቅ ቪላዎች በተጨማሪ በርካታ እንስሳት ያሉት የግሉ Zoo ነበረው። በተለይም በግቢው ውስጥ ብዙ ጉማሬዎች ያሉት መለስተኛ ሐይቅ ይገኝ ነበር።

በሌላ በኩል ፓብሎ ኢስኮባር በከተማዋ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ ድሆችን ሕይወት ለመቀየር የSocial Service ፕሮጀክት መዘርጋቱ ተመዝግቧል። በዚህ ፕሮጀክት አማካኝነትም ለብዙ ድሆች የመኖሪያ ቤቶችን አሰርቷል። ልጆቻቸው የሚማሩበትንም ትምህርት ቤት ከፍቶላቸዋል። በዚህም የተነሳ በ1982 የከተማዋ ህዝብ የፓርላማ አባል እንዲሆን መርጦት ነበር። ከከተማዋ ድሆች መካከል አንዳንዶቹ እስከ ዛሬ ድረስ "ፓብሎ ቅዱስ ሰው ነበር" ይሉታል።

ከዚህ በተጨማሪም ፓብሎ ኢስኮባር Atheltico Nacional የተሰኘውን የሜድሊን ከተማ ታዋቂ የእግር ኳስ ቡድን በገንዘቡ ይደግፍ ነበር። ይህ ቡድን በ1989 የላቲን አሜሪካ ክለቦች ዋንጫ (Copa Libertadors) አሸናፊ ለመሆን የበቃ ነው።
-----
አፈንዲ ሙተቂ
ጥቅምት 13/2013 ተጻፈ።

@wegoch
@wegoch
@paappii
3.0K viewsDAVE / PAPI, 01:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 21:29:22 በአንድ አፍታ በእጄ የያዘኝን እጁን አጥብቄ ስይዘው እና ዓይኖቼ የበለዘ አይኑን ሲያዩ እኩል ሆነ... አጥብቄ ያያዝኩት እጄ ህመም እንደሰጠው ፊቱ ላይ ስቃዩ ታየ:: እያየሁት እንደሆነ ሲያስተውል ህመሙን ለመዋጥ ታገለ:: እጁን ስቤ አየሁት:: እንደማበጥም እንደመቁሰልም ብሏል::

"አምላክ ሆይ!! ምን ሆነህ ነው?" ብዬ ጮህኩ:: እሱ ከአፉ ቃል ሳይወጣ የሆነው ነገር ከእኔ ጋር የተያያዘ እንደሆነ ገባኝ::

"ምንም አልሆንኩ! እንዲያው ዝም ብሎ ነገር ነው!" ይለኛል ደጋግሜም ብጠይቀው:: ቅስስስ ብዬ ተነስቼ እየተቀመጥኩ አገጬን በእጆቼ ወደራሴ እያዞርኩ ፊቱን አየሁት....

"እሺ የተፈጠረውን አትንገረኝ!! ተጎድተሃል?? ሌላ ቦታ ተመትተሃል?"

"ምንም አይደልኮ ትንሽ ነገር ነው!" ይበለኝ እንጂ ትልቅ ነገር እንደሆነ ሆዴ ነግሮኛል:: የዛን ቀን ከሰዓታት በኃላ ያላሰብኩት እንግዳ ጎበኘኝ..... ማንነቱ የገባኝ ከደቂቃዎች በኃላ ነው:: ... የዛን ምሽት ከደበደቡኝ ውስጥ አንዱ ነው:: ..... ጎንጥ አጠገቤ ቆሞ እንኳን ፍርሃት ልቤን ከደረቴ ጎትቶ ሊያስወጣት ታገለኝ:: ... ሳይታወቀኝ አይኔን ከድኜ እግሬን ሰብስቤ ጉልበቴን አቅፌ ጥቅልል አልኩ:: ....


        .......... ይቀጥላል........

@wegoch
@wegoch
@paappii
2.8K viewsDAVE / PAPI, 18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-24 21:29:22 #የመኖር አጋማሽ ..የመ: ሞ : ት ሲሶ ... መንገድ መሃል ..... (ክፍል ስምንት)
(ሜሪ ፈለቀ)

'ማናችሁ? ምን ፈለጋችሁ?' ከማለቴ በፊት ከታክሲው ኃላ መቀመጫ ጎትተው አስወጥተው ያበጥሩኝ ጀመር:: .... 'ምን አድርጌያችሁ ነው?' ማለት አፌ ይፈልጋል... በየትኛው ትንፋሽ?... እንኳን የማወራበት... የምተነፍስበት ፋታ ሳይሰጡ ተቀባበሉኝ.... ባለታክሲው ሁለት ቡጢውን ሲያጣጥም መፍጨርጨሩንም ተወው:: ... ሶስተኛ ሲሰልሱት እንዲተውኝ መለመኑንም ተወው! መሬቱ ላይ ወድቄ 'እንካ በእርግጫ' ተባባሉብኝ.... የምቱ ቁጥር ሲጨምር የህመሙ መጠን ቀነሰ... ሰውነቴ የደነዘዘ መሰለኝ.... አንደኛው በጫማው ደሬቴን ሲለኝ... ቁስሌ የተቀደደ አይነት ስሜት ተሰማኝ... ሳያስፈቅደኝ ልቤ ክድት ... ጭልጥ ይልብኝ እና ምቱ ያነቃኛል.... በስልምልምታ ከሩቅ እየቀረበ የመጣ የመኪና ድምፅ እና መብራት የተፈራረቁብኝ ይመስለኛል::..... የሚደልቁኝ ጫማዎች በፍጥነት ጥለውኝ ሲሄዱ ነገር.... ... ልቤ ቅልጥ ብሎ ጥፍት አለብኝ....

የሆነ በርቀት ነገር "እትይ! እትይ!" ... የሚል ጥሪ ይሰማኛል:: ... አይኖቼን ልገልጥ ስሞክር የአይኖቼ ቆቦች ህመማቸው ያሰቃየኛል:: ... ያልታመመ የሰውነት አካል የለኝም:: ... ሀኪም ቤት ተኝቻለሁ::.... ጎንጥ የአልጋዬን ጠርዝ ይዞራል:: ያልተጠቀለለ የሰውነት አካል የለኝም::.... አይኔን መግለጤን ሲያይ

"እትይ ነቁ? ክብር ምስጋና ይግባህ አምላከ ስላሴ!" ብሎ ወደ ሰማይ አየ.... ፊቴ ላይ ሳይቀር በፋሻ ተጠቅልያለሁ!.... እንባዬ ሲወርድ ወደ ጆሮዬ እየሄደ የሚያልፍበት ቆዳ ሁሉ አልኮል እንደተደፋበት ቁስል ያቃጥለኛል::... አንገቴ ቀስሮ በሚይዝ መደገፊያ ተደግፎ ስለታሰረ አይኔን እንጂ አንገቴን ማዞር አልችልም:: አፌን ላንቀሳቅስ ብሞክር የተሰነጠቀ ከንፈሬ ስቃይ ውስጥ ይጥደኛል::...

"እትይ! ግድ የለም እነዚህን ሽንታሞች አገኛቸዋለሁ!!" ይለኛል ጎንጥ እሳት በሚተፋ የንዴት እና የእልህ ትንፋሽ .... በቁጭት አንዱን እጁን በቡጢ ጨብጦ ሌላኛውን ይመታል::

በጥይት ተመትቼ ስነቃ እንዲህ በህመም አልተሰቃየሁም ነበር::.... ተኛኜ እና ጎንጥ እየተፈራረቁ እያስታመሙኝ ሆስፒታል ከረምኩ::.... ከሳምንታት በኃላ የተሰበረ አፍንጫዬ አገገመ.... የተሰነጠቀ ከንፈሬ ቁስል ሻረ... የተሰባበሩት የጎድን አጥንቶቼ ተደጋገፋ... የበለዙ ስጋዎቼ ፈዘዙ..... አንገቴ ያለ ድጋፍ ዞረ.... የዞረ ክንዴ ቦታው ሰገበ... ወደ አንጀቴ የፈሰሰ ደሜ ተቀዳ..... የተቀደደ ቁስሌ ተሰፋ......

"ተሻለሽ?" ሲሉኝ .... "ደህና ነኝ!" እላለሁ! ... የጠየቁኝ የስጋ ቁስሌን እንደሆነ ስለማውቅ...

እኔ ግን አልተሻለኝም!! ደህና አይደለሁም!! ጭራሽ ለደህና የቀረበ ነገር አይደለሁም!! ... ጎንጥ አጠገቤ ሆኖ እጄን ካልያዘኝ እንቅልፍ የማይወስደኝ ፈሪ ሆኛለሁ:: ኮሽ ባለ ቁጥር ከአልጋዬ የማልዘለው እሱ እየጠበቀኝ እንደሆነ ሳውቅ ብቻ ነው:: .... ካለበለዚያ ኮቴ ያስደነግጠኛል:: .... የትንኝ ጥዝታታታ እንኳን ጩሂ ጩሂ ይለኛል:: መጠየቅም መመለስም ተውኩ:: መሞትም መኖርም ፈራሁ!! ... ተናኜ አብራኝ ስትውል.... የቆጥ የባጡን ስትለፈክፍ አልመልስ ስላት!!

"ኸረ እትይ በማርያም እንዲህ አይሁኑ!" ትለኛለች:: ጭንቅ ጥብብ ሲላት ደግሞ
"እትይ? ካልሆነ እብስ ብለው ለምን የሆነ ሀገር አይሄዱም?" ትለኛለች::
"እትይ? እስኪ ትንሽ ነገር ደግሞ ይቅመሱ በማርያም?"

..... አግጯን ደገፍ ታደርግና "ምፅ!" ብላ እንባዋን ትለቀዋለች:: ...

"ምን ልሁን ነው የምትይ?" ይላታል ጎንጥ ማልቀሷን ሲያውቅ:: ....

የዛን ቀን ሹፌሩ የመኪና ታርጋቸውን መዝግቦ ስለነበር ለፖሊስ መረጃ ብንሰጥም ፖሊሶቹ የእኔ ጉዳይ ግድ የሚሰጣቸው አልመሰሉም:: ጎንጥ ብስጭት ብሎ

"በነጋ በጠባ 'ያላሰለሰ ጥረት እያደረግን ነው! ' ይሉኛል:: ጠብ የሚል ነገር የለም! እንዴት ያለ ህግ ነው?" አለኝ የሆነ ቀን.... አልመለስኩለትም!! .... ቀን ቀን ተናኜ ትውልልኛለች:: ማታ ማታ እሱ ያድራል:: ... ዳዊት አንድ ሁለቴ ሊጠይቀኝ መጥቶ ነበር:: እንዳይመጣ ስለነገርኩት ቀረ!! ....

"እትይ ? ዛሬ ጎንጥ ስለማይመጣ ምሽቱንም እኔ ነኝ የማስተዳድሮት.... እቤት ደረስ ብዬ እራት አበሳስዬ ላምጣ?" አለች በጨነቀው ልምምጥ....

"ለምንድነው ጎንጥ የማይመጣው? " አልኩኝ የወላለቀ ሰውነቴን እየጎተትኩ ተቀምጬ

"አላውቅም እትይ!! የምፈጣጥመው ነገር አለኝ ! ነው ያለው!"

"እሺ ትተሽኝ አትሂጂ.... ከካፍቴሪያ የሆነ ነገር ግዢ" ብያት (የሆስፒታሉ ጊቢ ውስጥ ያለ ካፍቴሪያ ነው) እሷ ልታመጣ ስትሄድ ከፋኝ!! እንደህፃን ልጅ አለቀስኩ:: .... ሆስፒታል ማደር ደክሞት ይሆን??? እኔን መጠበቅ ከነአካቴው ደክሞት ይሆን?? ጠልቶኝ ይሆን?? .... ላይመለስ ትቶኝ ቢሄድ ምንድነው የምሆነው?? ከእርሱና ከተናኜ ውጪ ማንንም እንደማላውቅ እያወቀ ትቶኝ ይሄድ ይሆን?? ይቅር ይበለኝ እና ብር አምጣ ብዬ ከካዝናው ውስጥ ያወጣሁት ብር የት እንዳለ ነግሬዋለሁኮ .... ብሩን ይዞ እኔን ትቶኝ ሄዶ ቢሆንስ? እኔ በወር የምከፍለውን ደመወዝ ከ20 ዓመት በላይ የሚከፍለው ብር ነው..... በስመአብ !! ኸረ እንደሱ አያደርግም!!!

ለሊቱ እንቅልፍ በአይኔ ሳይዞር ነጋ!! ተናኜ ሳለቅስ ካየችኝ ከእኔ ብሳ ታርፈዋለች:: አልጋዬ ስር ፍራሿን ዘርግታ እንቅልፍ እስኪወስዳት ጠብቄ ..... ብዙ አልቅሼ እንባዬ ሁላ ያለቀ መሰለኝ!! ፍርሃት ሆዴን አላወሰው!!! የበር ድምፅ በሰማሁ ቁጥር ልቤ ይርዳል:: ሰውነቴ ይንቀጠቀጣል::....  ነግቶ ብርሃን ሲሆን እንቅልፍ ጣለኝ:: .... ብርሃን ከክፋት የሚጠብቀኝ ይመስል ሲፈካ ልቤ ይረጋጋል:: ከእንቅልፌ ስነቃ አይኔን ሳልገልጥ በፊት እጄን የያዘኝን እጅ ጨበጥኩ.... አይኖቼን ስገልጣቸው ጎንጥ ለሊት ሲያድር እንደሚያደርገው ወንበር ላይ ተቀምጦ እጄን ይዞኝ ... አንገቱን አልጋው ላይ ደፍቶ ተኝቷል::  .... ደስታ ይሁን መከፋት የማላውቀው ስሜት ናጠኝ::: ህቅታዬ እንዳይረብሸው እየታገልኩ ተንሰቀሰቅኩ:: ... ከደቂቃዎች በኃላ ግን ልያዘውም ብል ፈንቅሎኝ የወጣ ህቅታዬ ቀሰቀሰው.... እንደነቃ ሳየው ይብስ ድምፅ አውጥቼ ማልቀስ ጀመርኩ:: ....

"መድሃንያለም! እትይ? ምን ሆነው ነው?? ኸረ በመድሃንያለም ነፍስያዬን አያስጨንቋት?? " የሚያደርገው ግር ብሎት እጄን ባልጨበጠ እጁ እንባዬን ሊጠርግ ይታገላል::

"የሄ.... ድክ ... መስሎኝ..." ብዬ መጨረስ አቃተኝ:: ህቅ ማለት ቀጠልኩ:: ክፉ ነገር እንደነገርኩት ሁሉ ... ዝግንን ብሎት እጄን እንደጨበጠ ከተቀመጠበት እየተነሳ

"መሄድ ሲሉ?? መሄድ ! መሄድ!? ... ይቅር ይበሎት! ምኑን አሰቡት? እንዲህ ያለ ሁኔታ ላይ እንዴት ትቼዎት እሄዳለሁ?? እንዴት ያለ ሰው ነው ብለው ነው የሚያስቡኝ?" አለ ቁጣም በቀላቀለው አነጋገር!!

"ይቅርታ አድርግልኝ!! እኔ አላውቅም!! ምን እንደማስብ... ግራ የገባኝ ሰው ነኝ! ካንተ እና ከተናኜ ውጪ ማን ምን እንደሆነ እንኳን አላውቅም!! አንተ ብትሄድ..." ብዬ መጨረስ ቸገረኝ:: ተመልሶ እየተቀመጠ በሚለማመጥ ድምፅ

"የትም አልሄድም! እርሶ አልፈልግህም ብለው እስካላበረሩኝ ድረስ እኔ የትም አልሄድም!!" አለኝ:: ...
3.0K viewsDAVE / PAPI, 18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 21:29:54 ባለትዳሮች ደግሞ እስኪ አዳዲስ ጅንጀና ፍጠሩ...

እንዴ ሁሌ አንድ አይነት ያለፈበት ነገር ቸከሶቹም ይደብራቸውል እኮ!

“ይሄ በትዳሬ ደስተኛ አይደለሁም”፣ “አልጋ ከለየን ቆየን”፣ “ሶፋ ላይ ነው ማድረው”፣ “ለልጆቹ ብለን ነው አብረን ያለነው”፣ “በትክክል ካወራን እራሱ ረጅም ግዜ ሆኖናል”፣ “”ምግብ እንኳን አንድ ላይ ከበላን ቆይተናል”... ምናምን ዝብዘባ ኸረ ላሽ እንዲ ብላችሁ እኮ ብትፋቱ አሪፍ ነበር በስንተኛው ወር መንታ ልጅ ትወልዳላችሁ እኮ ደሞ!

እስኪ አዲስ የተጣላችሁበትን ምክንያት ፍጠሩ እስኪ ላይክ...

ወንዶቹ..

ቅልጥም በልታ መጣ ከዛ በዘነዘና ሰብራ ትበላለች

ስስማት እንጥሏ ይዋጋል

ጉልበቷ እያደር መጥቆር አመጣ

ቅቤ ተቀብታ በስስ ፌስታል አስራ ማደር ጀመረች

የብብቷን ፀጉር ማሳደግ ጀመረች

ፓንቷን በሶስት ቀን ነው የምትቀይረው

ሁሌ ሽንት ቤት ገብታ ፍላሽ ሳታደርግ ትረሳዋለች

ሴቶች ደግሞ...

ስኪኒ ሱሪ መልበስ ጀመረ

መጠጥ መጠጣት አቆመ

አፍንጫውን ይጎሮጉራል

ሲቀመጥ የቂጡ ፍንክት ይታያል

ሁለት ካልሲ ብቻ ነው ያለው

አፉ ጥግ ጥግ ላይ ነጭ ነገር ማውጣት ጀመረ

የሆነ ነገር በወደቀ ቁጥር "እሜ ድረሽ!" እያለ ከወንድ ልጅ የማይጠበቅ ቀጭን ድምፅ ያወጥል...

ምናምን የሚሉ የማያስሟሟችሁን ምክንያቶች ደርድሩ እንጂ!

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Habtish doi yilma
4.7K viewsDAVE / PAPI, 18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-20 19:03:33 "አንች ጀጤነሽ" አለችኝ።
"አቤት"
"እንደው በጣድቁ ...አደራሽን በጣድቁ እንዳታሳፍሪኝ!"
"ምንድነው አያቴ?"
"ንጡህ ነሽ አይደል?"
"ማለት?"
"የሚል አላት ብያለሁኮ እችን ተንከሲስ!ንጡህ ነሽ ድንግል ነሽ ወይ ነውኮ 'ምልሽ" አቀርቅሬ ዝም አልኩኝ።ለሰከንዶች ምላሼን ስትጠብቅ ቆይታ ተስፋ ስትቆርጥ

"በይ'ንጂ ንገሪኝ ...አየ!አየ!አየ ለፍቶ መና አስበላሽው? ጀጤነሽ አስበላሽው?ያን የመሰለ ዳቦ አስበላሽው?ሀይ!ሀይ!ሀይ!ሀይ!ሀይ!"አለችና ወደሽማግሌዎቹ ሄደች።እኔም ባቀረቀርኩበት ቆየሁ።ከዚያ በላይ የተነጋገሩበትን የምሰማበት ድፍረት አልነበረኝም።

ማዕዶት ያየሕ

@wegoch
@wegoch
@paappii
4.0K viewsDAVE / PAPI, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ