Get Mystery Box with random crypto!

TRUTH

የቴሌግራም ቻናል አርማ tquset — TRUTH T
የቴሌግራም ቻናል አርማ tquset — TRUTH
የሰርጥ አድራሻ: @tquset
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 305
የሰርጥ መግለጫ

Media

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-08 13:08:00
77 viewsTurth Quset, 10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-08 12:20:40
የጃፓኑ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በተፈጸመባቸው ጥቃት ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ!!

የቀድሞ የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ በናራ ከተማ በዕጩ ቅስቀሳ ወቅት ከኋላቸው በጥይት ተመተው ሆስፒታል መግባታቸውን ዘገባው አስታውሷል፡፡

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በሆስፒታል ጥብቅ የህክምና ክትትል ሲደግላቸው ቢቆይም ህይወታቸው ሊተርፍ እንዳልቻለ ተነግሯል፡፡

ጥቃቱን በማድረስ የተጠረጠረው ግለሰብም ከእነ መሳሪያው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል።

የ67 አመቱ ሺንዞ አቤ ጃፓንን ከ2012 እስከ 2020 ድረስ በነበሩት ስምንት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትርነት መምራታቸው አይዘነጋም።

ሺንዞ አቤ ከጤና እክል ጋር በተያያዘ በፈረንጆቹ 2020 ላይ በገዛ ፍቃዳቸው ከስልጣን መልቀቃቸው ይታወሳል፡፡

https://t.me/Tquset
82 viewsTurth Quset, edited  09:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 19:49:35
የአስፓልት መንገዶች የታረሱ እስኪመስል ድረስ ለብልሽት እየተዳረጉ ነው፡፡ (ከሀረር እስከ ደገጎ)
የሚባክነው የሀገር ሀብት ነው፡፡
104 viewsyibeltal Gizaw, 16:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 15:13:26 በኢትዮጵያ ከሚገኙ 13 መድሃኒት ፋብሪካዎች ሶስቱ ስራ ማቆማቸው ተነገረ!

በኢትዮጵያ ካሉት አስራ ሶስት መድሃኒት እና የህክምና መገልገያ መሳሪያ ፋበሪካዎች ውስጥ ሶስቱ በውጪ ምንዛሬ እጥረት ምክንያት ስራ ማቆማቸው ተገልጿል፡፡ ፋብሪካዎች በምስራቅ አፍሪካ ትልቅ የሚባሉ እና መሰረታዊ የነፍስ አድን መድሃኒቶችን የሚያመርቱ ፋብሪካዎች ሲሆኑ ሰራተኞቹ ሙሉ ለሙሉ ስራ ማቆማቸውን የኢትዮጵያ መድኃኒት አምራቾች እና የህክምና መገልገያ ፋብሪካዎች ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ዳንኤል ዋቅቶሌ በተለይም ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ፡፡

ፋብሪካዎች በቢሾፍቱ ከተማ የሚገኙት ሳንሸንግ ፣ ካዲላ ፣ ሰሚድ ሲሆኑ ሙሉ ለሙሉ ስራ ያቆሙት ፋብሪካዎቹ የማሽን ፣የሰው ሃይል እንዲሁም የተሞላ ሰራተኛ ያሏቸዉ ሲሆን ፋብሪካው እንዲዘጋ ብቸኛ ምክንያት የሆነው የውጭ ምንዛሬ እጥረት መሆኑም ተገልጿል፡፡

አያይዘውም አቶ ዳንኤል ዋቅቶሌ እንደገጹት መድሃኒቶችን በውጪ ምንዛሬ ምክንያት በሚፈለገው መጠን ከውጪ ማስገባትም ሆነ ማምረትም አለመቻሉን ለሚመለከተው አካል ያሳወቅን ቢሆንም እስካሁን ምንም አይነት መልስ ማግኘት አለመቻላቸውን ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል ፡፡

Via Bisrat FM
153 viewsTurth Quset, 12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 15:13:22
118 viewsTurth Quset, 12:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 17:19:16 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት 114 ባለሀብቶች ጠፍተዋል አለ!

በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል 114 የፕሮጀክት ባለቤቶች መጥፋታቸውን ተከትሎ ከ100 ሚሊዮን ብር በላይ ግብር ማጣቱን የክልሉ መንግሥት የገጠር መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመንት ቢሮ ለአዲስ ማለዳ አስታወቀ።

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልላዊ መንግሥት የገጠር መሬት አስተዳደር እና ኢንቨስትመት ቢሮ ኃላፊ አመንቴ ገሽ ለአዲስ ማለዳ እንደገለጹት፣ በክልሉ በእርሻ፣ በማዕድን እና በሌሎች ኢንቨስትመንቶች ከዘጠኝ መቶ በላይ ፕሮጀክቶች በሥራ ላይ ይገኛሉ።

ከእነዚህ መካከል ከ2010 ጀምሮ እስከ 2014 ባለው ጊዜ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኹለት ቢሊዮን ብር በላይ ብድር በመውሰድ ወደ ሥራ ገብተው የነበሩ 114 የኘሮጀክት ባለቤቶች ጠፍተዋል። ለዚህም ዋናው ምክንያት በክልሉ በነበረው የጸጥታ ችግር ምክንያት መሥራት አልቻልንም በማለት እና በፍላጎታቸው ሥራ አቁመው መጥፋታቸውን ኃላፊው ጠቁመዋል።
114 viewsTurth Quset, 14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 08:48:39
ታዋቂው የትግረኛ ሙዚቃ አቀንቃኝ ዳዊት ነጋ ህይወቱ አለፈ።

ዘዊደሮ በሚለውና በሌሎች የትግረኛ ሙዚቃዎቹ የሚታወቀው ድምፃዊ ዳዊት ነጋ በትናንትናዉ እለት ህይወቱ ማለፍን ኢትዮ ኤፍ ኤም ከቤተሰቦቹ ቦታው ድረስ ተገኝቶ አረጋግጧል።

ለቤተሰቦቹ፣ለወዳጅ ዘመዶቹና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን እንመኛለን፡፡
92 viewsTurth Quset, 05:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 07:22:35
125 viewsTurth Quset, 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-06 07:22:35
ሩሲያ ከአውሮፓ ህብረት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟን ገለፀች

ሩሲያ ከሰሞኑ ከአውሮፓ ሀገራት ለዩክሬን የተለገሱ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን ማውደሟን የሀገሪቱ ዜና ወኪል ታስ ዘግቧል።

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሜሪካ እና ሌሎች ምዕራባዊያን ሀገራት ለዩክሬን የጦር መሳሪያ እንዳይለግሱ አሳስበው ልገሳቸውን ከቀጠሉ ግን እርምጃ መውሰዴን እንደሚቀጥሉ አስጠንቅቀዋል።

በተለይም ምእራባዊያን ሀገራት ረጅም ርቀት ተወንጫፍ ሚሳኤሎችን እንዳይለግሱ የተናገሩት ፕሬዝዳንት ፑቲን ሩሲያ ደህንነቷን ለመጠበቅ ስትል እርምጃ ትወስዳለች ብለዋል።

አሜሪካ፣ ስፔን እና ሌሎች የአውሮፓ ህብረት አባል ሀገራት ለዩክሬን ሚሳኤሎች እና ሌሎች የጦር መሳሪያዎችን ለግሰዋል ተብሏል።
እንደ ሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር መግለጫ ከሆነ ምዕራባዊያን ለዩክሬን የጦር መሳሪያ በመለገስ ጦርነቱን የማራዘም እቅድ እንዳላቸው ተገልጿል።

Via Alain
92 viewsTurth Quset, 04:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-23 08:12:55 በደቡብ ሱዳን በአንዲት ሴት ግድያ ጥፋተኛ የተባለዉ በግ በሶስት ዓመት እስር እንዲቀጣ ተወስል

በደቡብ ሱዳን በአንዲት አዛዉንት ደረት ላይ ተደጋጋሚ ጥቃት በመፈጸም ለሞት ዳርጓል የተባለዉ በግ በሶስት አመት እስር እንዲቀጣ መወሰኑን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።የበጉ ባለቤትም ለተጎጂው ቤተሰብ አምስት ላሞችን እንዲከፍል በደቡብ ሱዳን ሩምቤክ ከተማ የሚገኘው የአካባቢው ፍርድ ቤት ብይን ሰጥቷል።

ሱዳን ቱዴይ ጋዜጣ እንደዘገበው በደቡብ ሱዳን ሌክ ግዛት የሚገኘው የሩምቤክ ፖሊስ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ሴትየዋን የገደለዉን በግ በቁጥጥር ስር አውሏል። በጉ በሴቲቱ ላይ ጥቃት ሰንዝሮ ከመሞቷ በፊት ደረቷ ላይ ብዙ ጊዜ እንደመታት ተነግሯል።

በልማዳዊ ህግ ማንኛውም የቤት እንስሳ ሰውን የገደለ እንደሆነ ለሟች ቤተሰብ ካሳ ይከፈለዋል የሚል መመሪያ ቢኖርም የቤት እንስሳ በእስር መቀጣቱን አነጋጋሪ ሆኗል።
132 viewsTurth Quset, 05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ