Get Mystery Box with random crypto!

ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ ✝✝✝

የቴሌግራም ቻናል አርማ tinsae_ze_ethiopia — ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ ✝✝✝
የቴሌግራም ቻናል አርማ tinsae_ze_ethiopia — ትንሳዔ ዘኢትዮጵያ ✝✝✝
የሰርጥ አድራሻ: @tinsae_ze_ethiopia
ምድቦች: ሙዚቃ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.44K
የሰርጥ መግለጫ

📢 ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን እና ገዳማት ስርዓት ፣አሁናዊ ዜና እና ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን ፡ ቅዱሳን መካናት እና ገዳማት ታሪክ
📢 የቅዱሳን ገድላት
📢 ቅዱሳን አበው ሊቃውንት
📢 ህዝበ ክርስቲያንን ማንቃት
📢 ቅድመ ኢትዮጵያ ትንሳዔ እና የኢሉሚናቲ ኅቡእ ማኅበር ኢትዮጵያ ላይ የተሸረቡትን ሴራዎችን ማጋለጥ
ለውይይት
@Tinsae_ze_ethiopiaofficialgrp

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-09 00:02:24 በጾም ወራት ባለትዳሮች ከሩካቤ ስጋ |ግብረ-ስጋ ግንኙነት| እንዲታቀቡ ቤተክርስትያን የምትመክረው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ነውን
በጋብቻ ወስጥ ግብረ ስጋ ግኑኝነት በመጽሐፍ ቅዱስ እንዴት ይገለጻል

እንዲሁም በዚህ ታላቅ የፍልሰታ ፆም እና የማይደረግ ነገር ምንድን ነው
ምን እና እንዴት መፀለይ አለብን
በሱባኤ ጊዜ የሚጸለዩ ጸሎት

በነዚህ ትምህርቶች ዙርያ ከታች ባለው አድራሻ በመግባት መማር ትችላላቹ
በማርያም ይህን ቻናል ይቀላቀሉ

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 𝐉𝐎𝐈𝐍 𝐔𝐒 ➲   █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘
የይቱብ ቻናላችን


𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 ‌‌

ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ
በናታኒም ቲዩብ
በግሩም እና በተወዳጅ ዘማሪያን ይቀርባል ከታች
ባለው ሊንክ ሰብስክራቭ በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ።






18 viewsማኔ ቴቄል ፋሪስ, 21:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:46:08 ከዚህ በተጨማሪ ግሪኮች ፦
መፅሐፈ #ሶስናን
መዝሙረ #ዘሰለስቱ #ደቂቅን
#ተረፈ #ዳንኤልን ልክ እንደኛ ከትንቢተ ዳንኤል ጋር ጨምረው #ይቆጥራሉ ።

ይቀጥላል.........
ምንጭ:- ወንድም micah ayele

አቤል
528 viewsBereket, 06:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:46:08 የፕሮቴስታንቱ ቸርች የማይፈታው እንቆቅልሽ!

#መፅሐፍ #ቅዱስን ልዩ ከሚያረጉት ነገሮች መካከል አንዱ ዕድሜው ነው ከሱ ቀድሞ ወይም ከሱ በፊት የተፃፈ መፅሐፍ የለም የመጀመሪያው መፅሐፍ መፅሐፈ ሄኖክ ሲሆን የተፃፈውም ከአዳም ጀምሮ #ሰባተኛ #ትውልድ በሆነው በሄኖክ በ 1486 ዓመተ ዓለም ወይም ከክርስቶስ ልደት 4014 ዓመት በፊት ነው " #የአምላካችን #ቃል #ግን #ለዘላለም #ፀንታ #ትኖራለች " ት.ኢሳ 40 ፥ 8 እንደተባለ
መፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ የማይሽረው ዘመን የማይገታው የማያረጅ #ዘላለማዊ #ነው።

መፅሐፍ ቅዱስን #ከአርባ #ስምንት በላይ የሆኑ ጻሕፍት

እረኛ የነበሩ {ሙሴ ፣ አሞፅ }
ነገሥታት የነበሩ {ዳዊት ፣ ሰለሞን}
ካህን የነበሩ { ሕዝቅኤል }
ቀራጭ የነበሩ {ማቴዎስ }
ዓሳ አጥማጅ የነበሩ {ጴጥሮስ ፣ ዮሐንስ }
ሐኪም የነበሩ { ሉቃስ }
ከተለያየ የሥራ መስክ ተጠርተው ፤
በተለያየ ቦታ ማለትም ፦
በሲና ምድረ በዳ ፣
በኢየሩሳሌም ፣
በተለያዮ የእስራኤል ክፍሎች
በስደት አገር በባቢሎን ፣ በፋርስ ፣በሮም ከተማ ፣ በፍጥሞ ደሴት በወህኒ ቤት ሆነው በተለያዩ ዘመናት የጻፉት የቅዱሳት መጻሕፍት ስብስብ ቢሆንም መልዕክቱ ግን ያልተዛባ ርቱዕ {ቀጥተኛ} የሆነ #እርስ #በርሱ #የማይጋጭ #ነው #ምክንያቱም #በእግዚአብሔር #መንፈስ #እየተመሩ #ፅፈውታልና ። ለብዙዎች እንደሚመስላቸው ቅዱሳት መጻህፍት #በአንድ #ጊዜ #ተፅፈውና #ተጠርዘው #የተገኙ #ሳይሆኑ #ለየብቻቸው #በብራና እየተጻፉ #ተጠቅልለው #ይቀመጡ #ነበር "የነቢዮንም #የኢሳያስን #መፅሐፍ ሰጡት #መጽሐፋንም #በተረተረ #ጊዜ ..." ሉቃ 4 ፥ 17- 20 #እንደተባለ እንዲሁም #ቅዱስ #ጳውሎስ ጢሞቲዎስን " ስትመጣ በጢሮአዳ ከአክርጳ ዘንድ የተውሁትን በርኖሱንና #መጻሕፍቱን ይልቁንም #በብራና የተጻፋትን አምጣልኝ " እንዳለው 2ኛ. ጢሞ 4 ፥ 13 አብዛኛው የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት በዕብራይስጥ የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ደሞ በግሪክ ቋንቋ ተፅፈዋል ፤ በአዲስ ኪዳን ዘመንም እስከ 5ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መፅሐፍ ቅዱስ የተተረጎመባቸው ለመፅሐፍ ቅዱስ ነጠላ ትርጓሜ መሠረታውያን ( እንደ ሪፈራንስ ) የሚያገለግሉ ቋንቋዎች የሚባሉት ፦

#ግዕዝ (ኢትዬጵያ ) #ቮልጌት {ሮማይስጥ #የጥንቱ #ላቲን } #ኮብት {ግብፅ ቅብጥ} #ሱርስት { ሶሪያ }
#አርመንኛ { አርመን } #ናቸው በነዚህ #ቋንቋዎች #የተተረጎሙት መፅሐፍ ቅዱሳት በአሁኑ ጊዜ በጣም አስፈላጊ
ሆነዋል ምክንያቱም መፅሐፍ ቅዱስ የተጻፈባቸው መሠረታውያን ቋንቋዎች በመሆናቸው በየጊዜው ለሚነሱ ስህተቶች ማረሚያ ስለ ሆኑ ነው። ቅዱሳት መጻሕፍትን መሰብሰብ የተጀመረው የመጀመሪያው መፅሐፍ ከተጻፈበት ጊዜ ጀምሮ ሲሆን ብዛታቸውንና ዓይነታቸውን ለይቶ ለማወቅ ከፍተኛ ጥረት የተደረገው በአዲስ ኪዳን በመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን በሐዋርያት ነው ፤ ሐዋርያት አጠቃላይ ስለ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን 85 ቀኖናትን ደንግገዋል ከነዚህም ውስጥ 85ኛው ድንጋጌ (ቀኖና) #ስለ #ቅዱሳት #መጻሕፍት #የሚናገር #ነው፤ ከዚያም በ325 ዓም በኒቂያ በተካሄደ ጉባኤ ላይ እውነተኞቹን ቅዱሳት መጻሕፍት ለመሰብሰብ በተወሰነው መሠረት ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ በ367 ዓም እውነተኞቹን የቅዱሳት መጻሕፍትን ቁጥርና ዓይነት አስታውቋል እንዲሁም ፤ በ393 ፣ በ399 ፣ እና በ419 ዓም እ.ኤ.አ በሰሜን አፍሪካ (ካርቴጅ ) በተካሄደ ጉባኤ ቅዱሳት መጻሕፍት ተለይተው ታውቀዋል ከዚህም ጉባኤ በኃላ ቅዱሳት መጻሕፍት በአንድ መድብል ተጠርዘው " መፅሐፍ ቅዱስ " ለመባል #በቅተዋል ፤ ይህ መፅሐፍ ቅዱስ #ሰማንያ #አሐዱ ( 81 ) #ቅዱሳት #መጻሕፍትን #የያዘ #መድብል #ነው ነገር ግን ሰማንያ አሐዱ ተብሎ በታተመው መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሁሉም መፃሕፍት አልተካተቱም ምክንያቱም አንዳንዶቹ መጻሕፍት #በይዘታቸው #ትላልቅ #በመሆናቸው #ራሳቸውን #ችለው #እንዲቀመጡ #በመደረጉ #ነው።

#የኘሮቴስታንቱ #ዓለም #ግልፅ #ያልሆነለትና #ግራ #የተጋባው #ለመፅሐፍ #ቅዱስ #ታሪክ #ባዳ #ስለሆነ #ነው #ይኸውም #ያልተረዱት #ምንድን #ነው ? #ከተባለ #ከክርስቶስ ልደት 534 ዓመት በፊት ዕዝራና አብረውት የነበሩት ነቢያት ከባቢሎን ምርኮ ወደ ኢየሩሳሌም ተመልሰው #ጠፍተውና #ተቃጥለው #የነበሩትን #መፃሕፍት #ሲያሰባስቡ #በዕብራይስጥ የተፃፉትን #ብቻ #ነበር #ያሰባሰቡት ነገር ግን በሌላ ቋንቋ የተፃፉትን ቅዱሳት መፃህፍት ሳያሰባስቡ ቀርተዋል ለምሳሌ በ 1934 ዓ.አ {1947 እ.ኤ.አ} #በሙት #ባህር #አካባቢ #በቁምራን #ዋሻ ውስጥ #በዕብራይስጥ #ቋንቋቸው #የተፃፈው #መፅሐፈ_ሄኖክ #ተገኝቷል #ይሄ #የተገኝው #መፅሐፍ #በኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ #ቤተ #ክርስቲያን #ከሚገኘው #መፅሐፈ_ሄኖክ #ጋር #ተመሳክሮ #አንድ #ሆኖ #ተገኝቷል #በዚህም #ምክንያት #ዓለም #በእውነት #ኢትዮጵያ #የቅዱሳት #መፃህፍት #ማህደር #መሆኗን #ሳይወድ_በግድ #አምኖ #ተቀብሏል ፤ ይሄ የሚያሳየን በወቅቱ እነ ዕዝራ ሁሉንም ቅዱሳት መፃሕፍት ሰብስበው ለአይሁድ አለማስረከባቸውን ነው ፤ አይሁድ ለጊዜው እነዚህን ተጨማሪ መፃህፍት ከሌሎቹ መፃህፍትጋር አብረው ያልያዙአቸው ቢሆንም ከጊዜ በኃላ ግን ተገቢውን ክብር ሰተዋቸዋል ፤ አልተቀበሏቸውም ማለት ግን ፈፅሞ ስህተት ነው ምክንያቱም ከክርስቶስ ልደት 284 ዓመት በፊት #በበጥሊሞስ #ዘመነ መንግስት #ሰባው #ሊቃናት #መፅሐፍ #ቅዱስን #ከዕብራይስጥ #ወደ #ጽርዕ {ወደ ግሪክ} #ቋንቋ #የተረጎሙት #መፃሕፍት እነዚህን #ማጠቃለሉ #በቂ #ማስረጃ #ነው ፤ እነዚህ #ቅዱሳት #መፃሕፍት #በእናት #ቋንቋቸው #በዕብራይስጥ #ቋንቋ #ተፅፈው #ባያገኟቸው #ኖሮ #ከየት #አምጥተው #ይተረጉሙት #ነበር ? በ1959 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ግሪኮች ባሳተሙት መፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ደግሞ ፦

መፅሐፈ #ጦቢት መፅሐፈ #መቃብያን መፅሐፈ መቃብያን #ካለዕ መፅሐፈ መቃብያን ካለዕ * ዮሴፍ ወልደ ኮርዮን ( አራተኛ መፅሐፈ መቃብያካለዕ መመቃብያ ካለዕ መመቃብያካለዕ መፅሐፈ #ባሮክ #ይገኙበታል
331 viewsBereket, 06:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:42:34 Channel photo updated
06:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:39:41 የብልጽግና ወንጌል የመጨረሻ ክፍል።

➥ የብልጽና ወንጌል አብዮታዊ ዲሞክራሲን አንዴት ተካው?

ለሕወሓት የሥልጣን ዘመን ማብቃት ምክኒያት ስለሆኑ ሁኔታዎች የተለያዩ ዐሳቦች ቢሰነዘሩ ብዙም አይገርምም። ምክንያቱም ሕወሓት ከሥልጣን የወረደበት አንድ ሚሊዮን የተለያዩ ምክንያቶች ስላሉ። ነገር ግን ሕወሓት ኢሕአዴግ ውስጥ የነበረው የሀሳብ (የሥልጣን ወይም የጉልበት ማለት አደለም) የበላይነት እየተሸረሽረ የሄደው አቶ መለስን በሞት አቶ በረከትን ደግሞ በሕውሓት ሰወች ሥልጣናችን ይወስድብናል ፍርሃት ካጣ በኋላ ነው። ይህ በኢሕኣዴግ ውስጥ የነበረ የዐሳብ የበላይነት ማጣት መሬት ወርዶ ከተለያዩ በጣም ብዙ ውጫዊና ውስጣዊ ምክያቶች ጋር ተዳምሮ ወደ ሥልጣን ማጣት ተቀይሯል።

አብዮታዊ ዴሞክራሲ ጥርት ያለ መርህ ያለው ነገሮችን በግልጽ ለመተንትን የሚያስችል የተስናሰለና በአግባቡ የተሰነደ ርዕዮተ አለም ባይሆንም መምህሩ የነበሩት አቶ መለስና ደቀ መዝሙርቶቻችው እንደ ዳዊት የሚደግሟችው የተለያዩ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ዐሳቦች የያዘ ያላለቀ ነገር ግን ካድሬ ለማሠልጠን የሚይስችል ማንዋል ነበር ማለት ይቻለል። አብዮታዊ ዴሞክራሲ ማኅበራዊ መሠረት የሚለው መድብ (ገበሬው)ና ቡድኖች (ጭቁን ብሔሮች) እንደነበሩት ሁሉ ጠላት መደብና ጠላት ብሔር ማን እንደሆነ ለይቶ የሚያውቅ፤ ማኅበራዊ መሠረት የሚላቸው ቡድኖችን ጥቅም የሚያስከብር፤ ጠላቴ የሚለውን ብሔርና ሃይማኖት ደግሞ ሕልውና የሚያጠፋ ሕገ ምንግሥት፣ ፖሊሲ፣ አዋጅ፣ ደምብና መመሪያ የነበረው የፖለቲካ አስተሳሰብ ነው።

እነ አቶ መለስና አቶ በረከት ካድሬወቻቸውን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ በሚያጠምቁበት ዘመን ለሥልጣናችን አያሰጉነም እናምናቸዋለን ያሏቸውን እነ ፓስተር ባደግና ፓስተር ገመቺስ ቀን አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሲጋቱ የሚውሉትን የደኢሕዴንና የኦሕዴድ ባለሥልጣናትን ማታ የፕሮቴስታንት ቤተክርስትያን ውስጥ የብአዴን ካድሬወችን ደግሞ ኢንተርናሽናል ሊደርሽፕ ኢንስትዩት ውስጥ የብልጽግና ወንጌል፣ አውንታ ሃሳቢነት፣ አነቃቂ ንግግር፣ የብልጽግና ወንጌል ሥራ አመራር ጥበብ፣ ወዘተ ያስተምሩ ነበር።

አቶ መለስ ከሞቱ በኋላ የተለያዩ የጥቅም ኔትውርኮች እንደ አሽን ሲፈሉ የፓስተር ባደግና የፓስተር ገመቺስ የማታ ትምህርት ተማሪዎችም የራሳችውን ጠንካራ ኔትውርኮች #ከሕውሓት ኔትውርኮች በተጓዳኝ መስርተዋል። በሥልጣንና በገንዘብ ያበዱት የሕውሓት ባለሥልጣናትም እርስ በርስ በሚያድርጉት የዐሳብም ሆን የሥልጣን መገፋፋት ትግል ውስጥ እንደ አስፈላጊነቱ የፓስተር ባደግንና የፓስተር ገመቺስን ስዎች በዐሳብ አመንጪነት ደረጃ እንዲሳተፉ አድርገዋል። ይህ ተሳትፎ ከተላላኪነት ያለፈ ሚና ላልነበራቸው ስዎች የሞራል ስንቅ ሰጠ፤ የሕውሓት ስዎችን ኢሕአዴግ ውስጥ መሞገት እንደሚቻል አሳየ። ከጊዜ በኋላም የሀገሪቱ ጉዳይ ላይ የመወሰን የተሻለ ሚና ይገባናል ብሎ ደፈር ብሎ ወደ መጠየቅ እየተሽጋገረ ሂዷል።

በአማራ ክልልና ኦሮሚያ ውስጥ ባሉት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምክንያት ወጣቶች በማኅበራዊ ሚዲያ አንቂወች በመታገዝ አገዛዙን ሲቃወሙ ብአዴንና ኦሕዴድ ካድሬዎች እሳት ከማጥፋት ይልቅ አይዟችሁ እያሉ ነዳጅ ወደ ማቀበል ተሽጋገሩ። #የአብዮታዊ_ዲሞክራሲ አንዱ ትርክት ኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥር አብላጫ ያላቸው ሁለት ብሔሮች ግንኙነት "የጨቋኝና የተጨቋኝ ነው፤ እነዚህ ሁለት ቡድኖች ፍላጎቶቻቸው መቸም አይታረቁም፤ አብረው ሊሠሩ አይችሉም፤ የነዚህ ሁለት ብሔሮች ፉክክር እንደ ትግራይ ላሉ በቁጥር አናናሳ ብሔሮች ሲሳይ ነው" የሚል ነው። ነገር ግን ሕወሓት " #አምናቸዋለሁ፤ ለሥልጣኔ ስጋት አይደሉም" ብሎ ነገሮችን አልጋባልጋ ያደረገላችው ፓስተሮች ለዓመታት የብልጽግና ወንጌል ቤተክርስትያን ውስጥና ኢንተርናሽናል ሊደርሽፕ ኢንስቲትዩት ውስጥ ያስተማሯችውን የኦህዴድና የብአዴን ካድሬውችን በማስተባበር #የአሜሪካንና_የአውሮፓ_ኅብረትን ቡራኬ በመቀብል ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝን ያለ ሕውሓት ፍቃድ ሥልጣን እንዲለቁ በማድረግ፣ ዐቢይ አሕመድን በማንገሥ፤ ሕዋሓትን ከአራት ኪሎ እንዲባረር አድርገዋል።

የብልጽግና ወንጌል አቀንቃኞች ሥልጣን ከመያዝ ባለፈ የብልጽና ወንጌል ለኢትዮጵያ ችግሮች መፍትሔ ነው ብለው ያምናሉ። ለዚህም ይረዳ ዘንድ የብልጽግና ወንጌል መሠረታዊያን የኢትዮጵያን ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንዴት ሊፈቱ እንደሚችሉ የሚያሳየው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እንደተጻፈ የሚነገረው መደመር የተሰኘ ዓለማዊ መጽሐፍ በሚሊዮን በሚቆጠር ቅጅ ታትሞ እንዲሰራጭ ተደርጓል። ገዥው ፓርቲም ስሙን በአደባባይ ወደ #ብልጽግና_ፓርቲ ቀይሯል።

አሁን ብዙ ወገኖች በኦርቶዶክሳውያን ላይ የታወጀው እልቂት ስሜታዊ በሆኑና ማሰብ በማይችሉ ወጣቶች የተደረገ እንደሆነ አድርገው ይቆጥራሉ። ይህ ሞኝነት ነው !
ቀድሞ በሕወሓት "ኦርቶዶክስና አማራን ማጥፋት" ተብሎ በሰነድ የተዘጋጀ አሁንም በብልፅግና ፓርቲ " #ሀብት_ማፍራትን_እንደ_ኃጢአት_የሚቆጥር_ሃይማኖት_ባለበት_ሀገር_ውስጥ_ብልፅግናን_ማስፈን_ፈታኝ_ነው " ተብሎ# በኦርቶዶክሳውያን ላይ መንግሥታዊ የግድያና የማጥፋት አዋጅ ከታወጀ ቆይቷል።

ከዚህ በታች ካያያዝኩት ሰነድ አንደኛው ብልፅግና ፓርቲ በ2012 ዓ/ም ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ ሥልጠና ላይ የቀረበ ማሠልጠኛ ሰነድ ሲሆን በዚህ መንግሥታዊ ሰነድ ላይ ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ለብልፅግና የማትመች የለውጥ ጎታች ተደርጋ ተስላለች።

ኦርቶዶክስንና ጠላት ብለው የፈረጁትን "ነፍጠኛ" ከኢትዮጵያ ምድር የማስወገዱ ሥራ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ኦርቶዶክስን የማጥፋት ሥራ በመንግሥታዊ መዋቅር በቅንጅት እየተሠራ ባለበት ሁኔታ መንግሥትን ደጅ መጽናት ሞኝነት ነው። አድዋ ላይ ድል የመታናቸው ጠላቶቻችን በኢትዮጵያዊያንን የቆዳ ቀለም ተሸፍነውና የሃይማኖት ካባ ለብሰው እንደ እባብ አፈር ልሰው ተነሥተዋል። አሁን ተደራጅተህና ወገብህን ታጥቀህ ጠላቶችህን ድባቅ ለመምታት መነሣቱ ብቻ መፍትሔ ነው።

በተባበረ ክንድ ኢትዮጵያን ከሌቦች ለመታደግ እንነሣ!

ምንጭ፦ MikaelZethiop

ክፍል ፩ https://t.me/Tinsae_Ze_Ethiopia/568
ክፍል ፪ https://t.me/Tinsae_Ze_Ethiopia/570

https://t.me/Tinsae_Ze_Ethiopia
210 viewsBereket, 06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:39:36 የብልጽግና ወንጌል ቀጣይ ሁለተኛ ክፍል

➥የብልጽግና ወንጌልና ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ስርገት

ሕወሓት ለፕሮቴስታንቶች ቀና አመለካከት ነበረው። ሕወሓት መሀል ሀገር ውስጥ ባይተዋር በነበረበት የመጀመሪያዎቹ ዓመታት ከፕሮቴስታንቶች ውጭ የተማረና የከተማ ሰው አያምንም ነበር። በሕዋሃት ባለሥልጣናት ዘንድ "ፕሮቴስታንቶች እንደ ትግራይ ሕዝብ በደርግ ተጨቁነዋል ብናቀርባቸው ይጠቅሙናል፤ ለሥልጣናችን ስጋት አደሉም" የሚል አመለካክት ነበር። በፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮችም ዘንድም "ሕወሓት የእምነት ነጻነት እንዲከበር አድርጎልናል" የሚል ዕሳቤ ስለነበራቸው ለሕውሓት ቀና አመለካክት ነበራቸው። ብዙ የተማሩና በተለያዩ የሙያ ዘርፍ የተሰማሩ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮች ኢሕአዴግን ተቀላቅለው ሕውሓትን መሀል ሃገሩን አላምደዋል።

የብልጽግና ወንጌል ኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ በደምብ ታስቦበትና በተጠና መልኩ እንዲገባ ያደረጉት ሁለት #ከአሜሪካን ሀገር የመጡ ፓስተሮች ናቸው። በፈረንጆች አቆጣጠር 2001 ዓ/ም ጀምሮ ነው ፓስተር #ባደግ በቀለ ከካሊፎርንያ ግዛት፤ ፓስተር #ገመችስ ደስታ ከአተላንታ ጆርጂያ የተለያዩ ፕሮጄክቶችን በመቅረጽ የኢሕአዴግን ጽ/ቤት ማንኳኳት የጀመሩት። በወቅቱ የነበሩ ባለሥልጣናትም ሁለቱ ፓስተሮች ይዘዋቸው ለመጡት ፕሮጄክቶች አረንጓዴ መብራት በማብራት ረድተዋቸዋል።

ፓስተር ባደግ በቀለ በካሊፎርንያ ግዛት ለረጂም ዓመት የኖሩና ቅዱስ ኢማኑኤል የሚባል የብልጽግና ወንጌል ማስተማሪያ ቤተክርስትያን ባለቤት ሲሆኑ የዶክትሬት ዲግሪያቸውንም የሠሩት እዛው ካሊፎርንያ ውስጥ የሚገኘው የብልጽግና ወንጌላውያን ዩንቨርሲቲ የሆነው አዙሳ ፓስፊክ (Azusa Pacific) የተባለ ተቋም ውስጥ ነው። ፓስተር ባደግ በአሁኑ ወቅት የዳሎል ኦይል፣ ስድስት ኪሎ የሚገኘው ኢንተርናሽናል ሊደርሽፕ ኢንስቲትዮት፣ ኦሮሚያ ክልል ውስጥ ዓለም ጤና የሚገኘው የፕሮፌሰር ባደግ በቀለ አካዳሚ ባለቤት እንዲሁም ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ በርካታ ባንኮችና ኩባያወች ባለድርሻ ናቸው።

ፓስተር ባደግና አዙሳ ፓስፊክ ዩኒቨርሲቲ "የኢትዮጵያ ፕሮጄክት" የሚል ፕሮግራም ቀርጸው በወቅቱ ሁለተኛ ዲግሪ ለመያዝ የማይቆፍሩት ድንጋይ ያልነበረውን የኢሕአዴግ ባለሥልጣናት በሥራ አመራር የሁለተኛ ዲግሪ ለማሠልጠን ፍቃድ ያገኛሉ። ስድስት ኪሎ የኦሮሚያ ፍርድ ቤት ፊት ለፊት መሬት ተስጥቷቸው ትልቅ ሕንፃ ገንብተው በመቶዎች የሚቆጠሩ የሀገሪቱን ከፍተኛ የሲቪልና ወታደራዊ ባለሥልጣናትን #የመጀመሪያ_ዲግሪ ያላችውንም #የሌላችውንም በሥራ አመራር ዘርፍ በማስተርስ ፕሮግራም ማሠልጠን ይጀምራሉ። ሥልጠናው የሚሠጠው ኢትዮጵያ ውስጥ ቢሆንም ዲግሪውን የሚሠጠው አሜሪካን ሀገር ውስጥ የሚገኝ ዩኒቨርሲቲ በመሆኑ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት ከጠ/ሚ #መለስ_በስተቀር ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በአንድ ወቅት የፓስተር ባደግና አዙሳ ፓስፊክ ተማሪወች ሁነው ነበር። ለምሳሌ ያክል የቀድሞው ጠ/ሚ ኃ/ማርያም ደሳለኝ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ገዱ አንዳርጋቸው፣ ም/ጠ/ሚ ደመቀ መኮንን፣ መከላከያ ሚ/ር ለማ መገርሳ፤ የብልጽና ፓርቲ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊው ዓለሙ ስሜ፤ የቀድሞው የኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ሚ/ር ድኤታ ኤርምያስ ለገሰ፣ እንዲሁም ኢሕአዴግ ሹመት ሲሰጥ የትምህርት ዝግጂት በሥራ አመራር ሁለትኛ ዲግሪ የሚባልላቸው ቁጥራችው በጣም በርካታ ካድሬወች የፓስተር ባደግ ት/ቤት ምሩቃን ናቸው።

ፓስተር ባደግና አሱዛ ፓስፊክ ዩኒቭርሲቲ እነዚህን ሁሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት 'በክርስቲያን' ሥራ አመራርና ሐብት ፈጠራ ዘርፍ የማሠልጠን ዕድሉን ያገኛሉ.። እነዚህ የፓስተር ባደግ ተማሪ ባለሥልጣናት ከአቶ መለስ ህልፈት በኋላ ሥልጣኑን የተቆጣጠሩት የሕወሃት ሰዎች ዐሳብ ለማፍለቅ ሲቸገሩ፣ የድርጅቱን ካድሬውች ሰብስበው የሚመሩበት መሪ ዐሳብ ሲጠፋ ከፍትኛ የሆነ ውዥንብር ሲመጣ፣ #የፓስተር_ባደግ_ተማሪዎች የሆኑት እነ ኃ/ማርያም፣ ደመቀ፣ ዓለምነው፤ አርከበ፤ ዓለሙ፣ ገዱ፤ ለማ፣ ዓብይ የድርጅቱ #ዐሳብ_አፍላቂውች ሆኑ። አብዮታዊ ዲሞክራሲ፣ ግብርና መር ኢኮኖሚ፣ ገበሬው ነው ማኅበራዊ መሠረታችን የሚሉ አይነኬ ዐሳቦች የሀገሪቱን የፖለቲካ ሙቀት ተከትሎ ኢሕአዴግ ውስጥ አከራካሪ ዐሳቦች ሆኑ። “We have produced more than 30 mayors, Deputy Prime Ministers, 15 ministers and state ministers in Ethiopia.” ይላል የፓስተር ባደግ በባለቤትንት የሚመሩት ኢንተርናሽናል ሊደርሽፕ ኢንስቲትዮት አካዳሚ ድረ ገጽ። እንግዲህ የኢትዮጵያ ሕዝብ እስከ መኖሩም የማያውቀው አንድ ሃይማኖታዊ ተቋም 1 ጠቅላይ ሚኒስትር፣ 2 ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ፣ 15 ሚኒስትሮችንና 30 ከንቲባወችን ና በርካታ ጄኔራሎችን በክርስቲያን ሥራ አመራር ዘርፍ አስተምሮ አስመርቋል።

ሁለተኛው የብልጽግና ወንጌል የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ የበላይ ዐሳብ ሆኖ እንዲወጣ ትልቅ ሥራ የሠሩት ከአትላንታ ጆርጂያ የመጡት ፓስተር ገመቺስ ደስታ ቡባ ናቸው። #ፓስተር ገመቺስ #ሊድስታር ኢንተርናሽናል ሚኒስትሪስ (Lead star International Ministries) የተባለ በተለያዩ የብልጽግና ወንጌል ማስፋፍያ ዘርፎች ላይ የተሰማራ ተቋምን በባለቤትነት ያስተዳድራሉ። ሊድስታር ዋን ሚኒስትሪ ትሪ ፍሮንትየርስ (One Ministry Three Frontiers) በሚል መሪ ቃል ስር የብልጽግና ወንጌል በተለየዩ ቋንቋዎች የሚሰበኩባችው በርካታ "ቤተክርስትያኖችን"፣ የቴሌቪዝንና ሬድዮ ጣቢያወችን እንዲሁም ትምህርት ቤቶች ያሉት ትልቅ ተቋም ነው። ለመጥቀስ ያክል #LTV የተባለው ታዋቂ የቴሌቪዥን ጣቢያና ሊድስታር ኮሌጂ በፓስተር ገመችስ ባለለቤትነት የተያዙ ናቸው።

ፓስተር ገመቺስ #የዓለም አቀፍ የኦሮሞ ቤተክርስትያኖች ኅብረት (Worldwide Union of Oromo Churches) #ፕሬዘዳንትም ናቸው። ለኦሮሞ ፖለቲካ ባላችው ቅርበት ምክንያት ከብዙ የኦሕዴድ ባለሥልጣናት ጋር ቅርበትና ጓደኝነት ለመፍጠር የቻሉ ሲሆን #ከጠ/ሚ_ዐቢይ አሕመድ፣ #ለማ_መገርሳና #ሽመልስ_አብዲሳ ጋር ስላላቸው ቅርብ ጓደኝነትና የፖለቲካ አማካሪነት ሚና በኤል ቲቪ (LTV) አቅራቢዋ ቤቲ ታፈሰ ፕሮግራም ላይ ቀርበው ማብራራታቸው አይዘነጋም። #የኦሕዴድ_ከፍተኛ_ባለሥልጣናት ሁሉም ማለት ይቻላል #ፓስተር_ገመቺስ_ደስታና_የሪፍት_ቫሊ_ዩንቨርሲቲ_ባለቤት_የሆኑት_አቶ_ድንቁ_ደያሳ የፈጠሩት #የሃይማኖትና_የጥቅም ትስስር (ኔትወርክ) አባላት ናቸው። ይህ የሃይማኖትና የጥቅም ትስስር ሙስሊም ኦሮሞወችን ያገለለ በመሆኑ የኦሮሞን ፖለቲካ ለሁለት እንዲሰነጠቅ በማድረጉ የኦሮሚያ ክልል ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ከየትኛውም የኢትዮጵያ አካባቢ በባሰ ሰላም የራቀው አካባቢ እንዲሆን አድርጎታል።

እነዚህ ከላይ የጠቀሱት የፓስተር ባደግና የፓስተር ገመቺስ የሃይማኖትና የጥቅም ትስስሮች በጣም ጠንካራ የሆነ የውጭ የሃይማኖትና የፖለቲካ አካላት ድጋፍ ያላቸው ሲሆን በዚህ ጽሁፍ ከተጠቀሱትና በስማቸው ከተመዘገቡት ተቋማት በተጨማሪ የኢሊሊ ሆቴል ባለቤት ሁነው እንደተመዘገቡት አቶ ገምሹ በየነ ዓይነት ሰዎች ስም የተመዘገቡ በቢሊዮን ዶላር የሚቆጠር ገንዘብ የሚንቀሳቀስበት ኔትወርክ ነው።

የብልጽግና ወንጌል የመጀመሪያው ክፍል t.me/Tinsae_Ze_Ethiopia/568

https://t.me/Tinsae_Ze_Ethiopia
180 viewsBereket, 06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:39:34 #የብልጽግና ወንጌል በኢትዮጵያ
➽ሁሉም ሰው ሊያነበው የሚገባ ጥብቅ መረጃ!

"ሴረኛው ፓስተር ባደግ ኃ/ማርያም ደሳለኝን፣ ደመቀ መኮነንን፣ ዓለምነው መኮነን፤ አርከበ ቁባይን፤ ዓለሙ ስሜን፣ ገዱ አንዳርጋቸውን፤ ለማ መገርሳንና በርካታ ጄነራሎችን እንዴት 'በክርስቲያን' ሥራ አመራርና ሐብት ፈጠራ ዘርፍ ዲግሪ ሠጣቸው?"

#አብይ_አሕመድ ወደ ሥልጣን እንደመጡ #መደመር እና #ብልጽግና በተባሉ ቃላት ሲያደነቁሩን መሰንበታቸው አይዘነጋም። እነዚህ ቃላት በየሚዲያው እስኪሰለቸን ከመነገራቸውም አልፈው፤ "መደመር" የተሰኘ መጽሐፍ በዐቢይ አሕመድ ተጽፎ የፓርቲ ደጋፊዎች ተገደው እንዲሸጡና እንዲገዙ ተደረገ። "ብልጽግና" የሚል ፓርቲ ደግሞ በየክልልና ሀገር አቀፍ ደረጃ ተመሠረተ። የነዚህ ሁለት ቃላት ምንጭ ግን ምን ይሆን? ዐቢይ አሕመድ የተባሉት የቀድሞው የስለላ ድርጅት ባልደረባ፤ አሁን ደግሞ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ሁለቱን ቃላት ከየት እንዳመጡት መረዳት አሁን ያለውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሁኔታ በትንሹም ቢሆን ለመረዳት ያግዛል።

ይህንን በሚመለከት "ድራዛ አበበ" የተባለ ሰው ረዘም ያለ ጽሑፍ ያስነብበናል። እኔም ጥቂት ማሻሻያዎችን ጨምሬበት ገለጻውን እንደሚከተለው አቀርብላችኋለሁ።

#ብልጽግና (prosperity) እና #መደመር (synergy) ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ አዲስ አደንቋሪ ቃላት (buzzwords) ቢሆኑም ዓለም ላይ የቴሌቪዥን ጥምቀት (televangelism) ከተስፋፋበት ከ1980ወቹ ጀምሮ ከቴሌቪዥን ጠማቂወች (televangelists) አፍ የማይወጡ ቃላት ናቸው። አብዛኛወቹ ዝነኛ የቴሌቪዥን ጠማቂዎች #የብልጽግና_ወንጌል በሚባል አስተምህሮ የሚያምኑ ፕሮቴስታንቶች ናቸው።

➥የብልጽና ወንጌል ምንድን ነው?

የብልጽና ወንጌል የሚባለው አስትምህሮ አንዳንዴ የጤናና የሃብት ወንጌል፤ አንድንዴ ደግሞ የመሳካት ወንጌል በመባል ይታወቃል። አስትምህሮው በአጭሩ የካቶሊክ፣ የኦርቶዶክስ እና ነባር የፕሮቴስታንት ቤተክርስቲያኖቸ ከሚያምኑብት የማቴውስ ዎንጌል 19፡24 “ባለጸጎች መንግሥተ ሰማያትን ከሚወርሱ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ብትሾልክ ይቀላል /it is easier for a camel to go through the eye of a needle than for someone who is rich to enter the kingdom of God” ከሚለው እና ክርስትናን የድሆች፣ የተበደሉ፣ የተጨቆኑ፣ የተራቡ እና የታረዙ ሰዎች ተስፋነት በተቃራኒው እግዚአብሔር ባለጸጋ እንድንሆን፤ ገንዘብ እንድናክማች፤ ነግደን አንድናተርፍ፤ ጥሩ አንድንበላ፤ ጥሩ አንድንለብስ ይፈልጋል ወደሚል አስተምህሮ የሚለውጥ ነው። "የአግዚአብሔርን መንግሥት የሚወርሱት ድሆቸ፣ ምስኪኖች፣ ኀዘንትኞች፣ ደካሞች እና ያልተሳካላቸው ሳይሆኑ ባለጸጋወች፣ ብርቱወች፣ አነቃቂ ንግግር አዋቂወች፣ አውንታ ዐሳቢወች (positive thinkers) እና ኑሮ የሰመረላቸው ናቸው" የሚል ነው።

➥ባለጸጋወቹ የብልጽና ወንጌል ፓስተሮች

ባለጸጋነትን የሚያወድስውን 'ክርስትና' ለድሆች በመስበክ አንዲሁም አንድ ቀን የማርቆስ ወንጌል ትምቢት ይፈጸምልኛል ከሚሉ ምስኪኖች በሚሊዮን ዶላሮች በመሰብስብ የግል ቦይንግ አውሮፕላን የገዙ የብልጽግና ፓስተሮች በጣም ብዙ ናቸው። የብልጽግና ወንጌልም እነዚህን የሃይማኖት አባቶች ይሄን ያክል ገንዘብ ማከማችት እንደ ጽድቅ ሥራ እንጂ ከአንድ 'ክርስቲያን አባት' እንደማይጠበቅ ያልተገባ ተግባር አይቆጥረውም። ለአብንት እስኪ የሚቀጥሉትን ሦስት ባለጸጋ የብልጽግና ፓስተሮች ሐብት እንመልክት፦
1. ኬን ካፕላንድ/Kenneth Copeland፡ 760 ሚሊዪን ዶላር
2. ቲዲ ጄክስ/TD Jakes፡ 200 ሚሊዮን ዶላር
3. ዴቪድ ኦየዲፖ/ David Oyedepo: 150 ሚሊዮን ዶላር

የብልጽና ወንጌል እና የቴሌቪዥን ጥምቀት (televangelism) በኢትዮጵያ

#ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ መካነ እየሱስ፤ መሠረተ ክርስቶስ፣ ቃለ ሕይወትና ሙሉ ወንጌል የመሳሰሉት ነባሮቹ የፕሮቴስታንት ቤተክርስትያኖች የተከታዮቻችው ቁጥርና የገቢ ዐቅማቸው እየቀነሰ ሲሄድ ራሳቸውን ሐዋሪያና ነብይ ብለው የሚጠሩ የብልጽግና ወንጌል ፓስትሮች ግን የተከታዮቻቸው ቁጥር በሚሊዮኖቸ እይጨመረ ሄዷል። እንደ ዮናታን አክሊሉ፣ እዩ ጩፋ፣ እስራኤል ዳንሳ፣ ታምራት ታረቀኝና ብርቱካን ጣሰው የመሳስሉት የብልጽግና ፓስተሮች ትልልቅ ስብሰባወችንና ቴሌቪዥንን በመጠቀም ለሚሊዮኖች ታምር እንሠራለን፣ ከእግዚአብሔር ጋር እናገናኛለን፣ ክህመማችሁ እንፈውሳለን፣ ብልጽግናና ጸጋ እናስገኛለን እያሉ በነጻንት ይሰብካሉ። ግብር የማይከፈልበት በሚሊየኖች የሚቆጠር ገንዘብ ያለ ከልካይ ይሰበስባሉ። የኛ ሀገር ኬን ካፕላንድ የሆኑት እስራኤል ዳንሳና ዮናታን አክሊሉ ለባለጸጋ ፓስተርነት ስኬት የበቁት ከመሬት ተነስተው ሳይሆን ለዓመታት ከነሱ የተሻለ የትምህርት ዝግጂትና ከውጭው ዓለም ጋር ጥብቅ ቁርኝት ባላቸው ግለሰቦችና ቡድኖች በተሠራ የረጅም ዓመታት ሥራ ነው። ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለፓስተር ዮናታን 20 ሺህ ዮሮ ጳጉሜ 1፣ 2011 ዓ/ም በሚሊኒየም አዳራሽ በተዘጋጀ "መልካም ወጣቶች" የተሰኘ ሃይማኖታዊ ፕሮግራም ላይ ሲያበረክቱ ገንዘቡን ከየት አመጡት? ለምን ይሄን ያክል ገንዘብ ለአንድ 'የሃይማኖት አባት' ሰጡ ብሎ የጠየቀው ሰው ትንሽ ነው።

ቀጣይ ተከታታይ ክፍሎች በሰፊው ➥#የብልጽግና ወንጌልና ወደ ኢትዮጵያ ፖለቲካ ስርገት በሚል ጠለቅ ያለ ትንታኔ ስለሚኖረን ይህን ቻናል ይከታተሉ። @Tinsae_Ze_Ethiopia


ጸሎተ ለማርያም ወስእለታ ወአድኅነነ እመዓተ ወልዳ
ጸሎተ ለማርያም ወስእለታ ለህዝበ ክርስትያን እመዓተ ወልዳ
ጸሎተ ለማርያም ወስእለታ ለሀገሪትነ ኢትዮዽያ እመዓተ ወልዳ

ቅድመ ኢትዮጵያ ትንሳዔ
ስለሳልሳዊ ቴዎድሮስ
የኢሉሚናቲ ሴራዎችን ማጋለጥ
ህዝበ ክርስቲያንን ማንቃት

https://t.me/Tinsae_Ze_Ethiopia
281 viewsBereket, 06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-25 09:36:59 Messages in this channel will no longer be automatically deleted
06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 07:36:01 Messages in this channel will be automatically deleted after 1 month
04:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-13 21:11:37
ኦርቶዶክስ ኖት ?

ለመሆኑ እስካሁን በቴሌግራም ትልቁን የኦርቶዶክስ ቻናል ተቀላቅለዋል ? ካልተቀላቀሉ አሁኑኑ ይቀላቀሉ ።

➱ የብራና መፃህፍት በpdf ፣
➱ የታላላቅ መምህራን ስብከቶች በቮይስ ፣
➱ አስተማሪ ፅሁፎች ፣
➱ መንፈሳዊ ግጥምና ልቦለዶች ፣
➱ መንፈሳዊ ፊልሞች ፣
➱ ኦርቶዶክሳዊ መዝሙሮች ይቀርቡበታል።
ኦርቶዶክሳዊ የሆነ ሁሉ ሊቀላቀለው የሚገባ ቻናል ነው።

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

◤◢◤◢◤◢◣◥◣◥◣◥
█ 🇯 🇴 🇮 🇳  █
◣◥◣◥◣◥◤◢◤◢◤◢

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
1.9K viewsኦርቶዶክስ ፕሮሞሽን ❖ ፫ next, 18:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ