Get Mystery Box with random crypto!

የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!

የቴሌግራም ቻናል አርማ teyakaenamels — የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!
የቴሌግራም ቻናል አርማ teyakaenamels — የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!
የሰርጥ አድራሻ: @teyakaenamels
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.99K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልሶች የሚተላፉፈበት!
አስተያየት
@teyakaenamles_bot
https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjA
✝ወደ ፌስቡክ ፔጃችን ለመቀላቀል➡https://www.facebook.com/
✝ወደ ይቱብ ቻናል ለመቀላቀል➡https://youtube.com/channel/UCRc7pSmO4wrs-mhAfxwEuOw

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-06-28 07:06:24 ሰኔ 21 ለሚከበረው የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ከእመቤታችን 33ቱ በዓላት አንዱ ነው፤ ህንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል።የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን የታነጸው በዛሬዋ ቀን ነው አናጺውም እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ቦታው ፊልጰስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው።ጴጥሮስ፤ ዮሐንስ በርናባስና ሌሎችም ሐዋርያት በፊልጰስዩስ ተሰብስበው ሳለ ጌታችን መድሐኒታችን እየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መልአክትን አስከትሎ ይወርዳል እመቤታችን በቀኙ ነበረች፤ 3 ድንጋዮችን አንስቶ ጎተታቸው እንደ ሰም ተለጠጡ እንደ ግድግዳም ሆኑ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ በሰማያዊቷ እየሩሳሌም አምሳያ አድረጎ አነጻት ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፤ ዳግመኛ በበነጋው ሰኔ 21 ቀን እመቤታችንን እና ቅዱሳን መልአክትን አስከትሎ ይወርዳል ቅዳሴ ቀድሶ ለሐዋርያቱ አቆረባቸው ፍጹም ደስታም ሆነ።ከዚህ በኃላ ሐዋርያት ከጌታ እንዳዩት በዓለም ዞረው ቤተክርስቲያን አንጸዋል። ከዚያ በፊት የነበረው የነሶሎሞን ቤተ መቅደስ የአይሁድ ምኩራብ የአይሁድ ስርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ እንጂ የአዲስ ኪዳን የቁርባንም ሆነ የጥምቀት ስርዓት መፈጸሚያ አልነበረም፤ ታዲያ ሐዋርያት የት ነበር ህዝቡን የሚያጠምቁት የሚያቆርቡት ካሉ በየሰው ቤት ነበር። ዳግመኛ በዛሬዋ ቀን ታላቁ ነብይ ኤልሳዕ አረፈ። ይህ ነብይ በ 12 ጥማድ በሬ ሲያርስ ቴስቢያዊው ነብዩ ኤልያስ ተከተለኝ አለው ምንም ሳያቅማማ ሀብት ንብረቱን ትቶ ተከተለው፤ ኤልያስ በእሳት ሰረገላ ከማረጉ በፊት ምን እንዳደርግልህ ትፈልጋለህ ይለዋል ባንተ ላይ ያደረ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ እጥፍ ድርብ ሆኖ ይደርቢኝ ይለዋል፤ እንደ ቃሉ ሆነለት ተደረገለት፤ ኤልያስ አንድ ሙት ሲያስነሳ ኤልሳዕ ሁለት ሙት አስነስቷል፤ ኤልያስ አንድ ጊዜ ባህር ሲከፍል ኤልሳዕ ሁለት ጊዜ ባህር ከፍሏል። የእምቤታችንን የኤልሳዕ ጋን ይላታል ኤልሳ የመረረውን ውኃ እንዳጣፈጠ እመቤታችንም ይህን መራራ ዓለም ጌታን በመውለዷ አጣፍጣዋለች፤ የዚህ ነብይ ድንቅ ታሪኩ 2ኛ ነገስት ላይ በስፋት ተጽፏል ሰኔ 20 ቀን እረፍቱ ነው ቤተክርስቲያን የዛሬውን ቀን እመቤታችንን እና ነብዩን አስባ ትውላለችከበዓሉ ያሳትፈን የእመቤታችን ምልጃና ረዳትነት አይለየን!
910 viewssara mariyam, 04:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-19 09:08:27 ስንክሳር ዘወርሃ ሰኔ አስራ ሁለት(፲፪)
1.2K viewssara mariyam, 06:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 12:15:17 #ወረደ #መንፈስ #ቅዱስ

ሃሌ ሃሌ ሉያ ወረደ መንፈስ ቅዱስ/፪/
ላዕለ ሐዋርያት ከመ ዘእሳት/፪/

ትርጉም፡- ቅድመ ዓለም የነበረ አሁንም ያለ ዓለምን አሳልፎ የሚኖር መንፈስ ቅዱስ በሐዋርያት ላይ በእሳት አምሳል ወረደ፡፡
https://t.me/yaradawyimezmuroch
https://www.facebook.com/saramareyama
1.5K viewsናፍቆት ተስፋ, 09:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 12:07:58
1.3K viewssara mariyam, 09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-12 12:07:39 ዛሬ እኮ ታላቅ በአል ነው #በዓለ_ጰራቅሊጦስ##

☞ሰኔ 5 እንኳን ለበዓለ ጰራቅሊጦስ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡

☞ቃል የግሪክ ሲሆን ትርጓሜው አፅናኝ መንፈስ ቅዱስ ማለት ነው፡፡ይህ በዓል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በተነሣ በሃምሳኛው በዐረገ በአሥራኛው ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡
☞ለሐዋርያት መንፈስ ቅዱስ የወረደው ከጠዎቱ ሦስት ላይ ነበር፡፡

☞ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱሳን ሐዋርያት በተናገረው
አምላካዊ ቃል መሠረት"ኃይልን እስክትለብሱ በኢየሩሳሌም ቆዩ" ብሏቸው ነበር

ሰዓቱ ሲደርስ የሚያጽናኑበት ብርታት የሚሆናቸው የዕውቀት፤ የኃይል መንፈስ
ቅዱስ ሰደደላቸው፡፡

☞"በዓለ ሃምሳም የተባለው ቀን በደረሰ ጊዜ ሁሉም በአንድ ልብ ሆነው አብረው
ሳሉ ድንገት እንደሚቃጠል ዐውሎ ነፋስ ከሰማይ ድምጽ መጣ በሁሉም መንፈስ
ቅዱስ ሞላባቸው መንፈስም ይናገሩ ዘንድ እንደ ሠጣቸው በሌላ ልሣኖች ይናገሩ
ጀመር"(የሐዋርያት ሥራ 2፥1-11)

☞ይህችንም ዕለት ሊቃውንት የቤተ ክርስቲያን የልደት ቀን በማለት ይጠሯታል፡፡
1.3K viewssara mariyam, 09:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 10:35:36 https://t.me/+vWm8oOjSLsYwOGI0
3.0K viewsናፍቆት ተስፋ, 07:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 17:50:29
4.1K viewssara mariyam, 14:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 17:49:57 * በዚህ ሳምንት ብሉያትና ሐዲሳት መጻሕፍት ከጠዋት እስከ ማታ ይነበባሉ። የአምላኮ ስግደት ይሰገዳል። ይኸውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ እኛ ሲል መስቀልን ተሸክሞ ሲወድቅ ሲነሳ የዋለበትን፣ ይልቁንም ሥርዓተ ስግደትን ራሱ ሰግዶ እኛን ያስተማረንን በማሰብ ነው። /ሉቃ. 22:41-45 ፤ ዮሐ. 4:22-24/
.
* ስለዚህ በዚህ ሳምንት ወርኃዊ፣ አመታዊ በዓል ቢሆን እንኳ ስግደት አይቋረጥም። የአምልኮት ስግደት ሳምንት ስለሆነ። ዲያቆኑ ጥቁር ለብሶ መስቀል ይዞ ቃጭል እያቃጭለ ቤተክርስቲያንን ሶስት ጊዜ መዞሩ ዲያቆኒ የዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፣ ቃጭል የእመቤታችን ምሳሌ ሲሆኑ፤ ዮሐንስና እመቤታችን ጌታችን የተሰቀለበትን እግር መስቀሉን እየዞሩ አልቅሰው ነበርና።

* በዕለተ ዓርብ ሰርህ ሲሆን ምእመናን ወደ ቄሱ እየቀረቡ ስግደት እንዲሰጣቸው ይጠይቃሉ። ቄሱም በወይራ ቅጠል እየጠበጠበ ተጨማሪ ቀን ሲሰግዱ ከዋሉ ሌላ ስግደት ይሰጣቸዋል። ጥብጠባ የጌታችን ግርፋት ምሳሌ ነው። አንድም የተግሳጸ ምሳሌ ነው። /ማቴ 26:27/

አክፍሎት

* አክፍሎት ማለት ማካፈል፣ ማጠፍ፣መደረብ፣ ሁለቱን ቀን አንድ አድርጎ መጾም፣ ጌታ ከተያዘበት እስከ ተነሳበት ድረስ ይህ ስርዓት የመጣው በቤተክርስቲያናችን ልማድ እመቤታችን፣ ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታን ትንሳኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤ በመቆየታቸው ምክንያት ነው። በሀገታችን ብዙ ስዎች ሐሙስ ማታ የቀመሱ እሑድ የትንሳኤ እለት ብቻ እህልና ውኃን የሚቀምሱት፣ ያልተቻላቸው ግን ዓርብ ማታ የቀመሱ እስከ ትንሳኤ ይሰነብታሉ። የሁለት ቀን ማክፈሉ እንኳ ቢከብድ ቅዳሜ ማክፈል ሥርዓት ነው ቅዳሴው በመንፈቀ ሌሊት ስለሆነ በልቶ መቁረብ እንዳይሆን።
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++

3. በሕማማት ለምን መስቀል አንሳለምም ወይም አናማትብም ?

* የመስቀል ክብር እና ኃይል የታወቀው ጌታ በመስቀል ከተሰቀለ በኃላ ነው በሰሙነ ህማማት ከ ሰኞ እስከ ዓርብ ያሉ ቅናት የዓመት ፍዳ መታሰቢያ ናቸው በዚህ ዘመናት ሰዎች የመስቀልን አገልግሎት እንዳልጀመሩ ለማሳየት በሰሙነ ህማማት በቤተክርስቲያን ስርዓት መሰረት መስቀል ማሳለምም ሆነ የማማተብ ስርዓት የለም
~~~~~~

4. በሰሙነ ህማማት ለምን አንሳሳምም ?

* ይሁዳ ጌታውን በመሳም አሳልፎ ሰጥቷል እኛም እንደ ይሁዳ ክፋት ካለው መሳሳም መለየታችንን ለማስረዳት ከዚህ በተጨማሪ ፍፁም ሰላም በዘመነ ፍዳ እንዳልነበረ ለማሳየት በሰሙነ ህማማት እስከ መሳሳም የደረሰ ጥብቅ ሰላምታ የለም
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++

5. ስለ ሰሙነ ህማማት በመጽሐፍ ቅዱስ የተጻፈ አለን?

* ነብዩ ኢሳይያስ " በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ ሕማማችንንም ተሸክሞአል" /ኢሳ. 53:4/ ይላል ህማማት የሚለው ቃል በቀጥታ ከመጽሐፍ ቅዱስ የወሰደ ሲሆን የጌታን መከራ የምናስብበት ሳምንት ነው የጌታችንን ሞቱን ህማሙን ማሰብ መዘከር እንደሚገባ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይላል / ጌታ እስኪ መጣ ድረስ ሞቱን ትናገራላችሁና / (1ኛ ቆሮ 11: 26)

* ይህ ሳምንት ለአይሁድና ለመሰሎቻቸው የደስታ ወቅት ቢሆንም ለክርስትያኖች በጥልቅ ኅዘን ውስጥ የሚገቡበት ሳምንት ነው እንዲሁ ተብሎ እንደተጻፈ / እናንተ ታለቅሳላችሁ ሙሾም ታወጣላችሁ ዓለም ግን ደስ ይለዋል እናንተም ታዝናላችሁ ነገር ግን ኃዘናችሁ ወደ ደስታ ይለወጣል/ (ዮሐ 16:20)
በእርግጥ ኅልዘናችን ትንሳኤውን እስንናይ ለጥቂት ጊዜ ቢሆንም ግን እናዝናለን በትንሳኤው ደግሞ ደስታውን እንካፈላለን
~~~~~~

6. በሰሙነ ህማማት የማይፈቀዱ ሌሎች ነገሮች ምን ምን ናቸው ?

* ማንኛውም ለስጋ የሚያደሉ ተግባሮች መቀነስ እና ቢቻለን አብዛኛውን ጊዜአችንን በቤተ እግዚአብሔር የጌታን መከራ ሕማም በማሰብ በጾም በስግደት በጸሎት ማሳለፍ
በትዳር ያሉ በመኝታ ከመተዋወቅ መታቀብ
ቢቻል አመጋገባችንን ከወትሮው መቀነስ

ከህማሙ ከመከራው በረከት ይክፈለን
ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን
ወስበሀት ለእግዚአብሔር
3.2K viewssara mariyam, 14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-18 17:49:55 1. ሕጽበተ እግር ይባላል።
ይህ ስያሜ የተሰጠው ጌታችን በዚህ ዕለት የደቀመዛሙርቱን እግር በማጠቡ ምክንያት ነው። ይህም የሚያሳየው የዓለምን ኃጢአት ለማጠብ የመጣ መሆኑን ነው። ይህንን ለማስታወስ ዛሬ ካህናት በተለይም ሊቃነ ጳጳሳት በመካከላችን ተገኝተህ የእኛንና የሕዝቡን ኃጢአት እጠብ ሲሉ ሲሉ በቤተ ክርስቲያናችን የተገኙትን ምእመናን እግር በወይንና በወይራ ቅጠል ሲያጥቡ ያረፍዳሉ። / ዮሐ. 13:4-15/

2. የጸሎት ሐሙስ ይባላል።
የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ የሚደክም ሥጋን የተዋሐደ አምላክ ፍፁም ሰው መሆኑን ለመግለጽና ለአርአያነት ጠላቶቹ መጥተው እስኪይዙት ድረስ በጌቴሴማኒ ሲጸልይ በመቆየቱ ነው /ማቴ 26:36 ፤ ዮሐ 17:1/

3. የምስጢር ቀንም ይባላል።
ከሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን አንዱ በዚህ ዕለት ተመስርቷል። ይኸውም ይህ ስለ እናንተ በመስቀል ላይ የሚቆረሰው ስጋዬ ነው፤ እንካችሁ ብሉ ጽዋውንም አንስቶ አመሰገነ ይህ ስለ እናንተ ነገ በመስቀል ላይ የሚፈስ ደሜ ነው፤ ከእርሱም ጠጡ በማለት እኛ ከእርሱ ጋር አንድ የምንሆንበትን መንገድ ከጠላት ዲያብሎስ ሰውሮ ለደቀ መዛሙርቱ የገለጠበት ቀን በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው።

~ በዚህ ዕለት ቅዳሴ ይቀደሳል። የሚቀደሰውን በለሆሳስ /በዝግታ/ ሲሆን እንደ ቃጭል በመሆን የሚያገለግለውም ጽናጽል ነው። ይህም አይሁድ ጌታችንን ለመያዝ ሲመጡ ድምፃቸውን ዝግ አድርገው በለሆሳስ እየተነጋገሩ መምጣታቸውን ለማሰብ ነው።

~ በቅዳሴውም ኑዛዜ አይደረግም። ሥርአተ ቁርባን ግን ይፈጸምበታል። ይህም ጌታችን የሰጠውን ዘለዓለማዊ ቃል ኪዳን ለማሰብ ነው። በዚህ ዕለት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ በንስሀ ታጥቦ ተዘጋጅቶ ቅዱስ ስጋውንና ክቡር ደሙን መቀበል ይኖርበታል።

4. የሐዲስ ኪዳን ሐሙስ ይባላል።
ምክንያቱም መስዋዕተ ኦሪት ማለትም በእንሰሳ ደም የሚቀርበው መስዋዕት ማብቃቱን ገልጦ፣ ለድኀነቱ ዓለም ራሱን የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ያቀረበበት ዕለት በመሆኑ ነው። /ሉቃ 22:18-20/ ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው ደሜ የሚሆን የአዲስ ኪዳን ነው። ከእርሱም ጠጡ በማለቱ ይታወቃል። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለአዳምና ለልጆቹ ሁሉ ዘላለማዊ ቃል ኪዳን በራሱ ደም የፈጸመበት ዕለት መሆኑን በማሰብ የቃል ኪዳኑ ፈጻሚዎች ጠባቂዎች መሆን እንደሚገባን እንማራለን።

5. የነጻነት ሐሙስ ይባላል።
ለኃጢአትና ለዲያብሎስ ባርያ ሆኖ መኖር ማብቃቱ፤ የሰው ልጅ ያጣውን ክብር መልሶ ማግኘቱ የተረጋገጠበት ቀን ስለሆነ ነው። ራሱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ሰው ልጅ ነፃነት ሲናገር ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባሪያ ጌታው የሚደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆቼ ግን ብያችኋለሁ በማለቱ /ዮሐ 15:15/ ከባርነት ነፃ የወጣንበት ቀን መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ በግልጽ ያስረዳል። ስለዚህ እያንዳንዱ ክርስቲያን ከኃጢአት ባርነት በመራቅ ከእግዚአብሔር ሕይወቱን በቅድስና መምርልት ይኖርበታል። እርሱ ጠላቶቹ ስንሆን ወዳጆቹ አድርጎናል። /ማቴ 26:17-19/

6. አረንጓዴው ሐሙስ ይባላል።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአትክልት ቦታ ስለ ጸለየ።

#ዕለተ_ዓርብ

* የስቅለት ቀን ስቅለት፣ መስቀል፣ አሰቃቀል ማለት ነው። መስቀል በቁሙ መስቀያ፣ መመዘኛ፣ መሰቀያ፣ መንጠልጠያ፣ ለሞት የሚያበቃ መከራ በማር 8:34 ወጸውዖሙ ለሕዝብ ምስል አርዳኢሁ ወይቤሎሙ ዘይፈቅድ ይፀመደኒ ይጽልአ ለነፍሱ ወያጥብዕ ወይፁር መስቀለ ሞቱ ወይትለወኒ፤ ከደቀ መዛሙርቱም ጋር ሕዝቡን ጠርቶ እንዲህ አላቸው። ሊከተለኝ የሚወድ ሰው ራሱን ይካድ፤ ጨክኖም የሞቱን መስቀል ተሸክሞ ይከተለኝ ይላል።

* ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም በ /1ኛ ቆሮ. 1:17/ ላይ ወኢኮነ በጥበበ ነገር ከመ ኢንስዐር፤ መስቀሉ ለክርስቶስ የክርስቶስን መስቀሉን ከንቱ እንዳናደርግ ነገርን በማራቀቅ አይደለም ይላል።

* ጌታችን በተሰቀለ ዕለት ከስድስት ሰዓት ጅምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። /ፀሐይ ጨለመ/ ፣ እንሆም የቤተ መቅደስ መጋረጃም ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፤ ምድርም ተናወጠች፤ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤ መቃብሮችም ተከፈቱ፤ ተኝተውም ከነበሩት ቅዱሳን ብዙዎች ተነሱ፤ ከትንሳኤውም በኋላ ከመቃብሮች ወጥተው ወደ ቅድስት ከተማ ለብዙዎች ታዩ። /ማቴ 27:51/

* ጌታችን ለዓለሙ ያሰበውን ቤዛነት ሊፈጽም በመስቀል ላይ መሰቀሉ የሚታሰብበት ነውና ለስቅለቱ መታሰቢያ የሚሆን አጎበር ተዘጋጅቶ ከርቤ እየታጠነ ስቅለቱን የሚመለከት ምንባባት ሲነበብና ሲሰገድ ይዋላል። የሰው ልጅ በሙሉ በእግረ አጋንንት ተረግጦ ከፈጣሪው ተጣልቶ ለ5500 ዘመን በጨለማ መኖሩን ለማስታወስም መንበሩ ታቦቱ በዚህ ቀን በጥቁር ልብስ ይሸፈናሉ። ዲያቆኑም በቤተ ክርስቲያን በመዞር የሚያሰማው የቃጭል ድምጽ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለቅሶ አንድም ዋይ ዋይ እያሉ የተከተሉት የኢየሩሳሌም ሴቶችን ሙሾም ምሳሌ ነው። /ሉቃ 23:31/

* በዕለተ አርብ ነፍሳት ከሲኦል ወጡ። አንቀጸ ገነት ተከፈተልን፣ ርስተ መንግስተ ሰማያት ተመለሰችልን፣ አባታችን አዳምም ከፈጣሪው ጋር ታረቀልን በማለት ገብረ ሰላመ በመስቀሉ ትንሳኤሁ አግሃዶ እያልን የተድላ፣ የደስታ ምልክት ወይም መገለጫ የሆነ ልምላሜ ያለውን ቆጽለ ሆሳዕና ወይም ቄጤማ ግጫ ይዘን የምስራች እንባባላለን። /ኤፌ. 2:15-15/ ወዘእንበለ ምሳሌሰ ኢተናግሮሙ፣ ያለ ምሳሌ አልተናገረምና እንዳለ /ማቴ 13:34-35/ በኖኀ ጊዜም ርግብ ሐጸ ማየ አይኀ፣ ነትገ ማየ አይኅ፣ የጥፋት ውኃ ጎደለ፣ አለቀ እያለች ቅጠል ዕፅ ዘይት ይዛ ለኖኀ አብስራዋለች። /ዘፍ 8:8-11/

* ርግብ የካህናት፣ ኖኀ የምእመናን፣ ኖኀ እጁን ዘርግቶ ርግብን እንደተቀበላት ካህናትም በየመንደሩ እየዞሩ ክርስቶስ ተመረመረ ዲያብሎስ ታሰረ በማለት ቄጤማ ሲያድሉ ምእመናንም እጃቸውን ዘርግተው መቀበላቸው የዚህ ምሳሌ ነው። ስለዚህ አሁንም ቢገኝ የወይራ ልምላሜ ቢታጣ ግጫን እየታደልን የምስራች መባባላችን ነፍሳት ከሲኦል ለመውጣታቸው መታሰቢያ ነው። ይህን ቅጠል ልምላሜ ይዞ ተድላ፣ ደስታ መግለጽ ከጥንት ጀምሮ ሲያያዝ የመጣ ነው እንጂ እንግዳ ነገር አይደለም። ለዚህ በመጀመሪያዪቱ ቀን ከበጎ እንጨት ፍሬን የሰሌንና የተምር ዛፍ ልምላሜ ይዛችሁ በየ አመቱ ሰባት ቀን ተድላ፣ ደስታ ታደርጋላችሁ ብሏል /ዘሌ. 23:40-44/።
~~~~~~

2. በሰሙነ ሕማማት ጊዜ ቤተክርቲያናችን የምታደርገው ትውፊት/ የሐዋ.ሥራ 1:13/

* ከሆሳዕና እስከ ቅዳሜ ሥዑር ያሉት ዕለታት የዓመተ ፍዳ መታሰቢያ ናቸው። ጸሎተ ፍትሐት አይደረግም። በዚህ ሳምንት ውስጥ ለሚሞቱ ምዕመናን እግዚኦ ሕያዋን ይደገማልና። በሰሙነ ሕማማት መስቀል የለም። ስምንቱ የዘመነ ኦሪት ምሳሌ ስለሆነ እርስ በእራስ መሳሳም፣ ሰላም መባባልና መልክዐ መልክዕ መድገም የለም። ይኸውም ይሁዳ ክርስቶስን በሰላምታ ስላስያዘው እርሱን ላለመምሰል። /ማቴ 26/
1.6K viewssara mariyam, 14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ