Get Mystery Box with random crypto!

የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!

የቴሌግራም ቻናል አርማ teyakaenamels — የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!
የቴሌግራም ቻናል አርማ teyakaenamels — የድንግል ማርያም ልጆች!♥ጥያቄና መልስ ቻናል!
የሰርጥ አድራሻ: @teyakaenamels
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 3.99K
የሰርጥ መግለጫ

መንፈሳዊ የጠቅላላ እውቀት ጥያቄና መልሶች የሚተላፉፈበት!
አስተያየት
@teyakaenamles_bot
https://t.me/joinchat/AAAAAExg87tr37X8VNFEjA
✝ወደ ፌስቡክ ፔጃችን ለመቀላቀል➡https://www.facebook.com/
✝ወደ ይቱብ ቻናል ለመቀላቀል➡https://youtube.com/channel/UCRc7pSmO4wrs-mhAfxwEuOw

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-04-18 17:49:49 +++ ሰሙነ ህማማትና ሚስጢራቱ +++

~ ከትንሳኤ በፊት ያለው ሳምንት ሰሙነ ህማማት ይባላል። ይኸውም በነቢዩ ኢሳይያስ ነሰአ ደዌነ ወፆረ ህማማነ፣ በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ፤ ሕማማችንንም ተሸከመ፤ በእርሱ ቁስል ዕኛ ተፈወስን። /ኢሳ 53:34-36/ ተብሎ በመንፈስ ቅዱስ ትንቢት የተነገረው ቃል ተፈጸመ። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ሳምንት ውስጥ ለድኅነት ዓለም ሲል በአጭር ቁመት፣ በጠባብ ደረት ተወስኖ የተቀበለውን ጸዋትወ መከራ ለማስታወስ የወጣ ስያሜ ነው።

1. በዚህ ሳምንት ውስጥ ያሉት ዕለታት ስያሜያቸውና በእያንዳንዳቸው ዕለታት የተፈጸሙትን ድርጊቶች እንደሚከተለው እንመለከታለን።

ሰኞ

* አንጽሖተ ቤተ መቅደስና መርገም በለስ የተፈጸመበት ዕለት ነው። የሆሳዕና ዕለት ቢታንያ ያድራል። በማግስቱም ከቢታንያ ሲወጣ ተራበ ወበሳኒታ ወፂኦ አምቢታንያ ርኀበ ወርእየ በለስ እምርኁቅ ወባቲ ቌጽለ ወሖረ ይርአይ እመቦ ዘይረክብ ፍሬ በውስቴታ ወበጺሖ ኀቤሃ አልቦ ዘረከበ ዘእንበለ ቁጽል ባህቲቱ እስመ ኢኮነ ጊዜሁ ለበለስ፣ ቅጠል ያላት በለስ ከሩቅ ዓይቶ ወደ በለሲቱ ቀረበ፤ ነገር ግን ከቅጠል በቀር አንዳችም ፍሬ አላገኘባትም፤ ወአውሥአ ወይቤላ ለዓለም አልቦ ዘይበልዕ ፍሬ እምኔኪ እንከ፤ ከአሁን ጅምሮ ማንም ከአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ረገማት። / ማር 11:11-12/

*በለስ የተባለች ቤተ እስራኤል ናት። ፍሬ የተባለች ሃይማኖት ምግባር ናት። ከእስራኤል ፍቅርን ሃይማኖትን ምግባርን ፈለገ አላገኘም። እስራኤል ህዝበ እስራኤል መባል እንጂ ደግ ሰው አይገኝብሽ ብሎ ረገማት። በመርገም ምክኒያት እርሱ ከለያቸው በስተቀር ድግ ሰው ጠፋባት።

* አንድም በለስ ኦሪት ናት። በዚህ ዓለም ስፍና ቢያገኛት ኦሪትና ነቢያትን ልሽር አልመጣሁም ልፈጽም እንጂ በማለት ፈጸማት። እጸ በለስን ፍሬ በአንቺ አይሁን አላት።

* አንድም በለስ ኃጢአት ናት። የበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነች ኃጢአትም በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት። በለስ ሲበሉት ይጣፍጣል፤ ቆይቶ ግን ይመራል፤ ኃጢአትም ሲሰሩት ደስ ደስ ያሰኛል፤ ኋላ ግን ያሳዝናል፤ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ከኃጥአን ጋር ዋለ፤ ኃጥእ ከመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰት፤ በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልከት ፍሬ አላገኘባትም አለ፤ በአንቺ ፍሬ አይገኝ የሚለውም፤ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ የሚቀር አይኑር ለማለት ነው፤ ስትረገም ፈጥና መድረቋም፣ በአዳም ምክኒያት ያገኘችን እዳ በደል በእርሱ ካሳነት እንደጠፋችልን ለመግለጽ ነው።

* ከዚህ በኋላ ወደ ቤተመቅደስ ሄደ፤ ቤተ መቅደስ፣ ቤተጸሎት፣ ቤተመስዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቤተምስያጥ / የንግድ ቤት/ ሆኖ ቢያገኘው ቤቴ የጸሎት ቤት ትባላለች፤ እናንተ ግን የወንበዶች ዋሻ አደረጋችኋት ብሎ የሚሸጡትን ሁሉ ገለበጠባቸው፤ ገርፎም አስወጣቸው፤ ይህም የሚያሳየው ማደሪያው ቤቱ የነበርን የአዳም ልጆች ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያግኘን ኃጢአታችንን ሁሉ እንዳራቀልን የሚገልጽ ነው።

* በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምዕመናን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተገኝተው ወዛቸው ጠብ እስኪል ድረስ በነግህ፣ በሰለስት፣በስድስት ሰዓትና በተሰዓቱ ሰዓት መላልሰው ሲሰግዱና ሲጸልዩ ይሰነብታሉ። በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉ። ምክንያቱም የደረሰበትን መከራ ኅዘኑንና /5500/ ዘመን የሰው ልጅ በጨለማ ህይወት ይኖር እንደነበር ለማዘከር ነው።

#ማክሰኞ

* የጥያቄ ቀን በመባል ይታወቃል። ምክንያቱም ሹመትን ወይም ሥልጣንን ለሰው ልጅ የሰጠ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሰኞ ባደረገው አንጽሖተ ቤተ መቅደስ ምክንያት በዚህ ዕለት ስለ ስልጣኑ በጸሐፍት ፈሪሳውያን ተጠይቋልና።

* ጥያቄውም ከምድርልውያን ነገስታት፣ ከሌዋውያን ካህናት ያይደለህ ትምህርት ማስተማር፣ ተአምራት ማድረግ፣ ገበያ መፍታት በማን ስልጣን ታደርጋለህ ? የሚል ነበር

~ ይህንስ ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ። የየሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች ? ከሰማይ ወይስ ከሰው ? አላቸው። እነርሱም ከሰማይ ነው ብንል ለምን አልተቀበላችሁትም ? ይለናል። ከሰው ነው ብንል ሕዝቡ ሁሉ ዮሐንስን እንደ አባት ያከብሩታል፤ እንደ መምህርነቱም ይፈሩታልና ሕዝቡን እንፈራለን ተባብለው ወዴት እንደሆነ አናውቅም ብለው መለሱለት። እርሱም በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ እኔም አልነግራችሁም አላቸው። ይህንንም መጠየቃቸው እርሱ የሚያደርጋቸውን ሁሉ በራሱ ሥልጣን እንዲያደርግ አጥተውት አልነበረም። ልቦናቸው በክፋትና በጥርጥር ስለተሞላ ነው እንጂ። ከዚህ የምንማረው የእነሱን ክፉ ጠባይና ግብር መከተል እንደማይገባን ነው።

* በዚህ ዕለት በቤተ መቅደስም ረጅም ትምህርት ስላስተማረ የትምህርት ቀንም ይባላል። ይኸውም ከሃይማኖት የራቁትን፣ ከፍቅረ እግዚአብሔር የተለዩትን አስተምሮ ማቅረብ፣ መክሮ መመለስ እንደሚገባ ሲያስተምር ነው።

#ረቡዕ

* ይህ ዕለት የምክር ቀን ይባላል። ምክንያቱም የአይሁድ ሊቃነ ካህናትና ጻሐፍት ጌታን እንዴት መያዝ እንደሚገባቸው ምክር የጀመሩበት ቀን ስለሆነ ነው። በዚህ ምክራቸው ላይ በጣም ትልቅ ጭንቀት ነበር። ምክንያቱም ወቅቱ የፈሲካ በዓላቸውን የሚያከብሩበት በመሆኑ ብዙውን ሕዝብም በጌታችን ትምህርት የተማረኩ፣ ተአምራቱን የሚያደንቁ ስለነበር ሁከት እንዳይፈጥር ነው። በዚህ ጭንቀት ሳሉ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ የአስቆሮቱ ይሁዳ በመካከላቸው በመገኘት የምክራቸው ተባባሪ ሆኖ ጭንቀታቸውን አስወግዶላቸዋል። / ማቴ 26:1-5 ፤ ማር 14:1-2 /

* የሐዲስ ኪዳን ካህናት ምእመናን በዚህ ዕለት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተሰብስበው ከእህልና ውኃ ተለይተው፣ መላ ሰውነታቸውን ለእግዚአብሔር አስገዝተው፣ የሞት ፍርዱን በማሰብና በማልቀስ፣ ስለዚህ ታሪክ የሚይልወሳውንም በማንበብ እስከ ኮከብ መውጫ በጾም፤ በጸሎትና በስግደት ተወስነው ይቆዩና ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ።

~ ይሁዳ ማለት ታማኝ ማለት ቢሆንም እንደ ስሙ ግብሩ አልተገናኘም። ስምና ግብሩ አልተባበረለትም። እኛስ እንደ ስማችን ይሆን ግብራችን ?

* መልካም መዓዛ ያለው ቀንም ይባላል። ምክንያቱም ጌታችን በዚህ ዕለት በቤተ ስምዖን ዘለምጽ ተቀምጦ ሳለ መላ ህይወቷን ለዝሙት አስገዝታ ትኖር የነበረችው ማርያም እንተ እፍረት ከእንግዲህ በኃጢአት ተጎድቶ ይኖር የነበረውን ህይወቴን እደዚሁ መልካም ሽቶ ዋጋው እጅግ በጣም ውድ የሆነ ከሦስት መቶ ዲናር በላይ የሚያወጣ በአልባስጥሮስ ብልቃጥ የሞላ ሽቱ ይዞ በመሄድ በጠጉሩ /በራሱ/ ላይ በማርከፍከፍ ስላቀረበች ነው።

* የእንባ ቀንም ይባላል። ይህም ይህችው ሴት በጌታችን እግር ላይ ተደፍታ መላ ኃጢአቷን ይቅር እንዲላት በእንባዋ እግሩን አጥባዋለችና። /ማቴ 26:6-13 ፤ ማር 14:3-9 ፤ ዮሐ 12:1 / ከዚህም እያንዳንዳችን ልንማር የሚገባን ነገር አለ። ይኸውም የራሳችንን ኃጢአት በማሰብ ማልቀስና የተወደደ መስዋዕት አድርጎ ለእግዚአብሔር ማቅረብ ነው።

#ሐሙስ

* ከስቅለትና ከትንሣኤ በፊት ያለው ሐሙስ በቤተክርስቲያናችን የተለያዩ ስያሜዎች አሉት።
1.4K viewssara mariyam, 14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-16 14:56:30 #በሰሙነ_ሕማማት_የሚፈጸ_ሥርዓቶች

1, #ስግደት :-
በሰሙነ ሕማማት 41 ጊዜ ኪርያላይሶን 12 ጊዜ አቡነ ዘበሰማያት እየተዜመ እጅግ አብዝቶ ይሰገዳል።

2, #ጸሎት :-
በሰሙነ ሕማማት ከ24 ሰዓት ውስጥ 10 የጸሎትና የንባብ ሰዓታት ይገኛሉ እነዚህም ከጠዋቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት እንዲሁም ከምሽቱ 1 ሰዓት; 3ሰዓት; 6ሰዓት; 9ሰዓት; 11ሰዓት ናቸው።
በእነዚህም ሰዓታት የጌታን ስቃይ ለማዘከር መዝሙረ ዳዊትና ግብረ ሕማማት ድርሳነ ማኅያዊ አብዝተው ይጸለያሉ።

3, #ጾም :-
በሰሙነ ሕማማት ብዙ አዝማደ መባልዕት / አዘውትረን የምንመገባቸው ምግቦች አይበሉም። በዚህም ሳምንት እስከ ምሽቱ #አንድ_ሰዓት እንድንጾም; ይኸውም ቆሎ;ዳቦ;ወኃና ጨው ብቻ እንደታዘዙ በግብረ ሕማማት ላይ ተጽፎ ይገኛል።

4, #አለመሳሳም :-
አይሁድ ጌታችንን ለመስቀል እየተንሾካሾኩ ስለተመካከሩና ይሁዳ ጌታችንን በመሳም አሳልፎ ስለሰጠው መሳሳም አይፈቀድም። መስቀልም በዘመነ ኦሪት የወንጀለኛ መቅጫ የእርግማን ምልክት ስለ ነበር ጌታችን በክቡር ደሙ ቀድሶ የድል አርማ እስኪያደርግልን ድረስ አንሳለመውም ገላ.3:13 ማቴ.10:38 ማቴ. 26:29

5. #አክፍሎት :-
እመቤታችን; ያዕቆብና ዮሐንስ የጌታችን ትንሳኤ ሳናይ እህልና ውኃ አንቀምስም ብለው እስከ ትንሳኤው መቆየታቸውን በማሰብ የሚጾም ነው።

6, #ጉልባን :-
ከባቄላ ከስንዴ ከገብስ የሚዘጋጅ በጸሎተ ሐሙስ ዕለት የሚበላ ንፍሮ ሲሆን ትውፊቱም የስቅለቱ ሐዘን መግለጫ ነው።

7, #ጥብጠባ :-
ይህ ምዕመናን በሰሙነ ሕማማት የፈጸሟቸውን ኃጢአቶች ለካህን እየተናዘዙ በወይራ ቅጠል ቸብቸብ እየተደረጉ ስግደት የሚቀበሉበት ነው። ይህም የጌታ ምሳሌ ነው።

8, #ቄጠማ :-
ጌታችን ብርሃነ ትንሳኤዉን እንደገለጠልን የምናስብበት ሲሆን የእሾህ አክሊል በመድፋቱ ምሳሌም በራሳችን ላይ እናስረዋለን።
እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻም ወድካም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ ለብርሃነ ትንሳኤሁ እግዚአብሔር በፍስሐ ወበሰላም።
1.6K viewssara mariyam, 11:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 22:46:57
2.3K viewssara mariyam, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 22:46:42 ባለማመን ዕለታችንን ጊዜአችንን አናባክን፡፡

ወስብሃት ለእግዚአብሄር!!!!!!
1.8K viewssara mariyam, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-02 22:46:41 እንኳን አደረሳችሁ ለገብር ኄር በአብይ ፆም ቤ/ክን ምን አለ?

የአብይ ፆም 6ኛ ሳምንት ገብርኄር!!!!!
ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ሲሆን በዚህ ቀን ስለ ቅን አገልጋዮች ፤ ለአገልጋዮች የሚያገለግሉበት ፀጋ የሚሰጥ ፤አገልጋዮችን ‹ገብርኄር› እያለ ዋጋ የሚሰጥ አምላክ መሆኑ እየታሰበ ይመለካል፡፡

1. የዕለቱ የቅዱስ ያሬድ መዝሙር ርዕስ
መኑ ውእቱ ገብርኄር
(ቸር አገልጋይ ማን ነው?)
2. በቅዳሴ ሰዓት የሚነቡ የመፅሃፍ ቅዱስ ክፍሎች
1ኛ ጢሞ 2፡1-16(በዲያቆን)
1ኛ ጴጥ5፡1-12(በንፍቀ ዲያቆን)
ሀዋ 1፡6-9(በንፍቀ ካህን)
3. የዕለቱ ምስባክ
ከመ እግበር ፈቃድከ መከርኩ አምላኪየ
ወሕግከኒ በማእከለ ከርስየ
ዜኖኩ ጽድቅከ በማኅበር ዐቢይ

አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድኩ
ህግህም በልቤ ውስጥ ነው
በታላቁም ጉባኤም ጽድቅህን አወራለሁ፡፡ መዝ 39፡8
4. የገብርኄር ወንጌል ማቴ 25፡14-31‹‹‹‹‹››››››ቅዳሴ፡- የባስልዮስ
5. የዕለቱ ትምህርት(ቸር አገልጋይ ማን ነው?)
ቸር አገልጋይ(ገብርኄር) ማቴ 25፡14-30 በዚህ ዕለት በቅዳሴ ሰዓት የተነበበው ቃለ ወንጌል እንዳመለከተን መድሃኒታችን የወንጌል አደራ በምሳሌ እናዳስተማረ ተገንዝበናል፡፡ ትምህርቱም እንድ ባለፀጋ ሰው ነበር፡፡ ወደሩቅ አገር ለመሄድ ባሰበ ጊዜ አገልጋዮችን ጠርቶ ከመንገዱ እስኪመለስ ድረስ ይስራበት ዘንድ ለአንዱ አምስት መክሊት፤ ለሁለተኛው ሁለት ፡ ለሶስተኛው አንድ መክሊት ሰጣቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት መክሊት በማትረፍ አስር መክሊት አደረገው፡፡ ሁለት መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ እጥፍ አትርፎ አራት መክሊት አደረገው፡፡አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ወደ ስራ ከመግባቱ በፊት በልቡ ውስጥ ስጋት ፤ጥርጥር ፤ፍርሃትንና አለማመንን ስላነገሰ ስሰራበት ቢጠፋብኝስ ፤ ቢሰርቁኝስ ቢቀሙኝስ እያለ በማሰብ እሰራለሁ ብዬ ያለኝን ከማጣ ለምን ደብቄ አስቀምጬ በመቆየት ሲመጣ የሰጠኝን አልመልሰም ብሎ መክሊቱን ቆፍሮ ቀበረው፡፡ ጊዜው ሲደርስ ባለንብረቱ መጣና አገልጋዮቹን ይተሳሰባቸው ጀመር፡፡
በቅድሚያ አምስት የወሰደው መጣና ‹ጌታዬ ሆይ አምስት መክሊት ሰጠþኝ ነበር፡፡ ይþውና ሌላ አምስት መክሊት አትርፌያለሁ› ብሎ አስር መክሊት ለጌታው ሰጠ፡፡ ጌታውም መልካም አደረክ አንተ መልካም አገልጋይ (ገብርኄር) በጥቂቱ ስለታመንክ በብዙ ላይ እሾምሃለሁ› ተባለ፡፡
ሁለተኛው ‹ሁለት መክሊት ሰጠþኝ ነበር እነሆ አራት መክሊት› ብሎ እጥፍ ማትረፉን ገልፆ ለጌታው አስረከበ፡፡ እንደ ባለ አምስቱ ‹መልካም አደረግህ ቸር አገልጋይ ነህ በጥቂቱ ስለታመንክ በብዙ ላይ እሾምሃለሁ›› ተባለ
ሶስተኛው መጣ ሰነፍ ቃሉም መራራ ነው፡፡ የሰነፍ አካሉ ብቻ ሳይሆኑ አእምሮውም ሰነፍ ነው፡፡ ጌታው ገንዘቡን ሲጠይቀው ‹ጌታ ሆይ አንተ ካልዘራህበት የምታጭድ ፤ ካልበተንክበት የምትሰበሰብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፡፡ ስለዚህ ፈራሁህ ሄጄም መሬት ቆፍሬ መክሊቴን ጉድጓድ ውስጥ ቀበርኩ፡፡ ገንዘብህን ይþውልህ ውስድ አለው፡፡ ጌታውም ይህን ያህል ጨካኝ እንደሆንኩ ካወቅህ ንብረቴን ከነወለዱ ልትመልስው ይገባህ ነበር፡፡ገንዘቤን ልትሰራበት ሲገባህ ለምን ቀበርከው ብሎ መክሊቱን ወደ እርሱ ወስዶ ለባለ አምስቱ ጨምሩለት ‹ላለው ይጨመርለታል ይትረፈረፍለታልም ለሌላው ግን ያው ያለው ይወሰድበታል › ይህን የማይረባ አገልጋይ ግን ልቅሶ ፤ጥርስ ማፏጨት ወዳለበት ጽኑ የፍርድ ቦታ ውሰዱት አለ ይላል በምሳሌ የተሰጠው የመድሃኒታችን ትምህርት፡፡ የትምህርቱም ትርጉም እንደሚከተለው ነው፡፡
የንብረቱ ባለቤት መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፡፡ ሶስቱ አገልጋዮች ልዩ ልዩ ፀጋ ተሰጥቶአቸው ያሉ ህዝበ ክርስቲያኖች ምሳሌዎች ናቸው፡፡ስጦታው በአኃዝ ሲታይ ልዩነት መኖሩ አንዱ ፀጋ ከሌላው የሚለይ መሆኑን ያሳያል፡፡
የአገልጋዮቹ ባህሪ
1. የመጀመሪያውና የሁለተኛው አገልጋዮች መንፈስ ሁለቱም ሰርቶ ማግኘት እንደሚቻል የሚያምኑ ፤ ከጌታቸው ታማኞች ፤ በስራ ላይ የሚያጋጥማቸውን ችግር በማሰብ ጊዜያቸውን የማያጠፉ ናቸው፡፡ ሁለተኛው አገልጋይም እንደ መጀመሪያው አገልጋይ ለምን አምስት አልተሰጠኝም ብሎ ያለኩርፊያ በተሰጠው የሚሰራ ነው፡፡ ባለ አምስቱ አምስት ሲያተርፍ ባለሁለቱም ሁለት በማትረፍ ተመሳሳይ ትጋት የታየባቸው አገልጋዮች ናቸው፡፡ ዋጋቸው እኩል ነው ፤ለሁለቱም የተሰጠው የክብርም ስም አንድ ነው፡፡ ገብርኄር የሚል የገቡበት የክብር ስፍራ አንድ ነው፡፡ ያም ‹ጌታችን ደስታ ነው› ሁለቱም በጥቂት የታመኑ ነበሩ፡፡ከሰጪው አንጻር ሲታይ የባለ አምስቱ እንደ ባለ ሁለቱም ፤ የባለ ሁለቱ እንደ ባለአምስቱ ጥቂት ነበር፡፡ ሰው በተሰጠው ሳያንጎራጉር ፈጣሪውን ቢያገልግል ክብር ያገኛል፡፡ ለስው ልጅ የሚጠቅመውን ችሎታውን ፤ፀጋውን መቁጠር ሳይሆን በተሰተው ፀጋ ማገልገል ነው፡፡ እነዚህን አገልጋዮች በእውነት በፍቅር በእምነት የሚያገለግሉ የቤተክርሰቲያን አገልጋዮች ያመለክታሉ፡፡
2. የሶስተኛው አገልጋይ ባህሪ ፤ መልካም ጎኑ ስጦታው አነሰኝ አለማለቱ ነው፡፡ በርግጥ ስንፍናውን ስለሚያውቅ ይሆናል፡፡ ይህ ሰው ከስራ ይልቅ በስጋ ጊዜ የሚፈጠረው ችግር አስቀድሞ ይታየዋል፡፡ አንዱን ሁለት ሲያደርግ ሳይሆን ያንኑ ያለውን ሲቀማ ይታየዋል፡፡በጌታው ፊት እንደወንድሞቹ አይነቱን ትርፍ ይዞ ቀርቦ ሲሸለም ሳይሆን ዓይነታውም ጠፍቶበት ለጌታው የሚመልሰውን ሲያጣ ይታየዋል፡፡ በመሆኑም ምንም መስራት አልቻለም፡፡ የተሰጠውን መክሊት ኪሱን አላምነው ብሎ መሬት ቆፍሮ ቀበረው፡፡‹ጨካኝ መሆንህን ስላወቅሁ ይጠፋብኛል ብዬ ብርህን አስቀምጬዋለሁ ይþውልህ ና ወሰድ› ነው ያለው፡፡ ሰነፍ የሚናገረውም አያምርም ተቀምጦ መዐት ከማውራት ዝም አይልም፡፡
ዛሬም ቢሆን ተቀምጠው መዐት የሚያወሩ የእግዚአብሄር ፀጋ የቀበሩ ፤ ባስተምርና መናፍቅ ተከራክሮ ቢረታኝስ ?የማውቀውን እውነት ለመስበክ ስጀምር ቢያሳስሩኝስ? በቤተክርስቲያን ህዝብ በገበያ በልዩ ልዩ ቦታዎች ያሉትን ሃጢያተኞች ብቃወም ጠላት ሆነው ቢነሱብኝ? ለምን ዝም ብዬ ደመውዜን ሳልስራ አልበላም ብለው የሚኖሩ ስንት አገልጋዮች አሉ፡፡ የዚህ ሰው ችግሩ መክሊቱ አንድ መሆኑ ሳይሆን በዚያው በተሰተው አለመስራቱ ነው፡፡ እያንዳንዱ አምኖ በመቀበል ሊያገለግል ይገባዋል፡፡ ባለ ሁለት በባለ አምስቱ ፤ ባለ አንዱ በባለ ሁለቱ ሊቀና አይገባውም፡፡ ሁሉም ሊቀ ጳጳስ ፤ ጳጳስ ፤ ቄስ አይሆንም፡፡ ሁሉም ግን በተሰጠው ፀጋ ቢያገለግል እውነተኞች ሊቃነ ጳጳሳት ፤ ጳጳሳት ፤ ቀሳውስት የሚያገኙትን ዋጋ ያገኛል፡፡ ሁሉም ባለ ራዕይ ፤ ወንጌላዊ ፤ዘማሪ ፤ፈዋሽ ሊሆን አይችልም፡፡ ለእያንዳንዱ ልዩ ልዩ ፀጋ አለው፡፡ ሁሉም በፀጋው ቢያገለግል እኩል ዋጋ ያገኛል፡፡
ወንድሜ አንተስ ፀጋህ ምንድን ነው? ፀጋህን ታውቀዋለህ? ታገለግልበታለህን? አንቺስ እህቴ? መቼም ክርስቲያን ሁሉ የክርስቶስ አካል ነው፡፡ የስራ ክፍል የሌለው የአካል ክፍል ደግሞ የለም፡፡ አንተም/አንቺም የክርሰቶስ አካል ነህ /ነሽ፡፡ ስለዚህ አካሉ በመሆንህ ደግሞ ፀጋ አለህ/አለሽ ፡፡ በመሆኑም እንደ ፀጋችን እናገልግል፡ ፀጋውን እንቀበለው፤ ወንጌልን በጊዜውም አለጊዜውም ሲሞላልንም ሲጎድልብንም እንስበክ ፤ ሀብታሙ ይመፅውት ፤ መምህሩ ያስተምር ፤ ዘማሪው ይዘምር ፤ ፀሃፊው ይፃፍ ፤ ሁሉም በፀጋው ያገልግል፡፡እንድ መክሊት እንደተቀበለው ሰው ነገ እንዲህ ብሆንስ ፤እንደዚያ ቢፈጠርስ እያልን
2.0K viewssara mariyam, 19:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 07:43:12 የሊቀመላዕክት ቅዱስ ዑራኤል ተአምር ይህ ነው
1.5K viewssara mariyam, 04:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-26 21:12:26 Watch "የቀጥታ ስርጭት ከቅዱስ ፊልጶስ ካቴድራል" on YouTube


1.7K views ቀላያት, 18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ